መዝገበ ቅዱሳን
23.5K subscribers
1.96K photos
9 videos
6 files
28 links
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው! መ/ሳ 1÷7
Bewust mesimer lemanegager
@Yesadkusitota
የሰማነውን እንናገራለን
ያየነውን እንመሰክራለን
Download Telegram
ዳግመኛም መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከዕርገቱ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት የሞቱን መታሰቢያ እንዲያደርጉ ነግሯቸዋልና፡፡ ሕማሙንና ሞቱንም እንዲዘክሩ አዟቸዋልና አሁንም ያንን ሁሉ የመድኃኔዓለምን ሞቱን ያላሰበና የሞቱን መታሰቢያ በዓል ያላከበረና እርሱንም የማይወደው ቢኖር ዕድል ፈንታው ጽዋ ተርታው ከአይሁድ ጋር ነው፡፡
የአምላካችንን የመድኃኔዓለምን ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ተባብረን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ከእርሱ ለመተባበር ያብቃን!

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_መቃርስ_ታላቁ

ዳግመኛም በዚህች ቀን በገዳም ለሚፈጸም ተጋድሎ ፋና የሆነ በአስቄጥስ ገዳም ለሚኖሩ መነኰሳት ሁሉ አባት የሆነ የከበረ አባት ታላቁ አባ መቃርስ አረፈ። ይህም የከበረ አባት በግብጽ ደቡብ መኑፍ ከሚባል አውራጃ ሳሱይር ከሚባል አውራጃ መንደር ከሚኖሩ ሰዎች ወገን ነው ።

ወላጆቹም ደጎች ዕውነተኞች ነበሩ። አባቱ አብርሃም እናቱም ሣራ ይባላሉ። እናቱም እንደ ኤልሳቤጥና እንደ ሣራ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ጸንታ የምትኖር ናት አባቱም በፈሪሃ እግዚአብሔር ሁኖ ንጽሕናውንና ቅድስናውን ጠብቆ ሁልጊዜ ቤተ ክርስቲያን በማገልገል ጸንቶ ይኖራል እግዚአብሔርም በላያቸው በረከቱን አሳድሮ በሥራቸው ሁሉ ከፍ ከፍ አደረጋቸው።

ለድኆችም የሚመጸውቱ ለሰው ሁሉ የሚራሩ ናቸው። በጾም በጸሎትም ተወስነው እንዲህ ባለገድል ሲኖሩ ግን ልጅ አልነበራቸውም። ለአብርሃምም በሌሊት ራእይ ከእግዚአብሔር ዘንድ በልጅ አምሳል ተገለጠለት በዓለሙ ሁሉ የሚታወቅ ብዙ መንፈሳውያን ልጆችን የሚወልድ ልጅን ይሰጠው ዘንድ እግዚአብሔር አለው ብሎ አስረዳው።

ከዚህም በኋላ ይህን የከበረ ልጅ መቃርዮስን እግዚአብሔር ሰጠው። ትርጓሜውም ብፁዕ ማለት ነው በላዩም የእግዚአብሔር ጸጋ አደረበት ለወላጆቹም ይታዘዝና ያገለግል ነበር ሊያጋቡትም አሰቡ እርሱ ግን አይሻም ነበር ፈቃዳቸውን ይፈጽም ዘንድ ግድ ብለው አጋቡት ወደ ሙሽራዪቱም በገባ ጊዜ ራሱን እንደታመመ ሰው አደረገ እንዲህም ሁኖ ብዙ ቀን ኖረ።

ከዚያም በኋላ አባቱን ተወኝ ወደ ገዳም ልሒድ ከበሽታዬ ጥቂት ጤና ባገኝ አለው እግዚአብሔር ወደሚወደው ሥራ ይመራው ዘንድ ሁልጊዜ በጾምና በጸሎት ሁኖ ይለምነው ነበር። ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ በረሀ ሔደ ከበረሀውም በገባ ጊዜ ራእይን አየ ስድስት ክንፍ ያለው ኪሩብ እጅና እግሩን ይዞ ወደ ተራራ ላይ እንደሚያወጣውና የአስቄጥስን በረሀ ምሥራቋን ምዕራቧን የዚያችን በረሀ አራት ማእዘንዋን አሳይቶ እነሆ ይቺን በረሀ መላዋን ላንተና ለልጆችህ ርስት አድርጎ እግዚአብሔር ሰጥቶሃል አለው።

