እስኪ ምን ላርግልሽ
ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
አህያ
ጀርባው ይዞ ትልቅ ጭነት
አንገት ደፍቶ ሁሉ ሰው ፊት
አገልግሎት እንዳልሰጠ
በውጭ ገንዘብ ተለወጠ።
አንገቱ ላይ አርፎ ቢላ
ለእርድ ቀርቧል ነው እንዲበላ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
ጀርባው ይዞ ትልቅ ጭነት
አንገት ደፍቶ ሁሉ ሰው ፊት
አገልግሎት እንዳልሰጠ
በውጭ ገንዘብ ተለወጠ።
አንገቱ ላይ አርፎ ቢላ
ለእርድ ቀርቧል ነው እንዲበላ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
🤔
.
.
ግራ መጋባቴ እንደዉ ግራ ገብቶኝ፤
ስቋጥር ስፈታ እጅጉን አሳስቦኝ፤
ባስብ ባሰላስል ከልቤ አጣሀት፤
ግራ የገባኝን ግራ ገብቶኝ ተዉኩት።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ግራ መጋባቴ እንደዉ ግራ ገብቶኝ፤
ስቋጥር ስፈታ እጅጉን አሳስቦኝ፤
ባስብ ባሰላስል ከልቤ አጣሀት፤
ግራ የገባኝን ግራ ገብቶኝ ተዉኩት።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
በዚህ ሙቅ ከተማ
በዚህ ደማቅ መንገድ
ሺ አምፖል በበራበት
ፀሐይ ቀንና ሌት ፥ በማትጠልቅበት
ለሰው የማይታይ
አለ ብቸኝነት ።
አለ ብቸኝነት
በስንት እግሮች መሐል
ያደፈ ኮት ለብሶ
አይኑ ማዶ ፈዞ
የታክሲ ጥሩንባ የሚያደነቁረው
ሰው ገፍትሮት እንኳን
"ይቅርታ" የማይለው
ስሙ ፥ ማይነሳ
መኖሩ ፥ የተረሳ
ቢሞት ፥ ልብ የማይባል
አለ ብቸኝነት
እዚሁ ፥ እኛው መሐል ።
አለ ብቸኝነት
አንድ ጊዜ ተራምዶ
ብዙ ጊዜ የሚቆም
በፋሲካ በአል ፥ ብቻውን የሚጾም ።
አለ ብቸኝነት
ቢያውቀው ወይ ባያውቀው
የሚገላምጠው
(ወይ በመተያየት)
ፈገግታ 'ሚሰጠው
አንድ አይን የናፈቀው ።
አለ ብቸኝነት
ዕንባውን የዋጠ
ሳቁን የመጠጠ
ስሜቱን ያፈናት ፥ ልውጣ ባለች ቁጥር
ልቡ እንደ ድመት ሆድ ፥ ትር ትር የምትል ።
አለ ብቸኝነት
ወዴትም የማይሄድ ፥ ዝም ብሎ የሚራመድ
እንኳንስ ሰውና ፥ ልቡ ያልሆነው ዘመድ
ጭር ያለ ባይተዋር
በሰው ጎርፍ መሐል
ትንፋሹ የሚታየው
እርምጃ የሚመትር
ጠብታ የሚቆጥር
ወዴትም ሳንርቅ ፥ እዚሁ አፍንጫችን
እዚሁ ልባችን ስር
አለ ብቸኝነት ።
By HAB HD
@getem
@getem
@paappii
በዚህ ደማቅ መንገድ
ሺ አምፖል በበራበት
ፀሐይ ቀንና ሌት ፥ በማትጠልቅበት
ለሰው የማይታይ
አለ ብቸኝነት ።
አለ ብቸኝነት
በስንት እግሮች መሐል
ያደፈ ኮት ለብሶ
አይኑ ማዶ ፈዞ
የታክሲ ጥሩንባ የሚያደነቁረው
