መዝገበ ቅዱሳን
24.2K subscribers
1.97K photos
9 videos
6 files
26 links
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው! መ/ሳ 1÷7
Bewust mesimer lemanegager
@Yesadkusitota
የሰማነውን እንናገራለን
ያየነውን እንመሰክራለን
Download Telegram
#ጥቅምት_6

ጥቅምት ስድስት በዚህች ቀን እመ ሳሙኤል ነቢይ #ቅድስት_ነቢይት_ሐና ያረፈችበት፣ ቅዱስ አባት #አባ_ጰንጠሌዎን ያረፈበት፣ #ዕንባቆም_ነቢይ መታሰቢያው፣ የሀገረ አቴና ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ በሰማዕትነት ያረፈበት እና የሴት ልጅ #ቅዱስ_ሄኖስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ነቢይት_ሐና

ጥቅምት ስድስት በዚህች ቀን የታላቁ ነቢይና ካህን የሳሙኤል እናት ቅድስት ነቢይት ሐና አረፈች።

ይችም ቅድስት ከሌዊ ነገድ ናት የታኅርም ልጅ ሕልቃና አገባት ፍናና የምትባልም ሌላ ሚስት አለችው እርሷም ወላድ በመሆኗ ሐና ልጅ ስለሌላት መካንም ስለሆነች ሁልጊዜ ትገዳደራት ነበር።

ሐና ግን ፈጽማ በማዘን አትበላም አትጠጣም ባሏ ሕልቃናም ያረጋጋታል ማረጋጋቱንም አልተቀበለችውም በሊቀ ካህናቱ በኤሊ ዘመንም ወደቤተ እግዚአብሔር ወጣች እያለቀሰችና እያዘነች በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች እንዲህም ብላ ስለትን ተሳለች አቤቱ ልጅ የሰጠኸኝ እንደሆነ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለአንተ የሚያገለግል አደርገዋለሁ።

ካህኑ ኤሊም አያትና እርሷ የወይን ጠጅ ጠጥታ እንደ ሰከረች አሰበ እርሷ በዝምታ በልቧ ትጸልይ ነበርና በቊጣና በግሣጼ የወይን ጠጅ ጠጥተሽ ወደዚህ ወደ እግዚአብሔር ቤት ለምን መጣሽ አሁን ሒጂ ስካርሺን በእንቅልፍ አስወግጂ አላት።

እርሷም እንዲህ አለችው የወይን ጠጅ ከቶ አልጠጣሁም ልጅ ያጣሁ በመሆኔ በልቤ አዝናለሁ እንጂ ካህን ኤሊም አጽናናት እንዲሁም ብሎ ባረካት የእስራኤል ፈጣሪ የለመንሽውን ይስጥሽ በሰላም ሒጂ በቃሉም አምና ወደ ቤቷ ገባች።

ከዚህም በኋላ ፀንሳ ወንድ ልጅን ወለደች ስሙንም ሳሙኤል ብላ ጠራችው። ጡትንም በአስጣለችው ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዛው ወጣች ወደ ካህን ኤሊም አቀረበችውና እንዲህ ብላ አስረዳችው ከአሁን በፊት ልጅን ይሰጠኝ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ስጸልይና ስለምን ያየኸኝ ሴት ነኝ ልመናዬንም ሰምቶ ይህን ልጅ ሰጠኝ አሁንም በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ይሆን ዘንድ አመጣሁት።

ከዚህም በኋላ ሐና እግዚአብሔርን አመሰገነችው። ልቤ በእግዚአብሔር አምኖ ጸና የሚለውን ጸሎትና ትንቢት እስከ መጨረሻው ተናገረች። ይቺም በዳዊት መዝሙር መጨረሻ ከሙሴ መኀልይ ቀጥላ ተጽፋለች።

ከዚህም በኋላ እግዚአብሔርን አገልግላ በሰላም አረፈች።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ጰንጠሌዎን

ዳግመኛም በዚችም ቀን በዋሻ ውስጥ የሚኖር ቅዱስ አባት አባ ጰንጠሌዎን አረፈ። ይህም ቅዱስ በሮሜ አገር በንጉሥ ቀኝ ከሚቀመጡ ከከበሩ ሰዎች ወገን የተወለደ ነው ። በታናሽነቱም ጊዜ ወደ መነኰሳት ገዳም ወስደውት በበጎ ምክር ዕውቀትን እየተማረ በመጸለይና በመጾም በዚያ አደገ።

ከዚህም በኋላ ከቅዱሳን ከስምንቱ ባልንጀሮቹ ጋር ወደ ኢትዮጵያ በንጉሥ አልዓሜዳ ዘመን መጣ በአንድነትም ጥቂት ዘመናት ኑረው ከዚህም በኋላ እርስበርሳቸው ተለያዩ ቅዱስ ጰንጠሌዎንም ከታናሽ ተራራ ላይ ወጥቶ ርዝመቱ አምስት ክንድ አግድመቱ ሁለት ስፋቱ ሦስት ክንድ የሚሆን ዋሻ ለራሱ ሠራ ጠፈሩም አንድ ደንጊያ ነው ከጥቂት ቀዳዳ በቀር በር የለውም።

በውስጡም ሳይቀመጥ ሳይተኛ ያለመብልና ያለ መጠጥ አርባ አምስት ዓመት ኖረ ቆዳው ከዐጥንቱ እስከሚጣበቅ በዕንባ ብዛትም ቅንድቡ ተመለጠ። በሽተኞችን በማዳን የዕውሮችንም ዐይኖች በመግለጥ ብዙ ተአምራትን አደረገ።

በአንዲትም ቀን በማታ ጊዜ ዕንጨት ተከለ አሰከሚነጋ ድረስም አድጎ ትልቅ ዛፍ ሆነ ወዲያውም ደረቀና ደቀ መዝሙሩ ፈልጦ አነደደው ፍሙንም በልብሱ ቋጥሮ ለማዕጠንት ወሰደው።

የናግራንን አገር ያጠፋትን ምእመናኖችንም የገደላቸውን አይሁዳዊ ንጉሥ ሒዶ ሊወጋው ንጉሥ ካሌብ በአሰበ ጊዜ በጸሎቱ ይረዳው ዘንድ ይህን አባት ጰንጠሌዎንን ለመነው እርሱም በሥራው ሁሉ ላይ ችሎታ ያለው እግዚአብሔር በጠላቶችህ ላይ ድል አድራጊነትን ሰጥቶህ በደኀና በፍቅር አንድነት ትመለሳለህ አለው።

ንጉሥ ካሌብም ከናግራን ሀገር በደረሰ ጊዜ ከከሀዲው ንጉሥ ከፊንሐስ ጋር ተዋጋ ድል አድርጓቸውም ከሀድያንን ሁሉ እንደ ቅጠል እስቲረግፉ አጠፋቸው አባ ጰንጠሌዎንንም በጦርነቱ መካከል ጠላቶችን ሲአሳድዳቸው እንዳዩት ብዙዎች ምስክሮች ሆኑ።

ከዚህም በኋላ ንጉሥ ካሌብ ከድል አድራጊነት ጋር በተመለሰ ጊዜ መንግሥቱን ትቶ በዚህ አባት እጅ መነኰሰ ከዋሻ ውስጥም ገብቶ በጾምና በጸሎት እየተጋደለ ኖረ።

ይህም ቅዱስ አባ ጰንጠሌዎን ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጣ ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን የሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ቃል ኪዳን ሰጠው እንግዲህስ ድካም ይበቃሀል ዕረፍ ያን ጊዜም ዐጥንቶቹ ተነቃነቁ በፍቅር አንድነትም አረፈና በዚያ በዋሻው ውስጥ ተቀበረ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዕንባቆም_ነቢይ

በዚችም ቀን የስሙ ትርጓሜ አዋቂ የሆነ የዕንባቆም ነቢይ መታሰቢያው ነው። ይህም ቅዱስ በአንዲት ዕለት እህሉን ለሚያጭዱለት ምሳቸውን አዘጋጅቶ ተሸክሞ ሲሔድ መልአክ ተገልጾለት ይህን መብል በባቢሎን አገር በአንበሶች ጕድጓድ ውስጥ ላለ ለነቢዩ ዳንኤል ውሰድ አለው።

ዕንባቆምም ጌታዬ ሆይ ባቢሎንን አላየኋት ጉድጓዱንም አላውቀው አለው። የእግዚአብሔር መልአክም በራሱ ጠጉር ያዘው ምግቡን በእጁ እንደያዘ ወሰደውና ጉድጓዱ እንደተዘጋ አስገባው ምግቡንም ሰጥቶ መገበው ወዲያውኑ ዕንባቆምን ወደ ይሁዳ አገር መለሰው።

በአረጀና በሸመገለም ጊዜ የእስራኤል ልጆች ከተማረኩበት ተመልሰው ቤተ መቅደስን ሠሩ። ዕንባቆምም ኢየሩሳሌም ደርሶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ በታላቅ ደስታም ተቀበሉት ትንቢቱንም ሊሰሙ ወደርሱ ተሰበሰቡ አፉንም ከፍቶ በመንፈስ ቅዱስ እንዲህ አለ።

አቤቱ ድምፅህን ሰማሁ ሰምቼም ፈራሁ ሥራህንም አይቼ አደነቅሁ አለ። ስለ መድኃኒታችንም መውረድና በይሁዳ ክፍል በሆነች በቤተ ልሔም ስለመወለዱ ሲናገር የተመሰገነ እግዚአብሔር ግን ከፋራን ተራራ ከቴማን ከይሁዳ አውራጃ ይመጣል ብሎ እስከ መጨረሻው ተናገረ ከነቢያት መጻሕፍትም ጋራ ደመርዋት።

ከዚህ በኋላ ከእስራኤል ልጆች አንዲት ሴት ወደርሱ መጣች እያለቀሰችም እንዲህ አለችው። ሁለት ልጆች ነበሩኝ ጣዖት እንዲአመልኩ ፈለጉአቸው እምቢ በአሉ ጊዜም ገድለው በጐዳና ላይ ጣሉአቸው። ተገድለው ወደ አሉበትም አብሮዋት ሔደ ነፍሳቸውንም ይመልስላቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነው ልመናውንም ተቀበሎ በሕይወት አነሣቸው።

ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ ዘመዶቹን ጠራቸው። እንደሚሞትም ነገራቸውና አንዲት ሰዓት ያህል ወደላይ እየተመለከተ ተቀመጠ ። እነሆ እንደ ሰው ክንድ ያለች ታላቅ ክንድ የቤቱን ጣሪያ ሠንጥቃ ወረደች ወደ አፉም ተዘርግታ ነፍሱን ወሰደች ያን ጊዜም አረፈ።

በክርስቲያናዊ ንጉሥ በአንስጣስዮስ ዘመን እንዲህ ሆነ ገድሉን በአነበበ ጊዜ አድንቆ በግብጽ ደቡብ ቀርጣስ በሚባል ቦታ በስሙ ቤተ ክርስቲያን ተሠራለት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ኤጲስቆጶስ_ቅዱስ_ዲዮናስዮስ
#ጥቅምት_23

ጥቅምት ሃያ ሦስት በዚህች ቀን የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ዮሴፍ አረፈ፣ የከሀዲ ዱድያኖስ ንጉሥ ሚስት #ቅድስት_እለእስክንድርያ መታሰቢያዋ ነው፣ የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተተክለው በደብረ ሊባኖስ የተሾሙት #አቡነ_ኤልሳ ዕረፍታቸው ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ዮሴፍ_ሊቀ_ጳጳሳት

ጥቅምት ሃያ ሦስት በዚህች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ኀምሳ ሁለተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ አረፈ ። ይህም አባት ከመኑፍ አገር ከታላላቆች ተወላጆች ወገን ነው ወላጆቹም ብዙ ገንዘብ ያላቸው ነበሩ ታናሽም ሁኖ ሳለ አባትና እናቱ ትተውት ሲሞቱ ድኃ አደግ ሆነ አንድ እግዚአብሔርንም የሚወድ ሰው አሳደገው።

አድጎ በጎለመሰም ጊዜ የወላጆቹን ገንዘብ ሁሉንም ወስዶ ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወተ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጥቶ ከአንድ ፃድቅ ሽማግሌ ሰው አባት ዘንድ መነኰሰ በበጎ ገድል ሁሉ እየተጋደለ ኖረ ።

ዳግማዊ አባ ማርቆስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ የዚህን አባ ዮሴፍን በጎ ጠባዩንና የትሩፋቱን ዜና ሰምቶ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው በቤቱም አኖረው ።