ከበረሀውም በተመለሰ ጊዜ ያቺ ብላቴና ታማ አገኛት ጥቂት ቆይታ ወዲያው በድንግልናዋ እንዳለች አረፈች። የክብር ባለቤት እግዚአብሔርንም አመሰገነው። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ እናት አባቱ አረፉ የተዉለትንም ገንዘብ በሙሉ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጠ።

የሳሱይር ሰዎች ግን ዕውነተኛነቱንና ቅድስናውን አይተው ቅስና አሾሙት። ከከተማውም ውጭ ቤት ሠሩለት ሥጋውንና ደሙን ይቀበሉ ዘንድ ወደርሱ ይሔዱ ነበር።

በዚያች አገርም አንዲት ድንግል ብላቴና ነበረች ከአንድ ጐልማሳ ጋርም አመንዝራ ፀነሰች ጉልማሳውም አባትሽ ድንግልናሽን ማን አጠፋው ብሎ ሲጠይቅሽ መቃርስ የሚባለው ባሕታዊ ቄስ እርሱ ስለ ደፈረኝ ነው በዪው ብሎ መከራት።

ፅንሷም በታወቀ ጊዜ አባቷ ይህን አሳፋሪ ሥራ በአንቺ ላት የሠራብሽ ማነው ብሎ ጠየቃት። እርሷም በአንዲት ቀን መቃርስ ወደሚባለው ቄስ ሒጄ ሳለሁ በኃይል ይዞኝ ከእኔ ጋራ ተኛ ስለዚህ ከእርሱ ፀነስኩ ብላ መለሰችለት።

ወላጆቿና ቤተሰቦቿም በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቆጡ ከብዙ ሰዎችም ጋራ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሒደው ይዘው ከበዓቱ አወጡት እርሱ ግን ምን እንደሆነ አላወቀም። ለመሞት እስቲቃረብም አጽንተው ደበደቡት እርሱም ኃጢአቴ ምንድናት እናንተ ያለ ርኅራኄ ትደበድቡኛላችሁና እያለ ይጠይቃቸው ነበር።

ከዚህ በኋላ በፍሕም የጠቆሩ ገሎችን በአንገቱ ላይ በገመድ አንጠልጥለው ወዲያና ወዲህ እየጐተቱ የልጃችንን ድንግልና ያጠፋ ይህ ነው እያሉ እንደ እብድ በላዩ ይጮኹ ጀመር።

በዚያን ጊዜ መላእክት እንደሰው ተገልጠው የሚያሠቃዩትን ሰዎች ይህ ተጋዳይ ምን አደረገ አሏቸው። እነርሱም በልጃቸው ላይ የኀፍረትን ሥራ እንደሠራ አድርገው መልሰው ነገሩአቸው። እነዚያ መላእክትም ይህ ነገር ሐሰት ነው እኛ ይህን ሰው ከታናሽነቱ ጀምሮ እስከዚች ቀን እናውቀዋለን እርሱ የተመረጠ ጻድቅ ሰው ነውና አሏቸው የታሠረበትንም ፈትተው ከላዩ ገሎችን ጣሉ እነዚያ ክፉዎች ግን ዋስ እስከሚሰጠን ድረስ አንለቀውም አሉ። እጀ ሥራውን የሚሸጥለት አንድ ሰው መጣ ለልጅቷም በየጊዜው ምግቧን ሊሰጣት ዋስ ሆነው ከዚያ በኋላ አሰናብተው ወደ በዓቱ ተመልሶ ገባ።