ሰው ገፍትሮት እንኳን
"ይቅርታ" የማይለው
ስሙ ፥ ማይነሳ
መኖሩ ፥ የተረሳ
ቢሞት ፥ ልብ የማይባል
አለ ብቸኝነት
እዚሁ ፥ እኛው መሐል ።
አለ ብቸኝነት
አንድ ጊዜ ተራምዶ
ብዙ ጊዜ የሚቆም
በፋሲካ በአል ፥ ብቻውን የሚጾም ።
አለ ብቸኝነት
ቢያውቀው ወይ ባያውቀው
የሚገላምጠው
(ወይ በመተያየት)
ፈገግታ 'ሚሰጠው
አንድ አይን የናፈቀው ።
አለ ብቸኝነት
ዕንባውን የዋጠ
ሳቁን የመጠጠ
ስሜቱን ያፈናት ፥ ልውጣ ባለች ቁጥር
ልቡ እንደ ድመት ሆድ ፥ ትር ትር የምትል ።
አለ ብቸኝነት
ወዴትም የማይሄድ ፥ ዝም ብሎ የሚራመድ
እንኳንስ ሰውና ፥ ልቡ ያልሆነው ዘመድ
ጭር ያለ ባይተዋር
በሰው ጎርፍ መሐል
ትንፋሹ የሚታየው
እርምጃ የሚመትር
ጠብታ የሚቆጥር
ወዴትም ሳንርቅ ፥ እዚሁ አፍንጫችን
እዚሁ ልባችን ስር
አለ ብቸኝነት ።
By HAB HD
@getem
@getem
@paappii
[የሌሊት ራዕይ....]
🌟
አሮጊት ኮከቦች....
እንደ ፍም አብርተው....
ከሌሊቱ ሰማይ— ረከቦት ሰርተው ፤
(ነጭ ጉም — ስኒ ዘርግተው ፤)
በጨለማ በራድ — በድቅድቅ ጀበና
(ከሩቅ ተጠራርተው ይሰበሰቡና....)
ያፈላሉ — ቡና ።
🌟
በስብሰባው መሀል....
አቦል እየጠጡ — ጨረቃን ያሟታል ፤
(እንደዚህ ይሏታል....)
“አብራን እየኖረች እኛን ያልመሰለች
ከህብረት ከቡድን የተገነጠለች
ይቺ ' ቅርፀ ጥፉ ' የተድቦለቦለች....!”
🌒
እሷም ትሰማለች...
(ጎረቤት አይደለች?!)
መልኳ ያስጠላታል ፤
እንደ`ነሱ ሆና...
(ያፈሉትን ቡና...)
መጠጣት ይምራታል ።
(ቀረብ ትላለች....)
“አምራለሁ ብላ ነው ከእኛ መለየቷ?!
እኛን ለመብለጥ ነው ገዝፋ መታየቷ?!”
(ሲሉ ትሰማለች...)
አንገት ትደፋለች ....
(ብቻዋን አይደለች!?)
ሀሜት ይሰብራታል
አንሳ ትጠፋለች ።
🌒
[በራስ መንገድ መቆም ...
የሚያኖር አይደለም ፥
መንጋ መልቀቅ የለም!
'መለየት'-- 'ማፈንገጥ' ...
በሆነበት ዓለም...
በልዩነት መኖር — መቼ ይወደዳል!?
የህላዌ ህጉ — መምሰል ያስገድዳል ።]
🌒
(እኒህ አሮጊቶች....)
ሽሙጥ ሀሜታቸው በርዶ ካላበቃ ፤
ተፈጥሮ ስሪቷን
(ልዩ ማንነቷን)
ገላዋን አውልቃ ፤
ኮከብ ትሆናለች — አንድቀን ጨረቃ ።
_
ህዳር ፳፮—፪፼፲፮ ዓ.ም
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
🌟
አሮጊት ኮከቦች....
እንደ ፍም አብርተው....
ከሌሊቱ ሰማይ— ረከቦት ሰርተው ፤
(ነጭ ጉም — ስኒ ዘርግተው ፤)
በጨለማ በራድ — በድቅድቅ ጀበና
(ከሩቅ ተጠራርተው ይሰበሰቡና....)
ያፈላሉ — ቡና ።
🌟
በስብሰባው መሀል....