ከብዙ ወራትም በኋላ አባ ዮሴፍ ሊቀ ጳጳሳቱን አባ ማርቆስን ወደ አስቄጥስ ገዳም እሔድ ዘንድ ተወኝ ብሎ ለመነው ያን ጊዜም ቅስና ሹሞ አሰናበተው ሊቀ ጳጳሳት አባ ስምዖንም እስከ አረፈ ድረስ በዚያ በእስቄጥስ ገዳም ኖረ ከዚህም በኋላ የግብጽ አገር ያለ ሊቀ ጳጳሳት ብዙ ወራት ኖረች ።

ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሳቱ መማለጃ ስለተቀበሉ ከአንድ ሚስቱ ከሞተችበትና መዓስብ ከሆነ ጸሐፊ ጋር ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተስማሙ እኩሌቶቹ ግን ተቃወሟቸው እንዲህም አሏቸው የአባቶቻችን ቀኖና መማለጃ የሚቀበለውን ሁሉ ወይም ስለ ክህነት ሹመት መማለጃ የሚሰጠውን ያወግዛል ። ይልቁንም ይህ ሰው ሚስት አግብቷል እንዴት ሊሾም ይችላል በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ የሚሾም ንጹሕ ድንግልም ነውና።

ይህንንም በአሏቸው ጊዜ ፈሩ ተመልሰውም ተስማሙ ለዚች ለከበረች ሹመት የሚሻለውን ይገልጽላቸው ዘንድ ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን በአንድ ምክር ሁነው ጸለዩ እግዚአብሔርም ሰምቷቸው ለዚች የከበረች ሹመት የሚሻል አባ ዮሴፍ እንደሆነ አሳሰባቸው።

ከዚህም በኋላ አባ ዮሴፍን ያመጡት ዘንድ ወደ አስቄጥስ ገዳም መልእክተኞችን ላኩ መልክተኞችም ይህን አባት ዮሴፍን የመረጥከው ከሆነ ምልክትን ትገልጥልን ዘንድ አቤቱ እንለምንሃለን የቤቱም ደጃፍ ክፍት ሁኖ ካገኘን ምልክት ይሁንልን ብለው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ።

በደረሱም ጊዜ አንዱን መነኰስ እየሸኘ የበዓቱም ደጃፍ ክፍት ሁኖ አባ ዮሴፍን አገኙት በአያቸውም ጊዜ መንፈሳዊ ሰላምታ በመስጠት እጅ ነሣቸውና በደስታ ተቀብሎ ወደ በዓቱ አስገባቸው በዚያንም ጊዜ ለአባ ዮሴፍ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ይዘው አሠሩት ። እርሱ ግን እኔ ብዙ ኃጢአትን ሠርቻለሁና ይህ የከበረ ሹመት አይገባኝም እያለ ይጮህ ነበር እነርሱም ወደ እስክንድርያ ከተማ ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እንጂ ምንም ምክንያት አልተቀበሉትም።

በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም በተቀመጠ ጊዜ ለአብያተ ክርስቲያን እጅግ የሚያስብ ሆነ ለርሱ የሆነውን የግብሩን ገቢ ወስዶ ምድሮችን በመግዛት ለአብያተ ክርስተያን መተዳደሪያ ሊሆኑ ጉልቶች ያደርጋቸው ነበርና።

አዘውትሮም ሕዝቡን የሚያስተምራቸው ሆነ በምንም በምን ለየአንዳንዱ ቸለል አይልም ነገር ግን ሰይጣን ስለቀናበት ያለ ኀዘን አልተወውም ። ይህም እንዲህ ነው በምስር አገር የተሾሙ ሁለት ኤጲስቆጶሳት በሕዝቡ ላይ ክፉ ነገር በማድረግ በማይገባ ሥራ አስጨነቋቸው እርሱም በርኅራኄና በፍቅር መንጎቻቸውን እንዲጠብቁ አዘዛቸው ለመናቸውም እነርሱ ግን ሰምተው ከክፋታቸው አልተመለሱም።

በሕዝቡም ላይ ችግርን በአበዙ ጊዜ ሕዝቡ ሁሉም በጠቅላላ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ መጡ በፊቱም እንዲህ ብለው ጮኹ እሊህን ኤጲስቆጶሳት ከላያችን ካላነሣሃቸው እኛ ወደሌላ ሃይማኖት እንገባለን አባ ዮሴፍም በመካከላቸው ሰላምን ለማድረግ ብዙ ትግልን ታገለ ግን አልተቻለውም።

ከዚህም በኋላ በግብጽ አገር ያሉትን ኤጲስቆጶሳት ለጉባኤ ሰበሰባቸውና ስለ እሊህ ሁለት ኤጲስቆጶሳት ነገራቸው አሁንም ከመንጋዎቻቸው ጋር ሊአስታርቅ ሽቶ እሊህን ኤጲስቆጶሳት ወደ ጉባኤው አስቀረባቸው እነርሱ ግን የጉባኤውንም የእርሱንም ቃል አልተቀበሉም ስለዚህም ያ ጉባኤ ከሹመታቸው ሻራቸው።

እነርሱም ወደ ግብጽ ንጉሥ ሒደው በሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ ላይ በሐሰት ነገር ሠሩበት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍንም ያመጡት ዘንድ ንጉሡ ወንድሙን ከጭፍራ ጋር ላከው። የንጉሡም ወንድም ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ በደረሰ ጊዜ ተበሳጨ ሊገለውም ወዶ ሰይፉን መዞ ሊቀ ጳጳሳቱን ሊመታው ሰነዘረበት ግን እጁ ወደ ሌላ አዘንብሎ ምሰሶ መትቶ ሰይፉ ተሰበረ እጅግም ተቆጥቶ ሌላ ሰይፍን መዝዞ በመላ ኃይሉ መታው ያን ጊዜም ሰይፉ ከአንገቱ ወደ ወገቡ ተመልሶ ልብሱንና ቅናቱን ብቻ ቆረጠ የንጉሡም ወንድም ከክፋት ንጹሕ እንደሆነ ስለዚህም አምላካዊት ኃይል እንደምትጠብቀው አሰበ አስተዋለም።

ወደ ንጉሡም በክብር አደረሰው ወንድሙ ለሆነ ንጉሥም በእርሱ በሊቀ ጳጳሳቱ ላይ የሆነውን ሁሉ ነገረው ንጉሡም ፈራው አከበረውም ከዚህም በኋላ ስለከሰሱት ስለ ሁለቱ ኤጲስቆጶሳት ጠየቀው እርሱም ስለ ክፉ ሥራቸው በጉባኤ እንደተሻሩ እውነቱን ለንጉሡ አስረዳው ያን ጊዜም ሐሰተኞች እንደሆኑ ንጉሥ አወቀ ይገድሏቸውም ዘንድ አዘዘ።

ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍም ንጉሡን እንዲህ ብሎ ማለደው ጌታችን በክፉ ፈንታ በጎ እንድናደርግ እኛን አዞናልና ስለ እግዚአብሔር ብለህ እሊህን ማራቸው እንጂ አትግደላቸው ንጉሡም ስለ የዋህነቱ አደነቀ ልመናውንም ተቀብሎ ማረለት።

ከዚህም በኋላ በሹማምንቱና በኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ ላይ የፈለገውን ያደረግ ዘንድ ቢፈልግ እንዲሾም ወይም እንዲሽር የሚቃወመው እንዳይኖር ደብዳቤ በመጻፍ ሥልጣንን ሰጠው።

በዚህም አባት ዘመን የኢትዮጵያ ንጉሥ ወደዚህ አባት ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ እንዲህ ብሎ መልእክትን ላከ ለወንጌላዊ ማርቆስ መንበርና በላዩ ለመቀመጥ ለተገባው ቅድስናህ እጅ እነሣለሁ በእኔና በመንግሥቴ ላይ በመላው ወገኖቼ በኢትዮጵያ ሰዎች ላይ ይቅርታ እንድታደርግና አባታችንን አባ ዮሐንስን እንድትልክልን እለምንሃለሁ ከሀገራችን ሰዎች ከእውነት መንገድ የወጡና የሳቱ ጳጳሳችንን አባ ዮሐንስን እኔ ሳልኖርና ሳላውቅ አባረውታልና ስለዚህም በሀገራችን ቸነፈርና ድርቅ ሁኖ ከሰዎችም ከእንስሶችም ብዙዎች አለቁ።

አሁንም አባቴ ሆይ ስንፍናችንን ይቅር በል መሐሪና ይቅር ባይ ወደ ሆነ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልድልን ዘንድ በከበረች ጸሎቱም ከዚህ መከራ እንድን ዘንድ አባታችንን አባ ዮሐንስን ላክልን።

አባቴ ሆይ የተባረረበትን ምክንያት እኔ አስረዳሃለሁ እኔ ልጅህ ከአባቴ ከጳጳስ አባ ዮሐንስ ቡራኬ ተቀብዬ እርሱ ከሠራዊቴ ጋር በፍቅር አሰናብቶኝ ወደ ጦር ሜዳ ሔድሁ ከጦር ሜዳም በተመለስኩ ጊዜ አባቴን አባ ዮሐንስ ጳጳሱን አጣሁት ስለርሱም በጠየቅሁ ጊዜ በቀድሞ ዘመን ዮሐንስ አፈ ወርቅን ንግሥት አውዶክስያ እንዳሳደደችው በክፉዎች ሰዎች ምክር ንግሥቲቱ ሚስቴ ማሳደዷን የቀኖናውንም ትእዛዝ በመተላለፍ በፈቃዳቸው ሌላ ጳጳስ እንደሾሙ ነገሩኝ።
እርሱ አባ ዮሐንስም ከኢትዮጵያ በአሳደዱት ጊዜ ወደ አስቄጥስ በመሔድ አስቀድሞ በመነኰሰባት በአባ ሙሴ ጸሊም ገዳም በዚያ ተቀመጠ። የኢትዮጵያ ንጉሥ መልእክትም ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ በደረሰች ጊዜ አነበባት ስለ ኢትዮጵያ ንጉሥ የሃይማኖት ጽናት እጅግ ደስ አለው ፈጥኖም ወደ አስቄጥስ ገዳም መልእክተኞችን ልኮ አባ ዮሐንስን ወደርሱ አስመጥቶ አረጋጋው አጽናናው ከዚያም በኋላ ከደጋጎች ሰዎች ጋር ወደ ኢትዮጵያ አገር ላከው።

አባ ዮሐንስም ወደ ኢትዮጵያ አገር በደረሰ ጊዜ ቸነፈር ተወገደ ዝናብም ዘነበ ንጉሡና መላው የኢትዮጵያ ሰዎች ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑት። ይህም ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ መናፍቃንን የሚገሥጻቸው ሆነ ሕዝቡንም ከአባቶቻቸው በተቀበሏት በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አስተማራቸው ከቅዱሳት መጻሕፍትም ለእነርሱም ሥውር የሆነውን ተርጉሞ ያስረዳቸዋል ያስገነዝባቸዋልም በትምህርቱና በጸሎቱም እንዲህ ጠበቃቸው ጌታችንም በእጆቹ ብዙዎች ተአምራትን አደረገ ያማረች ገድሉንም ፈጽሞ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም በፍቅር አረፈ ። መላ የሕይወቱም ዘመን ሰባ ስምንት ነው ከምንኲስና በፊት ሃያ አመት በምንኲስና ተጋድሎ ሠላሳ ዘጠኝ ዓመት በሊቀ ጵጵስና ሹመት ዓሥራ ዘጠኝ ዓመት ኖረ ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_እለእስክንድርያ_ሰማዕት

ዳግመኛም በዚህች ቀን የከሀዲ ዱድያኖስ ንጉሥ ሚስት የከበረች እለእስክንድርያ መታሰቢያዋ ነው። ይኸውም ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ መስሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘበተበት ጊዜ ዝንጉዕ ዱድያኖስም ዕውነት መስሎት ራሱን ሊስም ተነሣ። ቅዱሱ ግን ለአማልክት ከመሠዋት አስቀድሞ አይሆንም ብሎ እንዳይስመው ከለከለው።

ከዚህ በኋላም ዱድያኖስ ወደ ቤተ መንግሥቱ አዳራሽ ቅዱስ ጊዮርጊስን አስገባው በዚያም በንግሥት እለእስክንድርያ ፊት የዳዊትን መዝሙር በማንበብ ጸለየ። በሰማችም ጊዜ ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው ያን ጊዜም ተረጐመላት የክብር ባለቤት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነቱን ገለጠላት ትምህርቱም በልቡዋ አድሮ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነች።