ከዚያቺም ቀን ጀምሮ ራሱን በራሱ መቃርስ ሆይ እንግዲህ ባለሚስትና ባለልጅ ሁነኻል ሌሊትና ቀን መሥራት ይገባሃል እያለ ያቺ ሐሰተኛ ልጅ የምትወልድበት ጊዜ እስኪደርስ ድረስ እንቅቦችን ቅርጫቶችን እየሠራ ለዚያ ወዳጅ ለሆነውና ለሚያገለግለው ወንድም ይሰጠውና ያም ሰው እየሸጠ ለዚያች ሐሰተኛ ልጅ እየሰጠ ኖረ።

የምትወልድበትም ቀን ሲደርስ እጅግ አስጨነቃት በታላቅ ሥቃይም ውስጥ አራት ቀኖች ያህል ኖረች። ለሞትም ተቃረበች እናቷም ከአንቺ የሆነው ምንድነው የተሠራ ሥራ አለና ንገሪኝ አለቻት። እርሷም በእግዚአብሔር አገልጋይ ላይ ዋሽቻለሁና ያመነዘርኩት ከዕገሌ ገ ልማሳ ጋር ሲሆን በዕውነት ሞት ይገባኛል አለቻት።

አባትና እናቷም በሰሙ ጊዜ ደንግጠው እጅግ አዘኑ የአገር ሰዎችም ሁሉም ተሰበሰቡ በእርሱ ላይ የሰሩትን በደል ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሒደው ለመኑት። ያን ጊዜ በበረሀ ያየውን ያንን ራእይ አስታውሶ ይቅር አላቸው ቀድሶም ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው።

ክንፉ ስድስት የሆነ ኪሩብ ደግሞ ተገለጠለት ትርጓሜው የልብ ሚዛን ወደተባለ ወደ አስቄጥስ ገዳም እጁን ይዞ መርቶ አደረሰው። ቅዱስ መቃርስም ያንን ኪሩብ ጌታዬ ሆይ በውስጡ የምኖርበትን ቦታ ወስንልኝ አለው። ያ ኪሩብም አልወስንልህም የእግዚአብሔርንም ትእዛዝ አትተላለፍ እነሆ ይህ ገዳም ሁለመናው ላንተ ተሰጥቷልና ወደፈለግህበት ሒደህ ተቀመጥ ብሎ መለሰለት።

ቅዱስ መቃርስም የቅዱሳን ሮማውያን የመኪሲሞስና የደማቴዎስ ቦታ ወደ ሆነው ከውስጥኛው በረሀ ገብቶ ኖረ። እነርሱ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ ከእርሱ አቅራቢያ ኑረዋልና ከዕረፍታቸው በኋላ ግን ሒዶ በዚያ ቦታ እንዲኖር የእግዚአብሔር መልአክ አዘዘው። ይኸውም ዛሬ የእርሱ ገዳም የሆነው መልአኩ ይህ ገዳም በልጆችህ በመክሲሞስና በደማቴዎስ በስማቸው ይጠራል ስለ አለው እስከዚች ቀን ደብረ ብርስም ተብሎ ይጠራል ትርጓሜውም የሮም ገዳም ማለት ነው።

የከበረ አባ መቃርስም ታናሽ በዓት ሠራ። በውስጥዋም ሆኖ ያለ ማቋረጥ በጾም በጸሎት በስግደትም በመትጋት ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ።
ሰይጣናትም ተገልጠው የሚመጡበትና በቀንም በሌሊትም በግልጥ የሚዋጉት ሆኑ።