አቦል እየጠጡ — ጨረቃን ያሟታል ፤
(እንደዚህ ይሏታል....)
“አብራን እየኖረች እኛን ያልመሰለች
ከህብረት ከቡድን የተገነጠለች
ይቺ ' ቅርፀ ጥፉ ' የተድቦለቦለች....!”
🌒
እሷም ትሰማለች...
(ጎረቤት አይደለች?!)
መልኳ ያስጠላታል ፤
እንደ`ነሱ ሆና...
(ያፈሉትን ቡና...)
መጠጣት ይምራታል ።
(ቀረብ ትላለች....)
“አምራለሁ ብላ ነው ከእኛ መለየቷ?!
እኛን ለመብለጥ ነው ገዝፋ መታየቷ?!”
(ሲሉ ትሰማለች...)
አንገት ትደፋለች ....
(ብቻዋን አይደለች!?)
ሀሜት ይሰብራታል
አንሳ ትጠፋለች ።
🌒
[በራስ መንገድ መቆም ...
የሚያኖር አይደለም ፥
መንጋ መልቀቅ የለም!
'መለየት'-- 'ማፈንገጥ' ...
በሆነበት ዓለም...
በልዩነት መኖር — መቼ ይወደዳል!?
የህላዌ ህጉ — መምሰል ያስገድዳል ።]
🌒
(እኒህ አሮጊቶች....)
ሽሙጥ ሀሜታቸው በርዶ ካላበቃ ፤
ተፈጥሮ ስሪቷን
(ልዩ ማንነቷን)
ገላዋን አውልቃ ፤
ኮከብ ትሆናለች — አንድቀን ጨረቃ ።
_
ህዳር ፳፮—፪፼፲፮ ዓ.ም
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ስንኩልኩል ተራማጅ በኃጥያት ቦይ ፈሳሽ
ቀና ብዬ ማላይ የህይወቴን ቀያሽ፤
እንደነገሩ ሂያጅ
እንዳሻኝ ወራጅ
ነጥዬ ማላውቅ ጠላት እና ወዳጅ፡
ስንፏቀቅ የምኖር ውድቀት ተንተርሼ
ዘመኔን የበላሁ
ራሴን የጎዳሁ አዳኜን ነክሼ።
የእውር ድንብር ተጓዥ ስንኩልኩል ወልካፋ
እየሄድኩ አልነበር ራሴን ላስጠፋ
ታዲያ እንዴት ተረፍኩ?
እስትንፋስን ታቀፍኩ?
መውደቂያዬን ሚያቆም መጥፊያዬን ሚያድን
ምን ነበር እኔጋ ፈዋሽ የቁም በድን?
ምንም!
ማንም!
እንዴ...
ወይ ጉዴ
ረስቼህ አልነበር ... እንዴት አስታወስከኝ
ንቀት ግፌን ትተህ እንደምን ታደግከኝ
ጥል ምርኩዝ ሲጥለኝ እንደምን ደገፍከኝ።
እንዴት ታዘዘልህ ክንፍህ እኔን ሊጋርድ
ገፍትሬህ አይደለ እንዲህ ምንገዳገድ።
ሚካኤል አባቴ
ጉዞዬ ወደ ምሬት መንገዴ ወደ ሞት
የት አግኝተህ ቀየርክ የኔን ስብር ህይወት
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
ቀና ብዬ ማላይ የህይወቴን ቀያሽ፤
እንደነገሩ ሂያጅ
እንዳሻኝ ወራጅ
ነጥዬ ማላውቅ ጠላት እና ወዳጅ፡
ስንፏቀቅ የምኖር ውድቀት ተንተርሼ
ዘመኔን የበላሁ
ራሴን የጎዳሁ አዳኜን ነክሼ።
የእውር ድንብር ተጓዥ ስንኩልኩል ወልካፋ
እየሄድኩ አልነበር ራሴን ላስጠፋ
ታዲያ እንዴት ተረፍኩ?
እስትንፋስን ታቀፍኩ?
መውደቂያዬን ሚያቆም መጥፊያዬን ሚያድን
ምን ነበር እኔጋ ፈዋሽ የቁም በድን?