ከዚህም በኋላ ሲነጋ ለአማልክት ወደሚሠዋበት ቅዱስ ጊዮርጊስን ወሰዱት እርሱም የረከሱ አማልክትን ትውጣቸው ዘንድ ምድርን አዘዛት ምድርም ዋጠቻቸው። ንጉሥ ዱድያኖስም አፈረ እየአዘነና እየተከዘ ወደ ሚስቱ ወደ እለእስክንድርያ ዘንድ ገባ። እርሷም ክርስቲያኖችን አትጣላቸው አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነው አላልኩህምን አለችው። ይህንንም ሰምቶ በእርሷ ላይ ተቆጣ ያሠቃዩዋት ዘንድ ጡቶቿንም ሠንጥቀው ይሰቅሏት ዘንድ አዘዘ። የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዲዮናስዮስ_ኤጲስቆጶስ

በዚችም ቀን የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ ዲዮናስዮስ በዐላውያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን በሰማዕትነት አረፈ ይህንንም ቅዱስ በያዙት ጊዜ ብዙ ሥቃይን አሠቃዩት ማሠቃየቱንም በሰልቹ ጊዜ ራሱን በሰይፍ አስቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ጻድቁ_አቡነ_ኤልሳ

ዳግመኛም በዚህች ቀን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተተክለው በደብረ ሊባኖስ የተሾሙት አቡነ ኤልሳ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ጻድቁ ሀገራቸው ሸዋ ነው፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመን የነበሩ ሲሆን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥለው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በእጨጌነት የተሾሙ የመጀመሪያ ዕጨጌ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከማረፋቸው በፊት ‹‹በእኔ ወንበር ኤልሳዕ ይሾም ነገር ግን ዘመኑ ትንሽ ስለሆነ ከእርሱ ቀጥሎ ፊሊጶስን ትሾማላችሁ›› ብለው ለቅዱሳን ተከታይ ሐዋርያቶቻቸው ተናግረው ነበር፡፡

በዚህም መሠረት አቡነ ኤልሳዕ ተሹመው ብዙም ሳይቆዩ አንድ ዲያቆን ሞተና ሊቀብሩት ሲወስዱት በመንገድ ላይ ሳለ ድንገት ከሞት ተነሥቶ ‹‹አባቴ ተክለ ሃይማኖት ኤልሳዕ አሁን ወደኔ ስለሚመጣ ፊሊጶስን ሹሙት ብለህ ተናገር ብለውኝ ነው›› ብሎ ከተናገረ በኋላ ተመልሶ ዐርፎ ተቀበረ፡፡ አቡነ ኤልሳዕም ወዲያው ዐርፈው አቡነ ፊሊጶስ 3ኛ ሆነው ተሾሙ፡፡ አቡነ ኤልሳዕ ከተጋድሎአቸው ብዛት የተነሣ በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ጎናቸውን አሳርፈው ተኝተው አያውቁም ነበር፡፡ ነገር ግን ማረፍ ሲኖርባቸው በወንበር ላይ ተደግፈው ትንሽ ብቻ ያርፉ ነበር፡፡ አቡነ ኤልሳዕ በሞት ያረፉትም እንደልማዳቸው ጎናቸውን ሳያሳርፉ በወንበር ላይ እንደተደገፉ ነበር፡፡ አባታችን ስለዚህም ጉዳይ ሲናገሩ እንዲህ ይሉ ነበር፡- ‹‹ነፍስ ትጋትን ትወዳለች፣ ሥጋ ግን ይደክማል፡፡ ለመነኮሳትና ለእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ መኝታ ማብዛት አይገባቸውም፡፡ መኝታ ማብዛት ሕልምን ያመጣል፣ ነፍስን ይጎዳል፣ ሰውነትንም ያደክማል፡፡››

አቡነ ኤልሳዕ በዘመናቸው ወንጌልን በማስተማርና ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቁ ነበር፡፡ እንደ ነቢዩ ኤልሳዕ እሳቸውም ሙት አስነሥተዋል፡፡ ባሕር እየከፈሉ ቀደ መዛሙርቶቻቸውን ያሻግሩ ነበር፡፡ በጸሎታቸው የዠማን ወንዝም ለሁለት የከፈሉ ታላቅ አባት ናቸው፡፡

ለእግዚአብርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥቅምት እና #ከገድላት_አንደበት)
#መጋቢት_13

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም

መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን የታላቁ አባት #የቅዱስ_መቃርስ እና #የቅዱስ_መቃርዮስ_ዘእስክንድርያ የስደታቸውን መታሰቢያ ነው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ አረፈ፣ የከበሩ #ቅዱሳን_አርባ_ሐራ ሰማይ በሰማዕትነት አረፉ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ታላቁ_ቅዱስ_መቃርስ እና #ቅዱስ_መቃርዮስ_እስክንድርያዊ

መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን ኦርቶዶክሳውያን ሰዎች የታላቁ አባት የመቃርስን የእስክንድርያው የመቃርዮስን የስደታቸውን መታሰቢያ ያከብራሉ። ይህም በሮም መንግሥት ከወንድሙ ከዋልጥስ በኋላ በነገሠ ጊዜ በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ ስደትንና መከራን አመጣ።የረከሰ የማኒንና የከሀዲው አርዮስን እምነት ስለሚከተል ነው ለእስክንድርያም ሉክዮስን ሊቀ ጳጳሳት አድርጎ ሹሞ ሐዋርያዊ አትናቴዎስን አሳደደው።

ይህም ከሀዲ ሉክዮስ ታላቁን አባት አባ መቃሪን እስክንድርያዊውን አባት መቃርዮስን ፈልጎ በንጉሥ ትእዛዝ ወደርሱ ከገዳማቸው አስመጣቸው። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ለያይቶ በለሰለሰ አንደበት በመሸንገል ወደረከሰ የአርዮስ ሃይማኖት ይገቡ ዘንድ አግባባቸው። እነርሱ ግን ወደ ነገሩ አልተመለሱም ሳይፈሩትም መለሱለት በቅንነትና በትዕግሥትም መከሩት ገሠጹት እንጂ የአርዮስንም ሃይማኖት ብላሽነት የባህሉንም አስከፊነት ከቅዱሳት መጻሕፍት ለይተው አስረዱት።

በዚያን ጊዜም ተቆጣ ከቊስጥንጥንያ መካከል ወደምትርቅ ደሴት አጋዛቸው ከእስክንድርያም መርከብን የሚጠብቋቸውንም ወታደሮችን በእነርሱ ላይ በሚያደርጉት ሥራ ሁሉ አጫንቀው በብረት አሥረው ይወስዱአቸው ዘንድ አዘጋጁ። ወደዚች ደሴት በደረሱ ጊዜ በደሴቱ ንጉሥ ፊት አቆሙአቸው ንጉሡም ሰይጣንን የሚያመልክ የከፋ ሰው ነበር የደሴቱም ሰዎች አምላክ ነው ብለው እስቲ አምልኩትና እስቲሰግዱለት ድረስ በሥራዩ አስቷቸው ነበር።

እሊህ አባቶቻችንም ከስሕተቱ እንዲመለስ አስተማሩት ለመኑትም አልሰማቸውም ከብዙ ሥቃይ ጋር በወህኒ ቤት ዘጋባቸው እንጂ በጽኑዕ ሥቃይም አሠቃያቸው ጌታችንም ተገልጦ የሚያጸናቸውና የሚያስታግሣቸው ሆነላቸው። የክብር ባለቤት ጌታችንም ጽድቃቸውንና ትሩፋታቸውን ሊገልጥ በወደደ ጊዜ የንጉሡን ልጅ ሰይጣን ያዛት። አባትና እናቷም በታላቅ ኀዘን ላይ እስቲሆኑ አብዝቶ አሠቃያት በከተማ ውስጥም ሰይጣናት ተገልጠው መቃርስና ባልንጀራው ሆይ እኛ ከእናንተ እናንተ ከኛ ምን አላችሁ ከአገራችሁ ያሰደዳችሁን እያሉ ተገልጠው ይጮኹ ጀመር።በንጉሡ ልጅ ያደረውም ሰይጣን ንጉሥ ሆይ መቃርስና ባልንጀራው ካልመጡ ከልጅህ ላይ አልወጣም ብሎ ጮኸ ንጉሡና አብረውት ያሉ አደነቁ ወደ ንጉሡም ቅዱሳንን አመጡአቸው።

እሊህ ቅዱሳን መቃርስና ባልንጀራው ወደ ንጉሥ በደረሱ ጊዜ በንጉሡ ልጅ ያደረ ሰይጣን እንዳያሠቃዩት ለመነ። ንጉሡና አብረውት ያሉትም ስለ ሥራቸው ቅዱሳንን መረመሩአቸው፡፡ እነርሱም የሆነውን ሁሉ ነገሩአቸው ስለ ንጉሡም ልጅ ያድኑዋት ዘንድ ለመኑዋቸው። እነርሱም ንጉሡን ገሠጹት እንዲህም አሉት አንተ ሰው ስትሆን ለምን ራስህን አምላክ ታደርጋለህ ዓለምን የፈጠረ አምላክ ከሆንክ ራስህንና ልጅህን ማዳን ይገባህ ነበር። ያን ጊዜም ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ጸልየው ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ስለ ክፉ ሥራቸው ንጉሡንና የዚያችን ደሴት ሰዎች ዘለፋቸው።

ንጉሡና በዚያ የተሰበሰቡት ይህን አይተው በእሊህ ቅዱሳን አምላክ እናምናለን ከእሊህ ቅዱሳን አምላክ ከእግዚአብሔር በቀር በሰማይና በምድር ሌላ አምላክ እንደሌለ ተረድተናልና እያሉ ጮኹ። የከበሩ አባቶቻችንም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን አሰተማሩአቸው እነርሱም በሽተኞቻቸውን ሁሉ ሰበሰቡ አባቶቻችንም በዘይት ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ቀብተው በሽተኞችን ሁሉ አጋንንት ያደሩባቸውንም ሁሉንም አዳኑአቸው እንዲሁም እያደረጉ እያስተማሩዋቸውም ብዙ ቀን ኖሩ።

ከዚህም በኋላ የሀገሩን ምኵራብ አስፈርሰው ቦታውን አጸዱ አነፁ ቦታውም እጅግ ስፋት ያለው መልካም ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሳነፁ ንጉሡም ስፍር ቁጥር የሌለው ወርቅና ብር የሐር ልብሶችንም ለእግዚአብሔር መቅደስ ለሚአሻውም ሁሉ አመጣ። የከበሩ አባቶቻችንም ጥበብ ያላቸው አንጣሪዎችን ሚዛኑ ለየአንዳንዱ ዘጠኝ ልጥር የሚሆን አሥራ ሁለት ጻህሎችን ሠርተው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንና የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ሥዕል የሁለቱንም የመላእክት አለቆች የሚካኤልንና የገብርኤልን ሥዕል በውስጡ እንዲሥሉ ደግሞ አሥራ ሁለት መንበሮችን ለመሠዊያ የሚፈለገውንም ሁሉ አሥራ ሁለት ጽዋዎችና አሥራ ሁለት ዕርፈ መስቀልም እያንዳንዱ ሦስት ሦስት ልጥር የሆኑ ሃያ አራት መስቀሎችን እንዲሠሩ ሦስቱንም የመቅደስ ግድግዳ እንዲሥሉ አዘዙ።

የቤተ ክርስቲያኒቱ የሕንፃዋ ሥራ ተፈጸመ። የተረፈውንም ገንዘብ ለድኆችና ለችግረኞች በተኑ። ጌታችን የተጠመቀባት ጥር ዐሥራ አንድ ቀን በሆነች ጊዜ ወደ ባሕር አጠገብ እንዲወርዱና እንዲሰበሰቡ የአገሩን ሰዎች አዘዙዋቸው። ከእስክንድርያም በተሰደዱ ጊዜ እግረ መንገዳቸውን የያዙትን የከበረ ሜሮንን አመጡ። ይህም ከሐዋርያዊ አትናቴዎስ ጊዜ ጀምሮ የተጠበቀ ሉክዮስም ያላገኘው ጌታችንም በዘመናት ሁሉ የጠበቀው ጥፋት ያላገኘው ነው።ይህ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ሆኖአልና።

በዚያንም ጊዜ አባት መቃሪ በከበረ ሜሮን በጥልቁ ባሕር ላይ ባረከ ባሕሩም ከእሳት ኃይል የተነሣ በድስት እንደሚያፈሉት ውኃ የሚፈላ ሆነ ዘይቱና ሜሮኑም በውኃው ላይ ተንሳፈው እንደሚያበሩ ከዋክብት ሆኑ ከእርሳቸውም እንደ ፀሐይ የሆነ ታላቅ ብርሃን ታየ። ንጉሡና የተሰበሰቡት ሕዝብ አይተው ፈሩ። የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠ። አጥማቂው ዮሐንስና ቅዱሳን መላእክትም ውኃው በመከብርበትና በሚለወጥበት ጊዜ ተገለጡ። ሕዝቡም ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ ያንጊዜ ከሽቱ ሁሉ መዓዛው የሚጣፍጥ ሽታ ሸተተ።

