FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.6K photos
32 videos
9 files
8.48K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
150 የሸኔ አባላት በተደረገላቸው የሠላም ጥሪ መሰረት በሰላማዊ መንገድ እጅ ሰጡ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የደቡብ ዕዝ ኮር ግዳጅ እየተወጣበት በሚገኘው ምዕራብ ጉጅ ዞን 150 የሸኔ አባላት የተደረገላቸውን የሠላም ጥሪ በመቀበል በሰላማዊ መንገድን እጅ ሰጥተዋል፡፡

የደቡብ ዕዝ ኮር ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሎኔል አባዲ ልዑል፣ የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አዶላ ሂርጳዬ ፣የዞንና የወረዳ አመራሮች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እጅ ለሰጡ የሸኔ አባላት አቀባበል አድርገዋል።

የኮሩ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሎኔል አባዲ ልዑል፣ እና የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አዶላ ሂርጳዬ፣
በሠላማዊ መንገድ እጅ የሠጡ የሸኔ አባላት ሠላም መርጠው እና የሠላም ጥሪውን ተቀብለው መግባታችው ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ ለሠላም መሥራት እንደሚገባቸው አመላክተዋል።

በሰላማዊ መንገድ የገቡት የሸኔ አባላትም እስካሁን ድረስ በሀገር እና በህዝብ ላይ ለፈፀሙት ያልተገባ ድርጊት መፀፀታቸውን ገልፀው ከእንግዲህ ሠላምን የማሥቀደም ሥራ እንደሚሠሩና ለሠላም እንደሚቆሙ ተናግረዋል፡፡

በዕለቱ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የሠራዊቱ አመራሮች አባገዳዎች የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። ዘገባው የኮሩ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
52👏12👍8🕊6🔥2🫡1
ዝግጁነቱን ያረጋገጠና በጠንካራ ስነ-ልቦና የተገነባ  ሠራዊት ተልዕኮዉን ለመፈጸም አስተማማኝ ነው።
‎     ሌተናል ጀኔራል መሰለ መሰረት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

‎የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሰለ መሰረት በቴዎድሮስ ኮር አንድ ክፍለጦር በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ተገኝተዉ  አጠቃላይ የወትሮ ዝግጁነት እና የግዳጅ አፈፃፀም የመስክ ምልከታ ባደረጉበት ወቅት ዝግጁነቱን ያረጋገጠና በጠንካራ ስነ-ልቦና የተገነባ  ሠራዊት ሀገራዊ ተልዕኮዉን ለመፈጸም አስተማማኝ  መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዋና አዛዡ ሠራዊታችን ከህዝብ የወጣ ለህዝብ የሚኖር እና ለህዝብ የሚሞት፣ አላማውን የማይሸጥ፣ ሃላፊነቱን የማይዘነጋ፣ ለህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ የታመነ በተቋማዊ እሴቶች ብቻ የሚመራ የሰላም እና የልማት ሃይል ነው ብለዋል።

‎አገርን መውደድ መዳረሻው ለሀገር ሰላም መስዋዕትነት መክፈል በመሆኑ በሰራዊታችን ዘንድ ሁሌም የሚፈፀም ሃቅና ተግባር ነው ያሉት ሌተናል ጀኔራል መሰለ መሰረት፤ የነፃነት ተምሳሌት የሆነችውን አገራችን ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ ማሻገር በሚችል በደማቅ መስዋዕትነት የህዝቦችን ዘላቂ ሰላም በማፅናት የአገሩን ሉዓላዊነትና ደህንነት እያስከበረ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።

‎የክፍለጦሩ የሠራዊት አባላት የኢትዮጵያን ሠላም ለማናጋት ሌት ተቀን በሚያሴሩ ፀረ ሰላም ሃይሎች ላይ ፈጣን ምላሽ በመስጠት የሚታወቅ ድል አድራጊ የህዝብ ልጅ መሆኑን የገለፁት ጀኔራል መኮንኑ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንቅፋት የሆነው አሸባሪው ሸኔ ላይ እርምጃ በመውሰድ ዞኖችን፣ ወረዳዎችን እና ቀበሌዎችን ከሸኔ በማፅዳት ህዝቡ በነፃነት ተንቀሳቅሶ ሰርቶ መግባት እንዲችል ከፍተኛ ሚና የተጫወተ ክፍለጦር መሆኑን ገልፀዋል።  

ዝግጁነቱን ያረጋገጠና በጠንካራ ስነ-ልቦና የተገነባ  ሠራዊት ሀገራዊ ተልዕኮዉን ለመፈጸም አስተማማኝ በመሆኑ በየትኛዉም ሁኔታ ዉስጥ እየተዋጋና እየሰለጠነ በተሰማራባቸው የግዳጅ ቀጠናዎች ሁሉ ጠንካራ አሃድን በስልጠና በማብቃት የማድረግ አቅሙን በየጊዜው በተግባር እያረጋገጠ የሚሰጠውን ማንኛውም ግዳጅ በጀግንነት በመፈፀም ዘላቂ ሰላም በማምጣት ኢትዮጵያን ማፅናት ከሁሉም የሠራዊታችን አመራርና አባላት ይጠበቃል ብለዋል።

‎ዘጋቢ ጋብዘው ዳና
‎ፎቶ ግራፍ ጋብዘው ዳና

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
19👏10👍6🔥2🏆1
መቻል ሶስት ወሳኝ ተጫዋቾችን ሲያስፈርም የግብ ጠባቂውን ውል አራዝሟል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