ምንም!
ማንም!
እንዴ...
ወይ ጉዴ
ረስቼህ አልነበር ... እንዴት አስታወስከኝ
ንቀት ግፌን ትተህ እንደምን ታደግከኝ
ጥል ምርኩዝ ሲጥለኝ እንደምን ደገፍከኝ።
እንዴት ታዘዘልህ ክንፍህ እኔን ሊጋርድ
ገፍትሬህ አይደለ እንዲህ ምንገዳገድ።
ሚካኤል አባቴ
ጉዞዬ ወደ ምሬት መንገዴ ወደ ሞት
የት አግኝተህ ቀየርክ የኔን ስብር ህይወት
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
#ህመም_አሞኝ_ያውቃል!
የሚያስጨንቅ የሚከፋ
አለ ሲሉት የሚጠፋ
የለም ሲሉት አለው የሚል
ስቃይ ሲሉት ደስ ደስ የሚል
የሚያደቀኝ በስልብ ቃል
ህመም ሚሉት አሞኝ ያውቃል።
#በድኔንም_ልክ_እንደዛው!
ያወሩኝ 'ለት አልነበርኩም
ሲጠላልፉኝ አልወደኩም
አታለሉኝ በመሃል ላይ በድን በድን በሚለው ቃል
አዎን ልክ እንደዛው...በድኔንም አሞኝ ያውቃል።
#እራሴንም_ምታት_መታው!
ስንለያይ ስትጨክን በጌታ ቃል ተማምላ
ከቆምኩበት ጥላኝ ስትሄድ ስትመልሰኝ ወደኋላ
ጭንቀት ቢጤ ሲጫርብኝ አስጨፍነው ለሚቀብሩት
ራሴንም ምታት ነገር ጠጋ ብለው አወራሩት።
#ማመኔንም_እምነት_ነሳው!
"አፈቀርኩህ" ስትል "አፈቀርኩሽ" ያልኳት
"ትበልጣለህ" ስትል በጭፍን ያመንኳት
ሳወራላት ስኖር የሚቆጨኝን ቃል
ማመኔንም አሞኝ ያውቃል።
#ህይወቴንም_አሞኝ_ነበር!
አጨብጭቤ ያስጨበትኳት
ስጦታ ነው ብዬ የላኳት
የሚሰማኝ እየጫረ
ከጓድ በላይ እኔን ለኔ የመከረ
ህይወቴንም ታምሜ ነበረ።
#ህሊናዬን_ጎድቻለሁ!
ወሰንኩና ውሳኔዎች ተናገርኳት እስኪበቃት
የተጠጋት ቆሌ መንፈስ ካጠገቧ እስኪርቃት
ተናደድኩኝ ከልክ በላይ አናደድኳት ልክ እንደኔው
ህሊናዬን ጎድቻለው በንዴት ቃል እኔው ለኔው።
የድባቴ መንፈስ ሲከናነብ አካላቴን
እንባ ሚሉት ውሃ ተናንቆት ህይወቴን
ገደል ገደል ሚያስመኝ የክፉ መንፈስ ቃል
#ተፈጥሮዬም_ታሞ_ያውቃል!
#mikiyas_feyisa
ዮኒ
ኣታን @yonatozz
@getem
@getem
@getem
የሚያስጨንቅ የሚከፋ
አለ ሲሉት የሚጠፋ
የለም ሲሉት አለው የሚል
ስቃይ ሲሉት ደስ ደስ የሚል
የሚያደቀኝ በስልብ ቃል
ህመም ሚሉት አሞኝ ያውቃል።
#በድኔንም_ልክ_እንደዛው!
ያወሩኝ 'ለት አልነበርኩም
ሲጠላልፉኝ አልወደኩም
አታለሉኝ በመሃል ላይ በድን በድን በሚለው ቃል
አዎን ልክ እንደዛው...በድኔንም አሞኝ ያውቃል።
#እራሴንም_ምታት_መታው!