በዚያን ጊዜም የከበሩ አባቶቻችን ይህን አይተው በምድር ላይ ወድቀው ሰገዱ በስግደታቸው እዚያው ዘገዩ። አባት መቃርስም ሰግዶ ሳለ ጌታችንን እንዲህ ሲል ለመነው። ጌታዬ እለምንሃለሁ ቸርነትህ ትድረሰኝ የዚች ታቦትና ንዋየ ቅድሳቷ ቡራኬ በአምላካዊት እጅህ እንዲሆን አለው።ጌታም እሺ በጎ ብሎ ሜሮኑን ከአባ መቃሪ እጅ ተቀብሎ ታቦቱንና ንዋየ ቅዱሳቱን አከበረ።

ከዚያም በኋላ አባት መቃርስን ሦስቱን ደርብ ትባርክ ዘንድ እኔ አዝሃለሁ እኔም ካንተ ጋራ አለሁ ይህንንም ንጹሕና ክቡር የሆነ አገልግሎት ባልንጀራህ አብሮህ ያገልግል። በመጀመሪያም የመካከለኛውን ደርብ በሥጋ በወለደችኝ በድንግል ማርያም ስም ለይተህ አክብር ደግሞ በቀኝ በኩል ያለውን በከበረ መስቀል ስም ለይተህ አክብር በግራ በኩል ያለውን ደርብ በስምህ ለይተህ አክብር በከሀዲ ሉክዮስ እጅ ስለ ስሜ በዚች ደሴት ውስጥ ደምህን አፍሰሃልና አለው።

እሊህም የተባረኩ አባቶች ጌታችን እንደ አዘዘ ሊሠሩ በጀመሩ ጊዜ ንጉሥ ዳዊት በመዝሙር ሊያመሰግን ጀመረ መላእክትም በመልካም ቃላት በቋንቋቸው ያመሰግኑ ጀመር ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
ዳግመኛም ጌታችን አባ መቃርስን መሥዋዕቱን ተሸክሞ በመሠዊያ ላይ ይቀድስ ዘንድ አዘዘው አባ መቃርስም ጌታችንን የሐዋርያት አለቃ አባታችን ጴጥሮስን እንዲቀድስ እዘዘው ይኽቺ ዕለት በከበረ ስምህ በዚች ደሴት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መሥዋዕት የተሠዋባት ናትና አለው።
ጌታም ላንተ ይገባል አንተ በዚች ደሴት ዘርተሃልና እኔም አሳደግሁ በደቀ መዝ ሙሬ በጳውሎስ አድሬ የተናገርኩትን አላስተዋልክምን የዘራና የደከመ እርሱ አስቀድሞ ፍሬውን ይብላ ያልሁትን አለው።

አባት መቃርስም የቅዳሴውን ሥርዓት ከጌታ ተባርኮ በጀመረ ጊዜ ከእስክንድርያዊ መቃርዮስ ጋራ ይራዱት ዘንድ ጴጥሮስ በቀኙ ማርቆስ በግራው ሁሉም ሐዋርያት በዙሪያው ቆሙ።ጳውሎስና ዮሐንስም የየራሳቸውን መልእክት አነበቡ ሉቃስም የሐዋርያትን ሥራ አነበበ ዳዊትም መዝሙሩን ዘመረ ለስም አጠራሩ ምስጋና ገንዘቡ የሆነ ጌታችንም ወንጌሉን አነበበ።በነጭ ርግብ አምሳልም መንፈስ ቅዱስ በኅብስቱና በውይኑ ላይ ወርዶ የጌታችን ክርስቶስን ሥጋና ደም ወደመሆን ለወጣቸው።

አባት መቃርስም ወደ ጽዋው ጣቱን በአስገባ ጊዜ ጣቱ በደም ታለለ።የመላእክት ሠራዊት ሁሉ በመሠዊያው ላይ ክንፋቸውን ዘርግተው ይራዱት ነበር ሚካኤልና ገብርኤልም መጡ የመላእክት አንድነት ሁሉም በእርሱ በአባት መቃርስ አምሳል ሁነው እየተራዱት ለሕዝቡ የከበረ ሥጋውንና ደሙን አቀበለ። ከቁርባን ሥርዓት ፍጻሜ በኃላ ጌታችን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃርስ አምሳል ሁኖ ወንጌል በሚነበብበት አትሮንስ ላይ ተቀመጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ ይበራ ነበር ለሕዝቡም ቡራኬ ሰጥቶ ወደ መሠዊያው ተመለሰ ሐዋርያትም ከርሱጋራ።

ዳግመኛም ከሰባት ቀኖች በኃላ አባታችን መቃርስ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሹመት ማዕርግ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጦ በእኔ ዘንድ ለዚህ ታላቅ ክብር የምትገባ አንተ ነህና አለው።

ሽማግሌውም ሰምቶ አለቀሰ በእግዚአብሔርም ፊት ሰገደ አቤቱ በሲሐት ገዳም ወዳሉ መነኰሳት ልጆችህ ጊዜው ሲደርስ እመልስሃለሁ ከዚህ ከሥጋህ ሳትለይ ያልከኝን አስብ።ይህ ካልሆነ መቃራ የምንኲስናውን ሥራ ትቶ ፓትርያርክ ሆነ ይላሉ አለ። ጌታችንም የመረጥኩህ መቃርስ ሆይ እኔ የልብህን ፍላጎት ሁሉ እፍጽምልሃለሁ ግን ፓትርያርክ ትሾም ዘንድ ከልጆችህ የመረጥከውን አንድ አቅርብ አለው። ቅዱስ መቃርስም አቤቱ አንተ ልብ ያሰበውን የምታውቅ ነህ እኔ ግን ወደዚህ አንጥረኛ ሽማግሌ ሰው ተመለከትኩ። እርሱ በቀናች ሃይማኖት የጸና ከሴቶችም ጋር ግንኙነት የማያውቅ ነው አለው ጌታችንም አንተ እንዳልክ ደግ ነው አለ። ቅዱስ መቃርስም ያንን አንጠረኛ ጠርቶ ወደ ታቦተ ሕጉ አቀረበው ያን ጊዜም ወንጌላዊው ማርቆስ መጣ እጁንም በአንጠረኛው ራስ ላይ ጭኖ ዲቁና ሾመው። ደግሞ ቅስና ሾመው ከዚያም የሊቀ ጵጵስና ሹመት እስከ ሚፈጽም በየመዐርጉ ሾመው ስሙንም ዮሐንስ አለው የሰማይ ሠራዊትም ሁሉም የወንጌላዊ ማርቆስ አዲስ ተክል የሆነ ለመቃርስ ልጅ ለዮሐንስ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሦስት ጊዜ ጮኹ በዚያ ያሉ ሕዝብም እሊህን ቃሎች ይሰሙ ነበር።

ጌታችንም የሊቀ ጳጳሳት የዮሐንስን ዓይነ ልቡናውን ገልጦለት በሚቻለው መጠን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አየው።ብዙ ቃላትንም ተናገረ ደግሞ ረቂቃን በሆኑ በሰማይ ሠራዊት ቤተ መቅደሱ ተመልቶ አየ የከበሩ ነቢያትና ሐዋርያትም በዚያ አሉ።

ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቁ አባ መቃራንና የእስክንድርያውን አባ መቃራን ጠራቸው እንዲህም አላቸው በምድር ሳሉ መታሰቢያችሁን የሚያደርጉ ሰዎች የተመሰገኑ ናቸው የዘላለም ሕይወትን ይወርሳሉና በራሴ እምላለሁ ስለ ስሜ የተቀበላችሁትን መከራ በትጋት የሚአስበውና የሚጽፈው የሚሰማው ሁሉ ያመሰግነኝ ዘንድ በቤተ ክርስቲያን የሚያነበው እኔ በጎ ነገርን ሁሉ እሰጠዋለሁ። ከበጎ ነገርም ምንም አላሳጣውም ከመከራውም ሁሉ አድነዋለሁ ኃጢአቱንም ሁሉ አስተሠርይለታለሁ። ከዚህ ዓለምም በሚለይለት ጊዜ ነፍሱን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ይወስዱ ዘንድ እናንተ ወደም ታስቡትም መንግሥቴ ሊአስገቡት የምሕረት መላእክትን እልካለሁ።

በገዳም ወይም በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ወይም በአገር ውስጥ ይህ ዜናችሁ በሚነበብበት እኔ አድራለሁ በረከቴንና ሰላሜንም እስከ ዓለም ፍጻሜ በውስጥዋ አደርጋለሁ። ለዚህ ለስደታችሁ ዜና ተቃራኒ የሚሆን ባልተወለደ በተሻለው ነበር። በእውነት እነግራችኋላሁ በሰው ፊት እንደአመናችሁብኝ በሰማያት በአለው አባቴ ፊትና በከበሩ መላእክቶቼ ፊት አምንባችኋለሁ። አሁን ግን ወደ ሀገራችሁ የምትመለሱበት ጊዜ ደረሰ ይህንንም ብሎ ሰላምታ ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ በክብር ዐረገ።

ከዚህ በኋላ ሕዝቡን ሁሉ ንጉሡንም ሰበሰቧቸው ወደ አገራቸውም እንደሚመለሱ ነገሩአቸው የክርስቶስንም ሕጉን ሁሉ እንዲጠብቁ ለሊቀ ጳጳሳቱ ዮሐንስም እንዲታዘዙ አዘዙአቸው።ከቀናች ሃይማኖት ወደ ቀኝም ቢሆን ወደ ግራም ፈቀቅ እንዳይሉ በብዙ አማፀኑአቸው አስጠነቀቋቸውም። ሕዝቡም ሰምተው ደነገጡ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ ቅዱሳን አባቶቻችንም ከእሳቸው ጋራ በአንድነት አለቀሱ ከእዚህም በኋላ እየአንዳንዳቸውን ባረኳቸውና ተሰናበቷቸው።

ያን ጊዜም ከኪሩቤል ወገን የሆነ መልአክ መጣ አውጥቶም በክንፎቹ ተሸከማቸው ወደ እስክንድርያም አድርሶ በሊቀ ጳጳሳቱ ደጅ እሑድ ጥዋት አወረዳቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስም ሰምቶ እጅግ ደስ አለው።ሁለተኛም በአያቸው ጊዜ አለቀሰ ሰገደላቸውም እነርሱም ሰገዱለት እርስ በርሳቸውም እጅ ተነሣሥተው ሰላምታ ተለዋወጡ። ጤንነታቸውንም ተነጋገሩ ደግሞም ልዩ የነበሩ የአሕዛብን ወደ እግዚአብሔር ስለመመለሳቸውና ስለ ተደረጉት ድንቆች ተአምራት ነገሩአቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስና ይህን የሰሙ ሁሉም ሕዝብ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት አባቶቻቸንም በዚያ ስምንት ቀን ተቀመጡ።

ከዚህም በኋላ ያ መልአክ ተገልጦ በክንፎቹ ደግሞ ተሸከማቸው ወደ ደብረ ሲሐትም አደረሳቸው አንዱ ኪሩብም ከአየር ሁኖ የአባት መቃርስ ልጆች ሆይ አባታችሁ የመንፈስ ቅዱስን ፍሬዎች ተሸክሞ ከስደት ተመልሶ መጥቷልና ወጥታችሁ ተቀበሉ እያለ ጮኸ፡፡ ይህንንም በሰሙ ጊዜ ከታላላቆች እስከ ታናናሾች ወጡ ቁጥራቸውም አምሳ ሺህ መነኰሳት ሆኑ። ከውስጣቸውም በዚያን ጊዜ አባ ዮሐንስ ሐፂርና አባ ብሶይ አሉ የደረሰባቸውንም ሥቃይ በነገራቸው ጊዜ እጆቹንና እግሮቹን እየሳሙ መሪር ዕንባ አለቀሱ። ደግሞ ፊቱን ስለአዩ ደስ አላቸው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባረካቸው።

የክርስቶስ ወገን የሆናችሁ በዓለሙ ሁሉ የምትገኙ ምእመናን ሆይ በዘመናት ሁሉ በዓል እያደረጋችኋት በዚች ዕለት ደስ ሊላችሁ ይገባል።ይህም ለአምላካችን ክርስቶስ ስለ ስሙ ደማቸውን እንዳፈሰሱ እንደ ጴጥሮስና እንደ ጳውሎስ መታሰቢያ ለእሊህ ታጋዮች አባቶች ለመከራቸው መታሰቢያ እንዲሆን።

እሊህም ታላቁ አባ መቃርስና ባልንጀራው የእስክንድርያው አባ መቃርስ ናቸው በዚች በመጋቢት ወር በዐሥራ ሦስተኛ ቀን ሉክዮስ ከእስክንድርያ አስቀድመን ወደ አወሳናት ደሴት አጋዛቸው ደግሞ በዚሁ ቀን ተመልሰው ወደ እስክንድርያ ደረሱ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዲዮናስዮስ
#ጥቅምት_23