በጸምና በጸሎት ሲጋደል ሰይጣናት እየተዋጉት ዕረፍትን ስለ አላገኘ በልቡ አሰበ በዓለም ውስጥ ሳለሁ የቅዱስ አባ እንጦንዮስን ዜና ሰምቻለሁ የምንኵስናን ሥርዓት ያስተማረኝና ይመራኝ ዘንድ ተነሥቼ ወደርሱ ልሒድ የረከሱ ሰይጣናት የመከሩትን ምክራቸውን እገለብጥ ዘንድ እርሱ ዕውቀትንና ማስተዋልን ይሰጠኛልና አለ።
ዳግመኛም መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከዕርገቱ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት የሞቱን መታሰቢያ እንዲያደርጉ ነግሯቸዋልና፡፡ ሕማሙንና ሞቱንም እንዲዘክሩ አዟቸዋልና አሁንም ያንን ሁሉ የመድኃኔዓለምን ሞቱን ያላሰበና የሞቱን መታሰቢያ በዓል ያላከበረና እርሱንም የማይወደው ቢኖር ዕድል ፈንታው ጽዋ ተርታው ከአይሁድ ጋር ነው፡፡
የአምላካችንን የመድኃኔዓለምን ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ተባብረን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ከእርሱ ለመተባበር ያብቃን!

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_መቃርስ_ታላቁ

ዳግመኛም በዚህች ቀን በገዳም ለሚፈጸም ተጋድሎ ፋና የሆነ በአስቄጥስ ገዳም ለሚኖሩ መነኰሳት ሁሉ አባት የሆነ የከበረ አባት ታላቁ አባ መቃርስ አረፈ። ይህም የከበረ አባት በግብጽ ደቡብ መኑፍ ከሚባል አውራጃ ሳሱይር ከሚባል አውራጃ መንደር ከሚኖሩ ሰዎች ወገን ነው ።

ወላጆቹም ደጎች ዕውነተኞች ነበሩ። አባቱ አብርሃም እናቱም ሣራ ይባላሉ። እናቱም እንደ ኤልሳቤጥና እንደ ሣራ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ጸንታ የምትኖር ናት አባቱም በፈሪሃ እግዚአብሔር ሁኖ ንጽሕናውንና ቅድስናውን ጠብቆ ሁልጊዜ ቤተ ክርስቲያን በማገልገል ጸንቶ ይኖራል እግዚአብሔርም በላያቸው በረከቱን አሳድሮ በሥራቸው ሁሉ ከፍ ከፍ አደረጋቸው።

ለድኆችም የሚመጸውቱ ለሰው ሁሉ የሚራሩ ናቸው። በጾም በጸሎትም ተወስነው እንዲህ ባለገድል ሲኖሩ ግን ልጅ አልነበራቸውም። ለአብርሃምም በሌሊት ራእይ ከእግዚአብሔር ዘንድ በልጅ አምሳል ተገለጠለት በዓለሙ ሁሉ የሚታወቅ ብዙ መንፈሳውያን ልጆችን የሚወልድ ልጅን ይሰጠው ዘንድ እግዚአብሔር አለው ብሎ አስረዳው።

ከዚህም በኋላ ይህን የከበረ ልጅ መቃርዮስን እግዚአብሔር ሰጠው። ትርጓሜውም ብፁዕ ማለት ነው በላዩም የእግዚአብሔር ጸጋ አደረበት ለወላጆቹም ይታዘዝና ያገለግል ነበር ሊያጋቡትም አሰቡ እርሱ ግን አይሻም ነበር ፈቃዳቸውን ይፈጽም ዘንድ ግድ ብለው አጋቡት ወደ ሙሽራዪቱም በገባ ጊዜ ራሱን እንደታመመ ሰው አደረገ እንዲህም ሁኖ ብዙ ቀን ኖረ።

ከዚያም በኋላ አባቱን ተወኝ ወደ ገዳም ልሒድ ከበሽታዬ ጥቂት ጤና ባገኝ አለው እግዚአብሔር ወደሚወደው ሥራ ይመራው ዘንድ ሁልጊዜ በጾምና በጸሎት ሁኖ ይለምነው ነበር። ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ በረሀ ሔደ ከበረሀውም በገባ ጊዜ ራእይን አየ ስድስት ክንፍ ያለው ኪሩብ እጅና እግሩን ይዞ ወደ ተራራ ላይ እንደሚያወጣውና የአስቄጥስን በረሀ ምሥራቋን ምዕራቧን የዚያችን በረሀ አራት ማእዘንዋን አሳይቶ እነሆ ይቺን በረሀ መላዋን ላንተና ለልጆችህ ርስት አድርጎ እግዚአብሔር ሰጥቶሃል አለው።