ስንለያይ ስትጨክን በጌታ ቃል ተማምላ
ከቆምኩበት ጥላኝ ስትሄድ ስትመልሰኝ ወደኋላ
ጭንቀት ቢጤ ሲጫርብኝ አስጨፍነው ለሚቀብሩት
ራሴንም ምታት ነገር ጠጋ ብለው አወራሩት።
#ማመኔንም_እምነት_ነሳው!
"አፈቀርኩህ" ስትል "አፈቀርኩሽ" ያልኳት
"ትበልጣለህ" ስትል በጭፍን ያመንኳት
ሳወራላት ስኖር የሚቆጨኝን ቃል
ማመኔንም አሞኝ ያውቃል።
#ህይወቴንም_አሞኝ_ነበር!
አጨብጭቤ ያስጨበትኳት
ስጦታ ነው ብዬ የላኳት
የሚሰማኝ እየጫረ
ከጓድ በላይ እኔን ለኔ የመከረ
ህይወቴንም ታምሜ ነበረ።
#ህሊናዬን_ጎድቻለሁ!
ወሰንኩና ውሳኔዎች ተናገርኳት እስኪበቃት
የተጠጋት ቆሌ መንፈስ ካጠገቧ እስኪርቃት
ተናደድኩኝ ከልክ በላይ አናደድኳት ልክ እንደኔው
ህሊናዬን ጎድቻለው በንዴት ቃል እኔው ለኔው።
የድባቴ መንፈስ ሲከናነብ አካላቴን
እንባ ሚሉት ውሃ ተናንቆት ህይወቴን
ገደል ገደል ሚያስመኝ የክፉ መንፈስ ቃል
#ተፈጥሮዬም_ታሞ_ያውቃል!
#mikiyas_feyisa
ዮኒ
ኣታን @yonatozz
@getem
@getem
@getem
አምላኬ
አይኖችሽ ይሉኛል እንደምትወጂኝ
አፍሽ ይነግረኛለ እንደማትወጂኝ
ታድያ የቱን ልመን
አፍሽ አዬገፋኝ አይንሽ ሲጎትተኝ
ልብሽ ምን እንደሚል ማወቅ ሲያዳግተኝ
ልቤን ልመን ይሆን ?
ልቤ የሚለኝን ወደ አምላክ ቅረብ
አንድት እፁብ ለምን ድልድይህን ጥረብ
ስትራምድ እንዳይጎዳህ ስትሻገር ወደ እሷ
መለያዬት እንዲያከትም ተጓዝ ወደ ነፍሷ
ከአንድ ልብ አንድ ነፍስ እንዲያጣምርህ
ተጠጋ ወደ አላህ ቅረብ ወደ እግዜርህ
ይለኛል
አምላኬ
ታነብልኚ ይሆን የአይኖቿን ሚስጥር
ሰብረህ ትገባለህ ወደ ልቧ ቅጥር?
አምላኬ
By kerim
@getem
@getem
@getem
አይኖችሽ ይሉኛል እንደምትወጂኝ
አፍሽ ይነግረኛለ እንደማትወጂኝ
ታድያ የቱን ልመን
አፍሽ አዬገፋኝ አይንሽ ሲጎትተኝ
ልብሽ ምን እንደሚል ማወቅ ሲያዳግተኝ
ልቤን ልመን ይሆን ?
ልቤ የሚለኝን ወደ አምላክ ቅረብ
አንድት እፁብ ለምን ድልድይህን ጥረብ
ስትራምድ እንዳይጎዳህ ስትሻገር ወደ እሷ
መለያዬት እንዲያከትም ተጓዝ ወደ ነፍሷ
ከአንድ ልብ አንድ ነፍስ እንዲያጣምርህ
ተጠጋ ወደ አላህ ቅረብ ወደ እግዜርህ
ይለኛል
አምላኬ
ታነብልኚ ይሆን የአይኖቿን ሚስጥር
ሰብረህ ትገባለህ ወደ ልቧ ቅጥር?
አምላኬ
By kerim
@getem
@getem
@getem
¹
“ግፋ” ብለኸው — እግርህን
እያፈስስከው — ላብህን
ስታሯሩጣት — ወደ ፊት...