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ሃያ ሦስት በዚህች ቀን የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ዮሴፍ አረፈ፣ የከሀዲ ዱድያኖስ ንጉሥ ሚስት #ቅድስት_እለእስክንድርያ መታሰቢያዋ ነው፣ የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተተክለው በደብረ ሊባኖስ የተሾሙት #አቡነ_ኤልሳ ዕረፍታቸው ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ዮሴፍ_ሊቀ_ጳጳሳት

ጥቅምት ሃያ ሦስት በዚህች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ኀምሳ ሁለተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ አረፈ ። ይህም አባት ከመኑፍ አገር ከታላላቆች ተወላጆች ወገን ነው ወላጆቹም ብዙ ገንዘብ ያላቸው ነበሩ ታናሽም ሁኖ ሳለ አባትና እናቱ ትተውት ሲሞቱ ድኃ አደግ ሆነ አንድ እግዚአብሔርንም የሚወድ ሰው አሳደገው።

አድጎ በጎለመሰም ጊዜ የወላጆቹን ገንዘብ ሁሉንም ወስዶ ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወተ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጥቶ ከአንድ ፃድቅ ሽማግሌ ሰው አባት ዘንድ መነኰሰ በበጎ ገድል ሁሉ እየተጋደለ ኖረ ።

ዳግማዊ አባ ማርቆስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ የዚህን አባ ዮሴፍን በጎ ጠባዩንና የትሩፋቱን ዜና ሰምቶ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው በቤቱም አኖረው ።

ከብዙ ወራትም በኋላ አባ ዮሴፍ ሊቀ ጳጳሳቱን አባ ማርቆስን ወደ አስቄጥስ ገዳም እሔድ ዘንድ ተወኝ ብሎ ለመነው ያን ጊዜም ቅስና ሹሞ አሰናበተው ሊቀ ጳጳሳት አባ ስምዖንም እስከ አረፈ ድረስ በዚያ በእስቄጥስ ገዳም ኖረ ከዚህም በኋላ የግብጽ አገር ያለ ሊቀ ጳጳሳት ብዙ ወራት ኖረች ።

ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሳቱ መማለጃ ስለተቀበሉ ከአንድ ሚስቱ ከሞተችበትና መዓስብ ከሆነ ጸሐፊ ጋር ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተስማሙ እኩሌቶቹ ግን ተቃወሟቸው እንዲህም አሏቸው የአባቶቻችን ቀኖና መማለጃ የሚቀበለውን ሁሉ ወይም ስለ ክህነት ሹመት መማለጃ የሚሰጠውን ያወግዛል ። ይልቁንም ይህ ሰው ሚስት አግብቷል እንዴት ሊሾም ይችላል በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ የሚሾም ንጹሕ ድንግልም ነውና።

ይህንንም በአሏቸው ጊዜ ፈሩ ተመልሰውም ተስማሙ ለዚች ለከበረች ሹመት የሚሻለውን ይገልጽላቸው ዘንድ ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን በአንድ ምክር ሁነው ጸለዩ እግዚአብሔርም ሰምቷቸው ለዚች የከበረች ሹመት የሚሻል አባ ዮሴፍ እንደሆነ አሳሰባቸው።

ከዚህም በኋላ አባ ዮሴፍን ያመጡት ዘንድ ወደ አስቄጥስ ገዳም መልእክተኞችን ላኩ መልክተኞችም ይህን አባት ዮሴፍን የመረጥከው ከሆነ ምልክትን ትገልጥልን ዘንድ አቤቱ እንለምንሃለን የቤቱም ደጃፍ ክፍት ሁኖ ካገኘን ምልክት ይሁንልን ብለው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ።

በደረሱም ጊዜ አንዱን መነኰስ እየሸኘ የበዓቱም ደጃፍ ክፍት ሁኖ አባ ዮሴፍን አገኙት በአያቸውም ጊዜ መንፈሳዊ ሰላምታ በመስጠት እጅ ነሣቸውና በደስታ ተቀብሎ ወደ በዓቱ አስገባቸው በዚያንም ጊዜ ለአባ ዮሴፍ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ይዘው አሠሩት ። እርሱ ግን እኔ ብዙ ኃጢአትን ሠርቻለሁና ይህ የከበረ ሹመት አይገባኝም እያለ ይጮህ ነበር እነርሱም ወደ እስክንድርያ ከተማ ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እንጂ ምንም ምክንያት አልተቀበሉትም።

በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም በተቀመጠ ጊዜ ለአብያተ ክርስቲያን እጅግ የሚያስብ ሆነ ለርሱ የሆነውን የግብሩን ገቢ ወስዶ ምድሮችን በመግዛት ለአብያተ ክርስተያን መተዳደሪያ ሊሆኑ ጉልቶች ያደርጋቸው ነበርና።

አዘውትሮም ሕዝቡን የሚያስተምራቸው ሆነ በምንም በምን ለየአንዳንዱ ቸለል አይልም ነገር ግን ሰይጣን ስለቀናበት ያለ ኀዘን አልተወውም ። ይህም እንዲህ ነው በምስር አገር የተሾሙ ሁለት ኤጲስቆጶሳት በሕዝቡ ላይ ክፉ ነገር በማድረግ በማይገባ ሥራ አስጨነቋቸው እርሱም በርኅራኄና በፍቅር መንጎቻቸውን እንዲጠብቁ አዘዛቸው ለመናቸውም እነርሱ ግን ሰምተው ከክፋታቸው አልተመለሱም።

በሕዝቡም ላይ ችግርን በአበዙ ጊዜ ሕዝቡ ሁሉም በጠቅላላ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ መጡ በፊቱም እንዲህ ብለው ጮኹ እሊህን ኤጲስቆጶሳት ከላያችን ካላነሣሃቸው እኛ ወደሌላ ሃይማኖት እንገባለን አባ ዮሴፍም በመካከላቸው ሰላምን ለማድረግ ብዙ ትግልን ታገለ ግን አልተቻለውም።

ከዚህም በኋላ በግብጽ አገር ያሉትን ኤጲስቆጶሳት ለጉባኤ ሰበሰባቸውና ስለ እሊህ ሁለት ኤጲስቆጶሳት ነገራቸው አሁንም ከመንጋዎቻቸው ጋር ሊአስታርቅ ሽቶ እሊህን ኤጲስቆጶሳት ወደ ጉባኤው አስቀረባቸው እነርሱ ግን የጉባኤውንም የእርሱንም ቃል አልተቀበሉም ስለዚህም ያ ጉባኤ ከሹመታቸው ሻራቸው።

እነርሱም ወደ ግብጽ ንጉሥ ሒደው በሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ ላይ በሐሰት ነገር ሠሩበት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍንም ያመጡት ዘንድ ንጉሡ ወንድሙን ከጭፍራ ጋር ላከው። የንጉሡም ወንድም ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ በደረሰ ጊዜ ተበሳጨ ሊገለውም ወዶ ሰይፉን መዞ ሊቀ ጳጳሳቱን ሊመታው ሰነዘረበት ግን እጁ ወደ ሌላ አዘንብሎ ምሰሶ መትቶ ሰይፉ ተሰበረ እጅግም ተቆጥቶ ሌላ ሰይፍን መዝዞ በመላ ኃይሉ መታው ያን ጊዜም ሰይፉ ከአንገቱ ወደ ወገቡ ተመልሶ ልብሱንና ቅናቱን ብቻ ቆረጠ የንጉሡም ወንድም ከክፋት ንጹሕ እንደሆነ ስለዚህም አምላካዊት ኃይል እንደምትጠብቀው አሰበ አስተዋለም።

ወደ ንጉሡም በክብር አደረሰው ወንድሙ ለሆነ ንጉሥም በእርሱ በሊቀ ጳጳሳቱ ላይ የሆነውን ሁሉ ነገረው ንጉሡም ፈራው አከበረውም ከዚህም በኋላ ስለከሰሱት ስለ ሁለቱ ኤጲስቆጶሳት ጠየቀው እርሱም ስለ ክፉ ሥራቸው በጉባኤ እንደተሻሩ እውነቱን ለንጉሡ አስረዳው ያን ጊዜም ሐሰተኞች እንደሆኑ ንጉሥ አወቀ ይገድሏቸውም ዘንድ አዘዘ።

ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍም ንጉሡን እንዲህ ብሎ ማለደው ጌታችን በክፉ ፈንታ በጎ እንድናደርግ እኛን አዞናልና ስለ እግዚአብሔር ብለህ እሊህን ማራቸው እንጂ አትግደላቸው ንጉሡም ስለ የዋህነቱ አደነቀ ልመናውንም ተቀብሎ ማረለት።

ከዚህም በኋላ በሹማምንቱና በኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ ላይ የፈለገውን ያደረግ ዘንድ ቢፈልግ እንዲሾም ወይም እንዲሽር የሚቃወመው እንዳይኖር ደብዳቤ በመጻፍ ሥልጣንን ሰጠው።

በዚህም አባት ዘመን የኢትዮጵያ ንጉሥ ወደዚህ አባት ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ እንዲህ ብሎ መልእክትን ላከ ለወንጌላዊ ማርቆስ መንበርና በላዩ ለመቀመጥ ለተገባው ቅድስናህ እጅ እነሣለሁ በእኔና በመንግሥቴ ላይ በመላው ወገኖቼ በኢትዮጵያ ሰዎች ላይ ይቅርታ እንድታደርግና አባታችንን አባ ዮሐንስን እንድትልክልን እለምንሃለሁ ከሀገራችን ሰዎች ከእውነት መንገድ የወጡና የሳቱ ጳጳሳችንን አባ ዮሐንስን እኔ ሳልኖርና ሳላውቅ አባረውታልና ስለዚህም በሀገራችን ቸነፈርና ድርቅ ሁኖ ከሰዎችም ከእንስሶችም ብዙዎች አለቁ።

አሁንም አባቴ ሆይ ስንፍናችንን ይቅር በል መሐሪና ይቅር ባይ ወደ ሆነ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልድልን ዘንድ በከበረች ጸሎቱም ከዚህ መከራ እንድን ዘንድ አባታችንን አባ ዮሐንስን ላክልን።

አባቴ ሆይ የተባረረበትን ምክንያት እኔ አስረዳሃለሁ እኔ ልጅህ ከአባቴ ከጳጳስ አባ ዮሐንስ ቡራኬ ተቀብዬ እርሱ ከሠራዊቴ ጋር በፍቅር አሰናብቶኝ ወደ ጦር ሜዳ ሔድሁ ከጦር ሜዳም በተመለስኩ ጊዜ አባቴን አባ ዮሐንስ ጳጳሱን አጣሁት ስለርሱም በጠየቅሁ ጊዜ በቀድሞ ዘመን ዮሐንስ አፈ ወርቅን ንግሥት አውዶክስያ እንዳሳደደችው በክፉዎች ሰዎች ምክር ንግሥቲቱ ሚስቴ ማሳደዷን የቀኖናውንም ትእዛዝ በመተላለፍ በፈቃዳቸው ሌላ ጳጳስ እንደሾሙ ነገሩኝ።
እርሱ አባ ዮሐንስም ከኢትዮጵያ በአሳደዱት ጊዜ ወደ አስቄጥስ በመሔድ አስቀድሞ በመነኰሰባት በአባ ሙሴ ጸሊም ገዳም በዚያ ተቀመጠ። የኢትዮጵያ ንጉሥ መልእክትም ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ በደረሰች ጊዜ አነበባት ስለ ኢትዮጵያ ንጉሥ የሃይማኖት ጽናት እጅግ ደስ አለው ፈጥኖም ወደ አስቄጥስ ገዳም መልእክተኞችን ልኮ አባ ዮሐንስን ወደርሱ አስመጥቶ አረጋጋው አጽናናው ከዚያም በኋላ ከደጋጎች ሰዎች ጋር ወደ ኢትዮጵያ አገር ላከው።

አባ ዮሐንስም ወደ ኢትዮጵያ አገር በደረሰ ጊዜ ቸነፈር ተወገደ ዝናብም ዘነበ ንጉሡና መላው የኢትዮጵያ ሰዎች ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑት። ይህም ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ መናፍቃንን የሚገሥጻቸው ሆነ ሕዝቡንም ከአባቶቻቸው በተቀበሏት በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አስተማራቸው ከቅዱሳት መጻሕፍትም ለእነርሱም ሥውር የሆነውን ተርጉሞ ያስረዳቸዋል ያስገነዝባቸዋልም በትምህርቱና በጸሎቱም እንዲህ ጠበቃቸው ጌታችንም በእጆቹ ብዙዎች ተአምራትን አደረገ ያማረች ገድሉንም ፈጽሞ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም በፍቅር አረፈ ። መላ የሕይወቱም ዘመን ሰባ ስምንት ነው ከምንኲስና በፊት ሃያ አመት በምንኲስና ተጋድሎ ሠላሳ ዘጠኝ ዓመት በሊቀ ጵጵስና ሹመት ዓሥራ ዘጠኝ ዓመት ኖረ ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_እለእስክንድርያ_ሰማዕት

