መዝገበ ቅዱሳን
24.2K subscribers
1.97K photos
9 videos
6 files
26 links
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው! መ/ሳ 1÷7
Bewust mesimer lemanegager
@Yesadkusitota
የሰማነውን እንናገራለን
ያየነውን እንመሰክራለን
Download Telegram
ይህንን ያሉት እርሱ የሊቃውንቱን ቅዳሴ አያውቅምና በሰው ፊት እንዲዋረድ ነው። እንዲህም ብለው ባለመማሩ ተሳለቁበት። አባ ሕርያቆስ ግን እያዘነ ወደ መንበሩ ዞረ። ድንግልንም "እመቤቴ መናቄን መገፋቴን ተመልከች" አላት።

ወዲያው ግን ድንግል ማርያም ወርዳ ቀጸበችው (ጠራችው)። በዘርፋፋው ቀሚሷ ላይም ረቂቅ የሆነ ቅዳሴን አሳየችው። ደጉ ሰው ደስ ብሎት "ጐሥዐ ልብየ" ሲል 2ቱ እግሮቹ ከመሬት ከፍ አሉ። እርሱም "ወአነ አየድእ ቅዳሴሃ ለማርያም" ብሎ እስከ ኃዳፌ ነፍሱ ድረስ አደረሰው።

ሕዝቡና ካህናቱ በሆነው ነገር ሲደነቁ አንዳንዶቹ "ዝም ብሎ ነው የቀባጠረ" አሉ። ቅዱሱ ግን ቅዳሴ ማርያምን በብራና ጠርዞ በሕዝቡ መካከል ድውይ ፈወሰበት። እሳት ሳያቃጥለው: ውሃ ሳይደመስሰው ቀረ።

መጽሐፈ ቅዳሴው ሙትንም አስነስቷል። ከዚህች ሰዓት ጀምሮ በዘመኑ ቁጥር 1 ሊቅሙ ሆነ። ብዙ መጻሕፍትን ሲተረጉም አጠቃላይ ድርሰቶቹም እልፍ (10,000) ናቸው። ሊቁ እንዲህ በንጹሕ ተመላልሶ ዐርፏል። ይህቺ ቀን ለቅዱሱ የልደቱና ዕረፍቱ መታሰቢያ ናት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ማትያስ_ዘፈጠጋር

ዳግመኛም በዚህች ቀን የፈጠጋሩ አቡነ ማትያስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የበቁ፣ የነቁ፣ ምግባር ሃይማኖታቸው እንደፀሐይ ያበራ፣ ከተጋድሏቸውም ብዛት የተነሣ ከብቃት ደረጃ ላይ የደረሱ ቅዱሳን የሆኑ ደገኛ መምህራንን በማሰልጠን በአንብሮተ እድ ዓሥራ ሁለት ዓሥራ ሁለት አድርገው እየሾሙ ለስብከተ ወንጌል በመላ አገራችን ያሰራጯቸው ነበር፡፡ እነዚህም ንቡራነ እድ ከዋክብት በመላ አገራችን የወንጌልን ብርሃን ያበሩ ቅዱሳን ናቸው፡፡

በመጀመሪያ በተክለ ሃይማኖት በአንብሮተ እድ የሾሟቸው 12ቱ ከዋክብት የወረቡ አኖሬዎስ፣ የሞረቱ ዜና ማርቆስ፣ የጽላልሹ ታዴዎስ፣ የድምቤው ገብረ ክርስቶስ፣ የወገጉ ሳሙኤል፣ የእናርያው ዮሴፍ፣ የዳሞቱ አድኃኒ፣ የወጁ ኢሳይያስ፣ የመንዝ የመራቤቴውና የወለቃው መርቆሬዎስ፣ የመሐግሉ ቀውስጦስ፣ የፈጠጋሩ ማትያስ፣ የደዋሮው ተስፋ ሕፃን፣ የእንሳሮው ዳዊት፣ የዘልዓቱ ናታን ናቸው፡፡

የፈጠጋሩ ማትያስም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሾሟቸው ከ12 ንቡራነ እድ ውስጥ አንዱ ሲሆኑ ቁጥራቸውም ሁለተኛ ናቸው፡፡ ደብረ ሊባኖስን ያጥኑ የነበረው በሰኔ ወር ሲሆን በገዳሙም 13ኛው አባት በመሆን በመምህርነት አገልግለዋል፡፡ በሀገራችን ተዘዋውረው በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ወንጌልን ሲሰብኩ ኖረው በሰላም ዐረፈዋል፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥቅምት እና #ከገድላት_አንደበት)