(ስትከተላት ህልምህን ...)
አሁን ግን በቃህ — ደክሞሃል
አየሁህ መንገድ — ወድቀሃል ።
•
“በርታ - ተነስ” — አልልህም
“” ደግመህ ሩጥ” — አልልህም
(“ውደቅ እረፍ” — ግዴለህም ።)
♟️
ያቺን ብሩህ ጊዜ...
(ያቺን ፍፁም ደስታ....)
ሮጠህ ብታጣት፤
ወድቀህ ፋታ ስጣት ።
(ወይም ደግሞ ቆመህ
በሩቅ ተመልከታት....)
ወዴትም አትሄድም....
ክብ ነው መሮጫው.....
(ምድርስ ክብ አይደለች?!)
ት ደ ር ስ ል ሃ ለ ች — ባትደርስባትም ፤
ወደ ፊት መሄድ ነው — እርምጃ መግታትም።
---
(አትልፋ ደጋግመህ ....)
እጅ ስጥ ግዴለም — “በቃኝ” በል አንዳንዴ ፤
ተስፋ ካልቆረጡት — ይቀጠላል እንዴ ?!
♟️
[ተራራ ሲገፉ....
ወደ ላይ ሲከንፉ...
ሰማይ የፈለጉት...
መሬት ወድቆ እንደሆን
መች ያስተውሉታል !?
(ዕድሜ ይስጠው ድካም)
ሲሮጡ ያጡትን — ሲያርፉ ያገኙታል ። ]
——
²
አንተም ወዳጄ ምስኪኑ እረኛ ፤
(ፍሬ ለማውረድ....)
መዝለልህ ይብቃ....
ዛፉ ስር ተኛ ።
•
(መተው መልካም ነው....)
“አልቻልኩም” ማለት ያስችልልሃል ፤
(ሽቅብ ወደ ላይ ስትንጠራራ...)
ያልደረስክበት ጣፋጩ ፍሬ....
ሲበስል መሬት — ይወድቅልሃል ።
“ተነስ” — አልልህም...
“ሩጥ” — አልልህም....
“እረፍ” — ግዴለህም ።
_
@Bekalushumye
ታህሳስ ፪ — ፳፲፮ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
“ግፋ” ብለኸው — እግርህን
እያፈስስከው — ላብህን
ስታሯሩጣት — ወደ ፊት...
(ስትከተላት ህልምህን ...)
አሁን ግን በቃህ — ደክሞሃል
አየሁህ መንገድ — ወድቀሃል ።
•
“በርታ - ተነስ” — አልልህም
“” ደግመህ ሩጥ” — አልልህም
(“ውደቅ እረፍ” — ግዴለህም ።)
♟️
ያቺን ብሩህ ጊዜ...
(ያቺን ፍፁም ደስታ....)
ሮጠህ ብታጣት፤
ወድቀህ ፋታ ስጣት ።
(ወይም ደግሞ ቆመህ
በሩቅ ተመልከታት....)
ወዴትም አትሄድም....
ክብ ነው መሮጫው.....
(ምድርስ ክብ አይደለች?!)
ት ደ ር ስ ል ሃ ለ ች — ባትደርስባትም ፤
ወደ ፊት መሄድ ነው — እርምጃ መግታትም።
---
(አትልፋ ደጋግመህ ....)
እጅ ስጥ ግዴለም — “በቃኝ” በል አንዳንዴ ፤
ተስፋ ካልቆረጡት — ይቀጠላል እንዴ ?!
♟️
[ተራራ ሲገፉ....
ወደ ላይ ሲከንፉ...
ሰማይ የፈለጉት...
መሬት ወድቆ እንደሆን
መች ያስተውሉታል !?
(ዕድሜ ይስጠው ድካም)
ሲሮጡ ያጡትን — ሲያርፉ ያገኙታል ። ]
——
²
አንተም ወዳጄ ምስኪኑ እረኛ ፤
(ፍሬ ለማውረድ....)
መዝለልህ ይብቃ....
ዛፉ ስር ተኛ ።
•
(መተው መልካም ነው....)