ከበረሀውም በተመለሰ ጊዜ ያቺ ብላቴና ታማ አገኛት ጥቂት ቆይታ ወዲያው በድንግልናዋ እንዳለች አረፈች። የክብር ባለቤት እግዚአብሔርንም አመሰገነው። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ እናት አባቱ አረፉ የተዉለትንም ገንዘብ በሙሉ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጠ።

የሳሱይር ሰዎች ግን ዕውነተኛነቱንና ቅድስናውን አይተው ቅስና አሾሙት። ከከተማውም ውጭ ቤት ሠሩለት ሥጋውንና ደሙን ይቀበሉ ዘንድ ወደርሱ ይሔዱ ነበር።

በዚያች አገርም አንዲት ድንግል ብላቴና ነበረች ከአንድ ጐልማሳ ጋርም አመንዝራ ፀነሰች ጉልማሳውም አባትሽ ድንግልናሽን ማን አጠፋው ብሎ ሲጠይቅሽ መቃርስ የሚባለው ባሕታዊ ቄስ እርሱ ስለ ደፈረኝ ነው በዪው ብሎ መከራት።

ፅንሷም በታወቀ ጊዜ አባቷ ይህን አሳፋሪ ሥራ በአንቺ ላት የሠራብሽ ማነው ብሎ ጠየቃት። እርሷም በአንዲት ቀን መቃርስ ወደሚባለው ቄስ ሒጄ ሳለሁ በኃይል ይዞኝ ከእኔ ጋራ ተኛ ስለዚህ ከእርሱ ፀነስኩ ብላ መለሰችለት።

ወላጆቿና ቤተሰቦቿም በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቆጡ ከብዙ ሰዎችም ጋራ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሒደው ይዘው ከበዓቱ አወጡት እርሱ ግን ምን እንደሆነ አላወቀም። ለመሞት እስቲቃረብም አጽንተው ደበደቡት እርሱም ኃጢአቴ ምንድናት እናንተ ያለ ርኅራኄ ትደበድቡኛላችሁና እያለ ይጠይቃቸው ነበር።

ከዚህ በኋላ በፍሕም የጠቆሩ ገሎችን በአንገቱ ላይ በገመድ አንጠልጥለው ወዲያና ወዲህ እየጐተቱ የልጃችንን ድንግልና ያጠፋ ይህ ነው እያሉ እንደ እብድ በላዩ ይጮኹ ጀመር።

በዚያን ጊዜ መላእክት እንደሰው ተገልጠው የሚያሠቃዩትን ሰዎች ይህ ተጋዳይ ምን አደረገ አሏቸው። እነርሱም በልጃቸው ላይ የኀፍረትን ሥራ እንደሠራ አድርገው መልሰው ነገሩአቸው። እነዚያ መላእክትም ይህ ነገር ሐሰት ነው እኛ ይህን ሰው ከታናሽነቱ ጀምሮ እስከዚች ቀን እናውቀዋለን እርሱ የተመረጠ ጻድቅ ሰው ነውና አሏቸው የታሠረበትንም ፈትተው ከላዩ ገሎችን ጣሉ እነዚያ ክፉዎች ግን ዋስ እስከሚሰጠን ድረስ አንለቀውም አሉ። እጀ ሥራውን የሚሸጥለት አንድ ሰው መጣ ለልጅቷም በየጊዜው ምግቧን ሊሰጣት ዋስ ሆነው ከዚያ በኋላ አሰናብተው ወደ በዓቱ ተመልሶ ገባ።