ዳግመኛም በዚህች ቀን የከሀዲ ዱድያኖስ ንጉሥ ሚስት የከበረች እለእስክንድርያ መታሰቢያዋ ነው። ይኸውም ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ መስሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘበተበት ጊዜ ዝንጉዕ ዱድያኖስም ዕውነት መስሎት ራሱን ሊስም ተነሣ። ቅዱሱ ግን ለአማልክት ከመሠዋት አስቀድሞ አይሆንም ብሎ እንዳይስመው ከለከለው።

ከዚህ በኋላም ዱድያኖስ ወደ ቤተ መንግሥቱ አዳራሽ ቅዱስ ጊዮርጊስን አስገባው በዚያም በንግሥት እለእስክንድርያ ፊት የዳዊትን መዝሙር በማንበብ ጸለየ። በሰማችም ጊዜ ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው ያን ጊዜም ተረጐመላት የክብር ባለቤት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነቱን ገለጠላት ትምህርቱም በልቡዋ አድሮ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነች።

ከዚህም በኋላ ሲነጋ ለአማልክት ወደሚሠዋበት ቅዱስ ጊዮርጊስን ወሰዱት እርሱም የረከሱ አማልክትን ትውጣቸው ዘንድ ምድርን አዘዛት ምድርም ዋጠቻቸው። ንጉሥ ዱድያኖስም አፈረ እየአዘነና እየተከዘ ወደ ሚስቱ ወደ እለእስክንድርያ ዘንድ ገባ። እርሷም ክርስቲያኖችን አትጣላቸው አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነው አላልኩህምን አለችው። ይህንንም ሰምቶ በእርሷ ላይ ተቆጣ ያሠቃዩዋት ዘንድ ጡቶቿንም ሠንጥቀው ይሰቅሏት ዘንድ አዘዘ። የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዲዮናስዮስ_ኤጲስቆጶስ

በዚችም ቀን የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ ዲዮናስዮስ በዐላውያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን በሰማዕትነት አረፈ ይህንንም ቅዱስ በያዙት ጊዜ ብዙ ሥቃይን አሠቃዩት ማሠቃየቱንም በሰልቹ ጊዜ ራሱን በሰይፍ አስቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ጻድቁ_አቡነ_ኤልሳ

ዳግመኛም በዚህች ቀን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተተክለው በደብረ ሊባኖስ የተሾሙት አቡነ ኤልሳ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ጻድቁ ሀገራቸው ሸዋ ነው፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመን የነበሩ ሲሆን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥለው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በእጨጌነት የተሾሙ የመጀመሪያ ዕጨጌ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከማረፋቸው በፊት ‹‹በእኔ ወንበር ኤልሳዕ ይሾም ነገር ግን ዘመኑ ትንሽ ስለሆነ ከእርሱ ቀጥሎ ፊሊጶስን ትሾማላችሁ›› ብለው ለቅዱሳን ተከታይ ሐዋርያቶቻቸው ተናግረው ነበር፡፡

በዚህም መሠረት አቡነ ኤልሳዕ ተሹመው ብዙም ሳይቆዩ አንድ ዲያቆን ሞተና ሊቀብሩት ሲወስዱት በመንገድ ላይ ሳለ ድንገት ከሞት ተነሥቶ ‹‹አባቴ ተክለ ሃይማኖት ኤልሳዕ አሁን ወደኔ ስለሚመጣ ፊሊጶስን ሹሙት ብለህ ተናገር ብለውኝ ነው›› ብሎ ከተናገረ በኋላ ተመልሶ ዐርፎ ተቀበረ፡፡ አቡነ ኤልሳዕም ወዲያው ዐርፈው አቡነ ፊሊጶስ 3ኛ ሆነው ተሾሙ፡፡ አቡነ ኤልሳዕ ከተጋድሎአቸው ብዛት የተነሣ በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ጎናቸውን አሳርፈው ተኝተው አያውቁም ነበር፡፡ ነገር ግን ማረፍ ሲኖርባቸው በወንበር ላይ ተደግፈው ትንሽ ብቻ ያርፉ ነበር፡፡ አቡነ ኤልሳዕ በሞት ያረፉትም እንደልማዳቸው ጎናቸውን ሳያሳርፉ በወንበር ላይ እንደተደገፉ ነበር፡፡ አባታችን ስለዚህም ጉዳይ ሲናገሩ እንዲህ ይሉ ነበር፡- ‹‹ነፍስ ትጋትን ትወዳለች፣ ሥጋ ግን ይደክማል፡፡ ለመነኮሳትና ለእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ መኝታ ማብዛት አይገባቸውም፡፡ መኝታ ማብዛት ሕልምን ያመጣል፣ ነፍስን ይጎዳል፣ ሰውነትንም ያደክማል፡፡››

አቡነ ኤልሳዕ በዘመናቸው ወንጌልን በማስተማርና ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቁ ነበር፡፡ እንደ ነቢዩ ኤልሳዕ እሳቸውም ሙት አስነሥተዋል፡፡ ባሕር እየከፈሉ ቀደ መዛሙርቶቻቸውን ያሻግሩ ነበር፡፡ በጸሎታቸው የዠማን ወንዝም ለሁለት የከፈሉ ታላቅ አባት ናቸው፡፡

ለእግዚአብርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥቅምት እና #ከገድላት_አንደበት)
#መጋቢት_13

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን የታላቁ አባት #የቅዱስ_መቃርስ እና #የቅዱስ_መቃርዮስ_ዘእስክንድርያ የስደታቸውን መታሰቢያ ነው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ አረፈ፣ የከበሩ #ቅዱሳን_አርባ_ሐራ ሰማይ በሰማዕትነት አረፉ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ታላቁ_ቅዱስ_መቃርስ እና #ቅዱስ_መቃርዮስ_እስክንድርያዊ

መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን ኦርቶዶክሳውያን ሰዎች የታላቁ አባት የመቃርስን የእስክንድርያው የመቃርዮስን የስደታቸውን መታሰቢያ ያከብራሉ። ይህም በሮም መንግሥት ከወንድሙ ከዋልጥስ በኋላ በነገሠ ጊዜ በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ ስደትንና መከራን አመጣ።የረከሰ የማኒንና የከሀዲው አርዮስን እምነት ስለሚከተል ነው ለእስክንድርያም ሉክዮስን ሊቀ ጳጳሳት አድርጎ ሹሞ ሐዋርያዊ አትናቴዎስን አሳደደው።

ይህም ከሀዲ ሉክዮስ ታላቁን አባት አባ መቃሪን እስክንድርያዊውን አባት መቃርዮስን ፈልጎ በንጉሥ ትእዛዝ ወደርሱ ከገዳማቸው አስመጣቸው። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ለያይቶ በለሰለሰ አንደበት በመሸንገል ወደረከሰ የአርዮስ ሃይማኖት ይገቡ ዘንድ አግባባቸው። እነርሱ ግን ወደ ነገሩ አልተመለሱም ሳይፈሩትም መለሱለት በቅንነትና በትዕግሥትም መከሩት ገሠጹት እንጂ የአርዮስንም ሃይማኖት ብላሽነት የባህሉንም አስከፊነት ከቅዱሳት መጻሕፍት ለይተው አስረዱት።

በዚያን ጊዜም ተቆጣ ከቊስጥንጥንያ መካከል ወደምትርቅ ደሴት አጋዛቸው ከእስክንድርያም መርከብን የሚጠብቋቸውንም ወታደሮችን በእነርሱ ላይ በሚያደርጉት ሥራ ሁሉ አጫንቀው በብረት አሥረው ይወስዱአቸው ዘንድ አዘጋጁ። ወደዚች ደሴት በደረሱ ጊዜ በደሴቱ ንጉሥ ፊት አቆሙአቸው ንጉሡም ሰይጣንን የሚያመልክ የከፋ ሰው ነበር የደሴቱም ሰዎች አምላክ ነው ብለው እስቲ አምልኩትና እስቲሰግዱለት ድረስ በሥራዩ አስቷቸው ነበር።

እሊህ አባቶቻችንም ከስሕተቱ እንዲመለስ አስተማሩት ለመኑትም አልሰማቸውም ከብዙ ሥቃይ ጋር በወህኒ ቤት ዘጋባቸው እንጂ በጽኑዕ ሥቃይም አሠቃያቸው ጌታችንም ተገልጦ የሚያጸናቸውና የሚያስታግሣቸው ሆነላቸው። የክብር ባለቤት ጌታችንም ጽድቃቸውንና ትሩፋታቸውን ሊገልጥ በወደደ ጊዜ የንጉሡን ልጅ ሰይጣን ያዛት። አባትና እናቷም በታላቅ ኀዘን ላይ እስቲሆኑ አብዝቶ አሠቃያት በከተማ ውስጥም ሰይጣናት ተገልጠው መቃርስና ባልንጀራው ሆይ እኛ ከእናንተ እናንተ ከኛ ምን አላችሁ ከአገራችሁ ያሰደዳችሁን እያሉ ተገልጠው ይጮኹ ጀመር።በንጉሡ ልጅ ያደረውም ሰይጣን ንጉሥ ሆይ መቃርስና ባልንጀራው ካልመጡ ከልጅህ ላይ አልወጣም ብሎ ጮኸ ንጉሡና አብረውት ያሉ አደነቁ ወደ ንጉሡም ቅዱሳንን አመጡአቸው።

እሊህ ቅዱሳን መቃርስና ባልንጀራው ወደ ንጉሥ በደረሱ ጊዜ በንጉሡ ልጅ ያደረ ሰይጣን እንዳያሠቃዩት ለመነ። ንጉሡና አብረውት ያሉትም ስለ ሥራቸው ቅዱሳንን መረመሩአቸው፡፡ እነርሱም የሆነውን ሁሉ ነገሩአቸው ስለ ንጉሡም ልጅ ያድኑዋት ዘንድ ለመኑዋቸው። እነርሱም ንጉሡን ገሠጹት እንዲህም አሉት አንተ ሰው ስትሆን ለምን ራስህን አምላክ ታደርጋለህ ዓለምን የፈጠረ አምላክ ከሆንክ ራስህንና ልጅህን ማዳን ይገባህ ነበር። ያን ጊዜም ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ጸልየው ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ስለ ክፉ ሥራቸው ንጉሡንና የዚያችን ደሴት ሰዎች ዘለፋቸው።

ንጉሡና በዚያ የተሰበሰቡት ይህን አይተው በእሊህ ቅዱሳን አምላክ እናምናለን ከእሊህ ቅዱሳን አምላክ ከእግዚአብሔር በቀር በሰማይና በምድር ሌላ አምላክ እንደሌለ ተረድተናልና እያሉ ጮኹ። የከበሩ አባቶቻችንም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን አሰተማሩአቸው እነርሱም በሽተኞቻቸውን ሁሉ ሰበሰቡ አባቶቻችንም በዘይት ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ቀብተው በሽተኞችን ሁሉ አጋንንት ያደሩባቸውንም ሁሉንም አዳኑአቸው እንዲሁም እያደረጉ እያስተማሩዋቸውም ብዙ ቀን ኖሩ።

ከዚህም በኋላ የሀገሩን ምኵራብ አስፈርሰው ቦታውን አጸዱ አነፁ ቦታውም እጅግ ስፋት ያለው መልካም ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሳነፁ ንጉሡም ስፍር ቁጥር የሌለው ወርቅና ብር የሐር ልብሶችንም ለእግዚአብሔር መቅደስ ለሚአሻውም ሁሉ አመጣ። የከበሩ አባቶቻችንም ጥበብ ያላቸው አንጣሪዎችን ሚዛኑ ለየአንዳንዱ ዘጠኝ ልጥር የሚሆን አሥራ ሁለት ጻህሎችን ሠርተው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንና የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ሥዕል የሁለቱንም የመላእክት አለቆች የሚካኤልንና የገብርኤልን ሥዕል በውስጡ እንዲሥሉ ደግሞ አሥራ ሁለት መንበሮችን ለመሠዊያ የሚፈለገውንም ሁሉ አሥራ ሁለት ጽዋዎችና አሥራ ሁለት ዕርፈ መስቀልም እያንዳንዱ ሦስት ሦስት ልጥር የሆኑ ሃያ አራት መስቀሎችን እንዲሠሩ ሦስቱንም የመቅደስ ግድግዳ እንዲሥሉ አዘዙ።