“አልቻልኩም” ማለት ያስችልልሃል ፤
(ሽቅብ ወደ ላይ ስትንጠራራ...)
ያልደረስክበት ጣፋጩ ፍሬ....
ሲበስል መሬት — ይወድቅልሃል ።
“ተነስ” — አልልህም...
“ሩጥ” — አልልህም....
“እረፍ” — ግዴለህም ።
_
@Bekalushumye
ታህሳስ ፪ — ፳፲፮ ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
¹
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች ....
(መውደድ በእነሱ ያምራል )
በልዑላኑ — በሀያላኑ —
በንጉሦቹ ፤
(በፈላጭ በቆራጮቹ )
ጊዜም ስልጣንም ባላቸው ፤
ሁሉን በሚቻላቸው ።
(እንደ እኔ አይደሉም እነሱ....)
የልብን መሻት ይሞላሉ ....
እንባን ማበስ ይችላሉ ....
(ለሚጠሉት ባይሆን እንኳን )
ለሚወዱት ይደርሳሉ ።
(ለምን ወደድኩሽ እኔ ግን?)
“መውደድ” (የንጉሥ ዘመድ)
በባሪያ ልብ ምን ይሰራል?
ላፈቀሩት ካልደረሱ ....
ማፍቀር ብቻ ምኑ ያምራል?
•
ባይሽም በእሳት መካከል
ባለጊዜ ሲያንገላታሽ
ቢሰማኝ ጩኸት እሪታሽ
አድንሽ ዘንድ ....
(አተርፍሽ ዘንድ )
አቅመቢስ ነኝ ድኩም ባሪያ
ስስ ጉልበቴ አንሶብኛል ፤
ታዲያ ....
(“ደረስኩልሽ” ማለት አቅቶኝ)
“ወደድኩሽ” ብል ያምርብኛል?
•
ለወደዱት አካል ለወደዱት ገላ ....
ለመድረስ የሚችል ከሌለበት አቅም
ያሳምማል እንጂ መውደድ ምን ሊጠቅም?
ካላበስኩልሽ እንባሽን
ካላከምኩት ህመምሽን
ካላተርፍኩት....
ቆሜ ካየሁት ልብሽ ሲሰበር ፤
ባልወድሽ ይሻለኝ ነበር ።
²
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች....
(መውደድ ያምራል በእነሱ ፤)
ቀላል ነው እንባ ማበሱ ፤
(ላፈቀሩት ሰው መድረሱ ። )
ጌታም ራሱ ሁሉን የሚችል....
(የማርያም ልጇ) የዓለም ንጉሥ ነው
ስለመውደዱ ተሰቅሎ ያልፋል ፤
ደሙን አፍስሶ ፍቅሩን ያተርፋል ፤
ሞቱ እንኳን ሚዛን ይደፋል ።
(ታውቂያለሽ ይሄንን)
የንጉሥ ነው እንጂ
የጌታ ነው እንጂ
ምንም ለውጥ የለውም
(ተዓምር አይፈጥርም ) የአንድ ባሪያ መጉደል
እኔ ብሞትልሽ አትተርፊም አይደል !?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች ....
(መውደድ በእነሱ ያምራል )
በልዑላኑ — በሀያላኑ —
በንጉሦቹ ፤
(በፈላጭ በቆራጮቹ )
ጊዜም ስልጣንም ባላቸው ፤
ሁሉን በሚቻላቸው ።
(እንደ እኔ አይደሉም እነሱ....)
የልብን መሻት ይሞላሉ ....
እንባን ማበስ ይችላሉ ....
(ለሚጠሉት ባይሆን እንኳን )
ለሚወዱት ይደርሳሉ ።
(ለምን ወደድኩሽ እኔ ግን?)
“መውደድ” (የንጉሥ ዘመድ)
በባሪያ ልብ ምን ይሰራል?
ላፈቀሩት ካልደረሱ ....
ማፍቀር ብቻ ምኑ ያምራል?
•
ባይሽም በእሳት መካከል
ባለጊዜ ሲያንገላታሽ
ቢሰማኝ ጩኸት እሪታሽ
አድንሽ ዘንድ ....