ከዚያቺም ቀን ጀምሮ ራሱን በራሱ መቃርስ ሆይ እንግዲህ ባለሚስትና ባለልጅ ሁነኻል ሌሊትና ቀን መሥራት ይገባሃል እያለ ያቺ ሐሰተኛ ልጅ የምትወልድበት ጊዜ እስኪደርስ ድረስ እንቅቦችን ቅርጫቶችን እየሠራ ለዚያ ወዳጅ ለሆነውና ለሚያገለግለው ወንድም ይሰጠውና ያም ሰው እየሸጠ ለዚያች ሐሰተኛ ልጅ እየሰጠ ኖረ።

የምትወልድበትም ቀን ሲደርስ እጅግ አስጨነቃት በታላቅ ሥቃይም ውስጥ አራት ቀኖች ያህል ኖረች። ለሞትም ተቃረበች እናቷም ከአንቺ የሆነው ምንድነው የተሠራ ሥራ አለና ንገሪኝ አለቻት። እርሷም በእግዚአብሔር አገልጋይ ላይ ዋሽቻለሁና ያመነዘርኩት ከዕገሌ ገ ልማሳ ጋር ሲሆን በዕውነት ሞት ይገባኛል አለቻት።

አባትና እናቷም በሰሙ ጊዜ ደንግጠው እጅግ አዘኑ የአገር ሰዎችም ሁሉም ተሰበሰቡ በእርሱ ላይ የሰሩትን በደል ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሒደው ለመኑት። ያን ጊዜ በበረሀ ያየውን ያንን ራእይ አስታውሶ ይቅር አላቸው ቀድሶም ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው።

ክንፉ ስድስት የሆነ ኪሩብ ደግሞ ተገለጠለት ትርጓሜው የልብ ሚዛን ወደተባለ ወደ አስቄጥስ ገዳም እጁን ይዞ መርቶ አደረሰው። ቅዱስ መቃርስም ያንን ኪሩብ ጌታዬ ሆይ በውስጡ የምኖርበትን ቦታ ወስንልኝ አለው። ያ ኪሩብም አልወስንልህም የእግዚአብሔርንም ትእዛዝ አትተላለፍ እነሆ ይህ ገዳም ሁለመናው ላንተ ተሰጥቷልና ወደፈለግህበት ሒደህ ተቀመጥ ብሎ መለሰለት።

ቅዱስ መቃርስም የቅዱሳን ሮማውያን የመኪሲሞስና የደማቴዎስ ቦታ ወደ ሆነው ከውስጥኛው በረሀ ገብቶ ኖረ። እነርሱ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ ከእርሱ አቅራቢያ ኑረዋልና ከዕረፍታቸው በኋላ ግን ሒዶ በዚያ ቦታ እንዲኖር የእግዚአብሔር መልአክ አዘዘው። ይኸውም ዛሬ የእርሱ ገዳም የሆነው መልአኩ ይህ ገዳም በልጆችህ በመክሲሞስና በደማቴዎስ በስማቸው ይጠራል ስለ አለው እስከዚች ቀን ደብረ ብርስም ተብሎ ይጠራል ትርጓሜውም የሮም ገዳም ማለት ነው።

የከበረ አባ መቃርስም ታናሽ በዓት ሠራ። በውስጥዋም ሆኖ ያለ ማቋረጥ በጾም በጸሎት በስግደትም በመትጋት ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ።
ሰይጣናትም ተገልጠው የሚመጡበትና በቀንም በሌሊትም በግልጥ የሚዋጉት ሆኑ።

በጸምና በጸሎት ሲጋደል ሰይጣናት እየተዋጉት ዕረፍትን ስለ አላገኘ በልቡ አሰበ በዓለም ውስጥ ሳለሁ የቅዱስ አባ እንጦንዮስን ዜና ሰምቻለሁ የምንኵስናን ሥርዓት ያስተማረኝና ይመራኝ ዘንድ ተነሥቼ ወደርሱ ልሒድ የረከሱ ሰይጣናት የመከሩትን ምክራቸውን እገለብጥ ዘንድ እርሱ ዕውቀትንና ማስተዋልን ይሰጠኛልና አለ።