የቤተ ክርስቲያኒቱ የሕንፃዋ ሥራ ተፈጸመ። የተረፈውንም ገንዘብ ለድኆችና ለችግረኞች በተኑ። ጌታችን የተጠመቀባት ጥር ዐሥራ አንድ ቀን በሆነች ጊዜ ወደ ባሕር አጠገብ እንዲወርዱና እንዲሰበሰቡ የአገሩን ሰዎች አዘዙዋቸው። ከእስክንድርያም በተሰደዱ ጊዜ እግረ መንገዳቸውን የያዙትን የከበረ ሜሮንን አመጡ። ይህም ከሐዋርያዊ አትናቴዎስ ጊዜ ጀምሮ የተጠበቀ ሉክዮስም ያላገኘው ጌታችንም በዘመናት ሁሉ የጠበቀው ጥፋት ያላገኘው ነው።ይህ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ሆኖአልና።

በዚያንም ጊዜ አባት መቃሪ በከበረ ሜሮን በጥልቁ ባሕር ላይ ባረከ ባሕሩም ከእሳት ኃይል የተነሣ በድስት እንደሚያፈሉት ውኃ የሚፈላ ሆነ ዘይቱና ሜሮኑም በውኃው ላይ ተንሳፈው እንደሚያበሩ ከዋክብት ሆኑ ከእርሳቸውም እንደ ፀሐይ የሆነ ታላቅ ብርሃን ታየ። ንጉሡና የተሰበሰቡት ሕዝብ አይተው ፈሩ። የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠ። አጥማቂው ዮሐንስና ቅዱሳን መላእክትም ውኃው በመከብርበትና በሚለወጥበት ጊዜ ተገለጡ። ሕዝቡም ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ ያንጊዜ ከሽቱ ሁሉ መዓዛው የሚጣፍጥ ሽታ ሸተተ።

በዚያን ጊዜም የከበሩ አባቶቻችን ይህን አይተው በምድር ላይ ወድቀው ሰገዱ በስግደታቸው እዚያው ዘገዩ። አባት መቃርስም ሰግዶ ሳለ ጌታችንን እንዲህ ሲል ለመነው። ጌታዬ እለምንሃለሁ ቸርነትህ ትድረሰኝ የዚች ታቦትና ንዋየ ቅድሳቷ ቡራኬ በአምላካዊት እጅህ እንዲሆን አለው።ጌታም እሺ በጎ ብሎ ሜሮኑን ከአባ መቃሪ እጅ ተቀብሎ ታቦቱንና ንዋየ ቅዱሳቱን አከበረ።

ከዚያም በኋላ አባት መቃርስን ሦስቱን ደርብ ትባርክ ዘንድ እኔ አዝሃለሁ እኔም ካንተ ጋራ አለሁ ይህንንም ንጹሕና ክቡር የሆነ አገልግሎት ባልንጀራህ አብሮህ ያገልግል። በመጀመሪያም የመካከለኛውን ደርብ በሥጋ በወለደችኝ በድንግል ማርያም ስም ለይተህ አክብር ደግሞ በቀኝ በኩል ያለውን በከበረ መስቀል ስም ለይተህ አክብር በግራ በኩል ያለውን ደርብ በስምህ ለይተህ አክብር በከሀዲ ሉክዮስ እጅ ስለ ስሜ በዚች ደሴት ውስጥ ደምህን አፍሰሃልና አለው።

እሊህም የተባረኩ አባቶች ጌታችን እንደ አዘዘ ሊሠሩ በጀመሩ ጊዜ ንጉሥ ዳዊት በመዝሙር ሊያመሰግን ጀመረ መላእክትም በመልካም ቃላት በቋንቋቸው ያመሰግኑ ጀመር ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
ዳግመኛም ጌታችን አባ መቃርስን መሥዋዕቱን ተሸክሞ በመሠዊያ ላይ ይቀድስ ዘንድ አዘዘው አባ መቃርስም ጌታችንን የሐዋርያት አለቃ አባታችን ጴጥሮስን እንዲቀድስ እዘዘው ይኽቺ ዕለት በከበረ ስምህ በዚች ደሴት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መሥዋዕት የተሠዋባት ናትና አለው።
ጌታም ላንተ ይገባል አንተ በዚች ደሴት ዘርተሃልና እኔም አሳደግሁ በደቀ መዝ ሙሬ በጳውሎስ አድሬ የተናገርኩትን አላስተዋልክምን የዘራና የደከመ እርሱ አስቀድሞ ፍሬውን ይብላ ያልሁትን አለው።

አባት መቃርስም የቅዳሴውን ሥርዓት ከጌታ ተባርኮ በጀመረ ጊዜ ከእስክንድርያዊ መቃርዮስ ጋራ ይራዱት ዘንድ ጴጥሮስ በቀኙ ማርቆስ በግራው ሁሉም ሐዋርያት በዙሪያው ቆሙ።ጳውሎስና ዮሐንስም የየራሳቸውን መልእክት አነበቡ ሉቃስም የሐዋርያትን ሥራ አነበበ ዳዊትም መዝሙሩን ዘመረ ለስም አጠራሩ ምስጋና ገንዘቡ የሆነ ጌታችንም ወንጌሉን አነበበ።በነጭ ርግብ አምሳልም መንፈስ ቅዱስ በኅብስቱና በውይኑ ላይ ወርዶ የጌታችን ክርስቶስን ሥጋና ደም ወደመሆን ለወጣቸው።

አባት መቃርስም ወደ ጽዋው ጣቱን በአስገባ ጊዜ ጣቱ በደም ታለለ።የመላእክት ሠራዊት ሁሉ በመሠዊያው ላይ ክንፋቸውን ዘርግተው ይራዱት ነበር ሚካኤልና ገብርኤልም መጡ የመላእክት አንድነት ሁሉም በእርሱ በአባት መቃርስ አምሳል ሁነው እየተራዱት ለሕዝቡ የከበረ ሥጋውንና ደሙን አቀበለ። ከቁርባን ሥርዓት ፍጻሜ በኃላ ጌታችን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃርስ አምሳል ሁኖ ወንጌል በሚነበብበት አትሮንስ ላይ ተቀመጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ ይበራ ነበር ለሕዝቡም ቡራኬ ሰጥቶ ወደ መሠዊያው ተመለሰ ሐዋርያትም ከርሱጋራ።

ዳግመኛም ከሰባት ቀኖች በኃላ አባታችን መቃርስ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሹመት ማዕርግ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጦ በእኔ ዘንድ ለዚህ ታላቅ ክብር የምትገባ አንተ ነህና አለው።

ሽማግሌውም ሰምቶ አለቀሰ በእግዚአብሔርም ፊት ሰገደ አቤቱ በሲሐት ገዳም ወዳሉ መነኰሳት ልጆችህ ጊዜው ሲደርስ እመልስሃለሁ ከዚህ ከሥጋህ ሳትለይ ያልከኝን አስብ።ይህ ካልሆነ መቃራ የምንኲስናውን ሥራ ትቶ ፓትርያርክ ሆነ ይላሉ አለ። ጌታችንም የመረጥኩህ መቃርስ ሆይ እኔ የልብህን ፍላጎት ሁሉ እፍጽምልሃለሁ ግን ፓትርያርክ ትሾም ዘንድ ከልጆችህ የመረጥከውን አንድ አቅርብ አለው። ቅዱስ መቃርስም አቤቱ አንተ ልብ ያሰበውን የምታውቅ ነህ እኔ ግን ወደዚህ አንጥረኛ ሽማግሌ ሰው ተመለከትኩ። እርሱ በቀናች ሃይማኖት የጸና ከሴቶችም ጋር ግንኙነት የማያውቅ ነው አለው ጌታችንም አንተ እንዳልክ ደግ ነው አለ። ቅዱስ መቃርስም ያንን አንጠረኛ ጠርቶ ወደ ታቦተ ሕጉ አቀረበው ያን ጊዜም ወንጌላዊው ማርቆስ መጣ እጁንም በአንጠረኛው ራስ ላይ ጭኖ ዲቁና ሾመው። ደግሞ ቅስና ሾመው ከዚያም የሊቀ ጵጵስና ሹመት እስከ ሚፈጽም በየመዐርጉ ሾመው ስሙንም ዮሐንስ አለው የሰማይ ሠራዊትም ሁሉም የወንጌላዊ ማርቆስ አዲስ ተክል የሆነ ለመቃርስ ልጅ ለዮሐንስ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሦስት ጊዜ ጮኹ በዚያ ያሉ ሕዝብም እሊህን ቃሎች ይሰሙ ነበር።

ጌታችንም የሊቀ ጳጳሳት የዮሐንስን ዓይነ ልቡናውን ገልጦለት በሚቻለው መጠን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አየው።ብዙ ቃላትንም ተናገረ ደግሞ ረቂቃን በሆኑ በሰማይ ሠራዊት ቤተ መቅደሱ ተመልቶ አየ የከበሩ ነቢያትና ሐዋርያትም በዚያ አሉ።

ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቁ አባ መቃራንና የእስክንድርያውን አባ መቃራን ጠራቸው እንዲህም አላቸው በምድር ሳሉ መታሰቢያችሁን የሚያደርጉ ሰዎች የተመሰገኑ ናቸው የዘላለም ሕይወትን ይወርሳሉና በራሴ እምላለሁ ስለ ስሜ የተቀበላችሁትን መከራ በትጋት የሚአስበውና የሚጽፈው የሚሰማው ሁሉ ያመሰግነኝ ዘንድ በቤተ ክርስቲያን የሚያነበው እኔ በጎ ነገርን ሁሉ እሰጠዋለሁ። ከበጎ ነገርም ምንም አላሳጣውም ከመከራውም ሁሉ አድነዋለሁ ኃጢአቱንም ሁሉ አስተሠርይለታለሁ። ከዚህ ዓለምም በሚለይለት ጊዜ ነፍሱን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ይወስዱ ዘንድ እናንተ ወደም ታስቡትም መንግሥቴ ሊአስገቡት የምሕረት መላእክትን እልካለሁ።

በገዳም ወይም በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ወይም በአገር ውስጥ ይህ ዜናችሁ በሚነበብበት እኔ አድራለሁ በረከቴንና ሰላሜንም እስከ ዓለም ፍጻሜ በውስጥዋ አደርጋለሁ። ለዚህ ለስደታችሁ ዜና ተቃራኒ የሚሆን ባልተወለደ በተሻለው ነበር። በእውነት እነግራችኋላሁ በሰው ፊት እንደአመናችሁብኝ በሰማያት በአለው አባቴ ፊትና በከበሩ መላእክቶቼ ፊት አምንባችኋለሁ። አሁን ግን ወደ ሀገራችሁ የምትመለሱበት ጊዜ ደረሰ ይህንንም ብሎ ሰላምታ ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ በክብር ዐረገ።

ከዚህ በኋላ ሕዝቡን ሁሉ ንጉሡንም ሰበሰቧቸው ወደ አገራቸውም እንደሚመለሱ ነገሩአቸው የክርስቶስንም ሕጉን ሁሉ እንዲጠብቁ ለሊቀ ጳጳሳቱ ዮሐንስም እንዲታዘዙ አዘዙአቸው።ከቀናች ሃይማኖት ወደ ቀኝም ቢሆን ወደ ግራም ፈቀቅ እንዳይሉ በብዙ አማፀኑአቸው አስጠነቀቋቸውም። ሕዝቡም ሰምተው ደነገጡ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ ቅዱሳን አባቶቻችንም ከእሳቸው ጋራ በአንድነት አለቀሱ ከእዚህም በኋላ እየአንዳንዳቸውን ባረኳቸውና ተሰናበቷቸው።

ያን ጊዜም ከኪሩቤል ወገን የሆነ መልአክ መጣ አውጥቶም በክንፎቹ ተሸከማቸው ወደ እስክንድርያም አድርሶ በሊቀ ጳጳሳቱ ደጅ እሑድ ጥዋት አወረዳቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስም ሰምቶ እጅግ ደስ አለው።ሁለተኛም በአያቸው ጊዜ አለቀሰ ሰገደላቸውም እነርሱም ሰገዱለት እርስ በርሳቸውም እጅ ተነሣሥተው ሰላምታ ተለዋወጡ። ጤንነታቸውንም ተነጋገሩ ደግሞም ልዩ የነበሩ የአሕዛብን ወደ እግዚአብሔር ስለመመለሳቸውና ስለ ተደረጉት ድንቆች ተአምራት ነገሩአቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስና ይህን የሰሙ ሁሉም ሕዝብ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት አባቶቻቸንም በዚያ ስምንት ቀን ተቀመጡ።