(አተርፍሽ ዘንድ )
አቅመቢስ ነኝ ድኩም ባሪያ
ስስ ጉልበቴ አንሶብኛል ፤
ታዲያ ....
(“ደረስኩልሽ” ማለት አቅቶኝ)
“ወደድኩሽ” ብል ያምርብኛል?
•
ለወደዱት አካል ለወደዱት ገላ ....
ለመድረስ የሚችል ከሌለበት አቅም
ያሳምማል እንጂ መውደድ ምን ሊጠቅም?
ካላበስኩልሽ እንባሽን
ካላከምኩት ህመምሽን
ካላተርፍኩት....
ቆሜ ካየሁት ልብሽ ሲሰበር ፤
ባልወድሽ ይሻለኝ ነበር ።
²
ፍቅርንስ ያፍቅሯት ጌቶች....
(መውደድ ያምራል በእነሱ ፤)
ቀላል ነው እንባ ማበሱ ፤
(ላፈቀሩት ሰው መድረሱ ። )
ጌታም ራሱ ሁሉን የሚችል....
(የማርያም ልጇ) የዓለም ንጉሥ ነው
ስለመውደዱ ተሰቅሎ ያልፋል ፤
ደሙን አፍስሶ ፍቅሩን ያተርፋል ፤
ሞቱ እንኳን ሚዛን ይደፋል ።
(ታውቂያለሽ ይሄንን)
የንጉሥ ነው እንጂ
የጌታ ነው እንጂ
ምንም ለውጥ የለውም
(ተዓምር አይፈጥርም ) የአንድ ባሪያ መጉደል
እኔ ብሞትልሽ አትተርፊም አይደል !?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
አሚን አሚን አሚን
እስኪ ልነሳና እንዝርቴን ላስላዉ
ምን ያቦዝነዋል ፈትሎ አዳሪ ሰዉ
እንደ ጊዜው ክፋት
እንደሰዉ ክዳት
እንደኔ አንድ መሆን
ምን ይበጀኝ ነበር አንተ ከኔ ባትሆን።
የዘመናችን ሰው ምንኛ ተጎዳ
በአፉ እየወደደ በሆዱ እየከዳ፤
እኔማ ረግሜ ምንኛ ልጎዳው
እሱም ይውደድና ያመነው ሰው ይክዳው።
አሚን አሚን እማዋየው አሚን
ጌትዬ እጄን አውዛው
እጁ የወዛ ነው ሚዜው የሚበዛው።
የወሎ ደመና አይጥልም ከየጁ
ገልግለኝ ህመሜን ከነእግዴ ልጁ።
ብሶቴ ችግሬ ገለል በል ከፊቴ
እግሬን ልዘርጋበት
አሞኛል ጉልበቴን የኮረተምኩበት።
አቤት አቤት አቤት
እማማ ዚነት🖤
@getem
@getem
እስኪ ልነሳና እንዝርቴን ላስላዉ
ምን ያቦዝነዋል ፈትሎ አዳሪ ሰዉ
እንደ ጊዜው ክፋት
እንደሰዉ ክዳት
እንደኔ አንድ መሆን
ምን ይበጀኝ ነበር አንተ ከኔ ባትሆን።
የዘመናችን ሰው ምንኛ ተጎዳ
በአፉ እየወደደ በሆዱ እየከዳ፤
እኔማ ረግሜ ምንኛ ልጎዳው
እሱም ይውደድና ያመነው ሰው ይክዳው።
አሚን አሚን እማዋየው አሚን
ጌትዬ እጄን አውዛው
እጁ የወዛ ነው ሚዜው የሚበዛው።
የወሎ ደመና አይጥልም ከየጁ
ገልግለኝ ህመሜን ከነእግዴ ልጁ።
ብሶቴ ችግሬ ገለል በል ከፊቴ
እግሬን ልዘርጋበት
አሞኛል ጉልበቴን የኮረተምኩበት።
አቤት አቤት አቤት
እማማ ዚነት🖤
@getem
@getem