ከዚህም በኋላ ያ መልአክ ተገልጦ በክንፎቹ ደግሞ ተሸከማቸው ወደ ደብረ ሲሐትም አደረሳቸው አንዱ ኪሩብም ከአየር ሁኖ የአባት መቃርስ ልጆች ሆይ አባታችሁ የመንፈስ ቅዱስን ፍሬዎች ተሸክሞ ከስደት ተመልሶ መጥቷልና ወጥታችሁ ተቀበሉ እያለ ጮኸ፡፡ ይህንንም በሰሙ ጊዜ ከታላላቆች እስከ ታናናሾች ወጡ ቁጥራቸውም አምሳ ሺህ መነኰሳት ሆኑ። ከውስጣቸውም በዚያን ጊዜ አባ ዮሐንስ ሐፂርና አባ ብሶይ አሉ የደረሰባቸውንም ሥቃይ በነገራቸው ጊዜ እጆቹንና እግሮቹን እየሳሙ መሪር ዕንባ አለቀሱ። ደግሞ ፊቱን ስለአዩ ደስ አላቸው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባረካቸው።

የክርስቶስ ወገን የሆናችሁ በዓለሙ ሁሉ የምትገኙ ምእመናን ሆይ በዘመናት ሁሉ በዓል እያደረጋችኋት በዚች ዕለት ደስ ሊላችሁ ይገባል።ይህም ለአምላካችን ክርስቶስ ስለ ስሙ ደማቸውን እንዳፈሰሱ እንደ ጴጥሮስና እንደ ጳውሎስ መታሰቢያ ለእሊህ ታጋዮች አባቶች ለመከራቸው መታሰቢያ እንዲሆን።

እሊህም ታላቁ አባ መቃርስና ባልንጀራው የእስክንድርያው አባ መቃርስ ናቸው በዚች በመጋቢት ወር በዐሥራ ሦስተኛ ቀን ሉክዮስ ከእስክንድርያ አስቀድመን ወደ አወሳናት ደሴት አጋዛቸው ደግሞ በዚሁ ቀን ተመልሰው ወደ እስክንድርያ ደረሱ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዲዮናስዮስ
#ጥቅምት_6

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ስድስት በዚህች ቀን እመ ሳሙኤል ነቢይ #ቅድስት_ነቢይት_ሐና ያረፈችበት፣ ቅዱስ አባት #አባ_ጰንጠሌዎን ያረፈበት፣ #ዕንባቆም_ነቢይ መታሰቢያው፣ የሀገረ አቴና ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ በሰማዕትነት ያረፈበት እና የሴት ልጅ #ቅዱስ_ሄኖስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ነቢይት_ሐና

ጥቅምት ስድስት በዚህች ቀን የታላቁ ነቢይና ካህን የሳሙኤል እናት ቅድስት ነቢይት ሐና አረፈች።

ይችም ቅድስት ከሌዊ ነገድ ናት የታኅርም ልጅ ሕልቃና አገባት ፍናና የምትባልም ሌላ ሚስት አለችው እርሷም ወላድ በመሆኗ ሐና ልጅ ስለሌላት መካንም ስለሆነች ሁልጊዜ ትገዳደራት ነበር።

ሐና ግን ፈጽማ በማዘን አትበላም አትጠጣም ባሏ ሕልቃናም ያረጋጋታል ማረጋጋቱንም አልተቀበለችውም በሊቀ ካህናቱ በኤሊ ዘመንም ወደቤተ እግዚአብሔር ወጣች እያለቀሰችና እያዘነች በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች እንዲህም ብላ ስለትን ተሳለች አቤቱ ልጅ የሰጠኸኝ እንደሆነ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለአንተ የሚያገለግል አደርገዋለሁ።

ካህኑ ኤሊም አያትና እርሷ የወይን ጠጅ ጠጥታ እንደ ሰከረች አሰበ እርሷ በዝምታ በልቧ ትጸልይ ነበርና በቊጣና በግሣጼ የወይን ጠጅ ጠጥተሽ ወደዚህ ወደ እግዚአብሔር ቤት ለምን መጣሽ አሁን ሒጂ ስካርሺን በእንቅልፍ አስወግጂ አላት።

እርሷም እንዲህ አለችው የወይን ጠጅ ከቶ አልጠጣሁም ልጅ ያጣሁ በመሆኔ በልቤ አዝናለሁ እንጂ ካህን ኤሊም አጽናናት እንዲሁም ብሎ ባረካት የእስራኤል ፈጣሪ የለመንሽውን ይስጥሽ በሰላም ሒጂ በቃሉም አምና ወደ ቤቷ ገባች።

ከዚህም በኋላ ፀንሳ ወንድ ልጅን ወለደች ስሙንም ሳሙኤል ብላ ጠራችው። ጡትንም በአስጣለችው ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዛው ወጣች ወደ ካህን ኤሊም አቀረበችውና እንዲህ ብላ አስረዳችው ከአሁን በፊት ልጅን ይሰጠኝ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ስጸልይና ስለምን ያየኸኝ ሴት ነኝ ልመናዬንም ሰምቶ ይህን ልጅ ሰጠኝ አሁንም በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ይሆን ዘንድ አመጣሁት።

ከዚህም በኋላ ሐና እግዚአብሔርን አመሰገነችው። ልቤ በእግዚአብሔር አምኖ ጸና የሚለውን ጸሎትና ትንቢት እስከ መጨረሻው ተናገረች። ይቺም በዳዊት መዝሙር መጨረሻ ከሙሴ መኀልይ ቀጥላ ተጽፋለች።

ከዚህም በኋላ እግዚአብሔርን አገልግላ በሰላም አረፈች።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ጰንጠሌዎን

ዳግመኛም በዚችም ቀን በዋሻ ውስጥ የሚኖር ቅዱስ አባት አባ ጰንጠሌዎን አረፈ። ይህም ቅዱስ በሮሜ አገር በንጉሥ ቀኝ ከሚቀመጡ ከከበሩ ሰዎች ወገን የተወለደ ነው ። በታናሽነቱም ጊዜ ወደ መነኰሳት ገዳም ወስደውት በበጎ ምክር ዕውቀትን እየተማረ በመጸለይና በመጾም በዚያ አደገ።

ከዚህም በኋላ ከቅዱሳን ከስምንቱ ባልንጀሮቹ ጋር ወደ ኢትዮጵያ በንጉሥ አልዓሜዳ ዘመን መጣ በአንድነትም ጥቂት ዘመናት ኑረው ከዚህም በኋላ እርስበርሳቸው ተለያዩ ቅዱስ ጰንጠሌዎንም ከታናሽ ተራራ ላይ ወጥቶ ርዝመቱ አምስት ክንድ አግድመቱ ሁለት ስፋቱ ሦስት ክንድ የሚሆን ዋሻ ለራሱ ሠራ ጠፈሩም አንድ ደንጊያ ነው ከጥቂት ቀዳዳ በቀር በር የለውም።

በውስጡም ሳይቀመጥ ሳይተኛ ያለመብልና ያለ መጠጥ አርባ አምስት ዓመት ኖረ ቆዳው ከዐጥንቱ እስከሚጣበቅ በዕንባ ብዛትም ቅንድቡ ተመለጠ። በሽተኞችን በማዳን የዕውሮችንም ዐይኖች በመግለጥ ብዙ ተአምራትን አደረገ።

በአንዲትም ቀን በማታ ጊዜ ዕንጨት ተከለ አሰከሚነጋ ድረስም አድጎ ትልቅ ዛፍ ሆነ ወዲያውም ደረቀና ደቀ መዝሙሩ ፈልጦ አነደደው ፍሙንም በልብሱ ቋጥሮ ለማዕጠንት ወሰደው።

የናግራንን አገር ያጠፋትን ምእመናኖችንም የገደላቸውን አይሁዳዊ ንጉሥ ሒዶ ሊወጋው ንጉሥ ካሌብ በአሰበ ጊዜ በጸሎቱ ይረዳው ዘንድ ይህን አባት ጰንጠሌዎንን ለመነው እርሱም በሥራው ሁሉ ላይ ችሎታ ያለው እግዚአብሔር በጠላቶችህ ላይ ድል አድራጊነትን ሰጥቶህ በደኀና በፍቅር አንድነት ትመለሳለህ አለው።

ንጉሥ ካሌብም ከናግራን ሀገር በደረሰ ጊዜ ከከሀዲው ንጉሥ ከፊንሐስ ጋር ተዋጋ ድል አድርጓቸውም ከሀድያንን ሁሉ እንደ ቅጠል እስቲረግፉ አጠፋቸው አባ ጰንጠሌዎንንም በጦርነቱ መካከል ጠላቶችን ሲአሳድዳቸው እንዳዩት ብዙዎች ምስክሮች ሆኑ።

ከዚህም በኋላ ንጉሥ ካሌብ ከድል አድራጊነት ጋር በተመለሰ ጊዜ መንግሥቱን ትቶ በዚህ አባት እጅ መነኰሰ ከዋሻ ውስጥም ገብቶ በጾምና በጸሎት እየተጋደለ ኖረ።

ይህም ቅዱስ አባ ጰንጠሌዎን ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጣ ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን የሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ቃል ኪዳን ሰጠው እንግዲህስ ድካም ይበቃሀል ዕረፍ ያን ጊዜም ዐጥንቶቹ ተነቃነቁ በፍቅር አንድነትም አረፈና በዚያ በዋሻው ውስጥ ተቀበረ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዕንባቆም_ነቢይ

በዚችም ቀን የስሙ ትርጓሜ አዋቂ የሆነ የዕንባቆም ነቢይ መታሰቢያው ነው። ይህም ቅዱስ በአንዲት ዕለት እህሉን ለሚያጭዱለት ምሳቸውን አዘጋጅቶ ተሸክሞ ሲሔድ መልአክ ተገልጾለት ይህን መብል በባቢሎን አገር በአንበሶች ጕድጓድ ውስጥ ላለ ለነቢዩ ዳንኤል ውሰድ አለው።

ዕንባቆምም ጌታዬ ሆይ ባቢሎንን አላየኋት ጉድጓዱንም አላውቀው አለው። የእግዚአብሔር መልአክም በራሱ ጠጉር ያዘው ምግቡን በእጁ እንደያዘ ወሰደውና ጉድጓዱ እንደተዘጋ አስገባው ምግቡንም ሰጥቶ መገበው ወዲያውኑ ዕንባቆምን ወደ ይሁዳ አገር መለሰው።

በአረጀና በሸመገለም ጊዜ የእስራኤል ልጆች ከተማረኩበት ተመልሰው ቤተ መቅደስን ሠሩ። ዕንባቆምም ኢየሩሳሌም ደርሶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ በታላቅ ደስታም ተቀበሉት ትንቢቱንም ሊሰሙ ወደርሱ ተሰበሰቡ አፉንም ከፍቶ በመንፈስ ቅዱስ እንዲህ አለ።

አቤቱ ድምፅህን ሰማሁ ሰምቼም ፈራሁ ሥራህንም አይቼ አደነቅሁ አለ። ስለ መድኃኒታችንም መውረድና በይሁዳ ክፍል በሆነች በቤተ ልሔም ስለመወለዱ ሲናገር የተመሰገነ እግዚአብሔር ግን ከፋራን ተራራ ከቴማን ከይሁዳ አውራጃ ይመጣል ብሎ እስከ መጨረሻው ተናገረ ከነቢያት መጻሕፍትም ጋራ ደመርዋት።

ከዚህ በኋላ ከእስራኤል ልጆች አንዲት ሴት ወደርሱ መጣች እያለቀሰችም እንዲህ አለችው። ሁለት ልጆች ነበሩኝ ጣዖት እንዲአመልኩ ፈለጉአቸው እምቢ በአሉ ጊዜም ገድለው በጐዳና ላይ ጣሉአቸው። ተገድለው ወደ አሉበትም አብሮዋት ሔደ ነፍሳቸውንም ይመልስላቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነው ልመናውንም ተቀበሎ በሕይወት አነሣቸው።

ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ ዘመዶቹን ጠራቸው። እንደሚሞትም ነገራቸውና አንዲት ሰዓት ያህል ወደላይ እየተመለከተ ተቀመጠ ። እነሆ እንደ ሰው ክንድ ያለች ታላቅ ክንድ የቤቱን ጣሪያ ሠንጥቃ ወረደች ወደ አፉም ተዘርግታ ነፍሱን ወሰደች ያን ጊዜም አረፈ።

በክርስቲያናዊ ንጉሥ በአንስጣስዮስ ዘመን እንዲህ ሆነ ገድሉን በአነበበ ጊዜ አድንቆ በግብጽ ደቡብ ቀርጣስ በሚባል ቦታ በስሙ ቤተ ክርስቲያን ተሠራለት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ኤጲስቆጶስ_ቅዱስ_ዲዮናስዮስ