መቻል እግር ኳስ ቡድን ሶስት ወሳኝ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ ሲያሥፈርም የግብ ጠባቂውን ውል አራዝሟል።

የመጀመሪያ ፈራሚው በወላይታ ዲቻ በቅዱስጊዮርጊስ እና ያለፈውን ሁለት አመታት በጣና ሞገዶቹ ባህርዳር ከተማ ጥሩ ጊዜን ማሳለፍ የቻለው እና ለብሄራዊ ቡድን ግልጋሎት እየሠጠ የሚገኘው የመስመር አጥቂው ቸርነት ጉግሳ ለመቻል ፊርማውን አኑሯል።

ሁለተኛው በቅዱስ ጊዮርጊስ እና በባህርዳር ከተማ በተጠናቀቀው የውድድር አመት ለመቐለ 70 እንደርታ ሲጫወት ያሳለፈው የመሀል ሜዳ ተጫዋቹ የአብስራ ተስፋዬ ለመቻል ፈርሟል።

ላለፉት ሶስት አመታት በሀዲያ ሆሳዕና ቤት ምርጥ ብቃቱን በማሳየት ብሄራዊ ቡድን በተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበለት ሲጫወት የቆየው የተከላካይ አማካይ ብሩክ ማርቆስ ለማቻል ሶስተኛ ፈራሚ ሆኗል።

ያለፉትን ሁለት አመታት ለመቻል ግልጋሎቱን ሲሰጥ የቆየው ግብ ጠባቂው ውብሸት ጭላሎ በመቻል ለመቆየት ውሉን አራዝሟል። ዘጋቢ ገረመው ጨሬ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
30👍4👎2🔥2
በተለያዬ አካባቢ የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ደም ለግሰዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የሁርሶ እጩ መኮነን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮችና ዕጩ መኮነን ሠልጣኞቾ፣ የደቡብ ዕዝ ኮር የሠራዊት አባላት እና የ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር የሠራዊት አባላት በፈቃደኝነት ደም ለግሰዋል።

የሁርሶ እጩ መኮነን ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ምክትል አዛዥ ለውጊያና ድጋፍ አገልግሎት ኮሎኔል ሙዞ ሸሪፋ የሚተካ ደም በመስጠት የማይተካ ህይወት ማዳን የሠራዊቱ አንዱ ተግባር በመሆኑ አጠናክረን በማስቀጠል የሰብአዊነት በጎ ተግባራችንን መወጣት ይገባናል ብለዋል።

የማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ የበሽታ መከላከል ሀላፊ  ሻለቃ አበራ ታደሰ በበኩላቸው  የደም ልገሳ በተለያየ ምክንያት የደም እጦት ለገጠማቸው ወገኖች በመድረስ ህይወትን ማስቀጠል በመሆኑ የሚያኮራ ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። ዘጋቢ ሜሮን ጌታነህ ናት

በተመሳሳይ የደቡብ ዕዝ ኮር ሰራዊት በደም እጥረት ምክንያት የሚጠፋዉን የሰው ህይወት እንታደግ በሚል መሪ ሃሳብ ለኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ አገልግሎት የምስራቅ ቦረና ዞን ቅርንጫፍ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ማድረጋቸውን የኮሩ 3ኛ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ሻለቃ ተረፈ ታደሰ ተናግረዋል።

የምስራቅ ቦረና ዞን ደም ባንክ ቅርንጫፍ ሃላፊ አቶ ዳርጌ ባርጩ በበኩላቸው፤ ሰራዊታችን ከግዳጁ ጎን ለጎን ደም በመለገስ የበርካታ ወገኖቻችንን ህይወት መታደግ እየቻለ መሆኑን አሥረድተዋል ዘጋቢ ፈይሳ መልካሙ ነው።

በተያያዘ የ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር የሠራዊት አባላት በመተከል ዞን ግልገል በለስ ሆስፒታል ደም መለገሳቸውን የክፍለጦሩ ጤና ማበልፀግና በሽታን መከላከል ሀላፊ ሻለቃ ጥላሁን ገዛሃኝ ሰማ ገልፀዋል።

ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር በሚለው እሴት መሠረት የክፍለጦሩ አባላት በተሠማሩበት የግዳጅ ቀጠና  ሠላምን ከማስፈን በተጓዳኝ በደም እጥረት ምክንያት  የሚሰቃዩ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ ደም እየለገሱ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዘገባው የተሾመ ወንደሰን ነው
‎    
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
32👍8👏2🔥1😁1💔1
የጥበቃ ብርጌዱ ተልዕኮውን በውጤት መፈፀም በሚያሥችለው አግባብ መገንባቱ ተገለፀ። 

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

‎የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል አብዱራህማን እስማኤል በውጊያና በተለያዩ ግዳጆች ደጀን በመሆን ከፍተኛ የሆነ ኮምቮይ 
‎እጀባና የዲፖዎችን ደህንነት የሚጠብቅ እንዲሁም ለተቋሙ ጋሻ የሆነ ጠንካራ የጥበቃ ብርጌድ መመሥረቱን ተናግረዋል።

‎የጥበቃ ብርጌድ አባላት አካባቢያችሁን ለስራ ውብና ማራኪ በማድረግ ላሳያችሁት ቁርጠኝነት እያመሠገንኩ በተመደባችሁት የስራ ዘርፈ ከመተግበርና ከማስተግበር ባሻገር በመስክ ስልታዊ እንቅስቃሴ ውጊያን መርቶ የመፈፀምና የማስፈፀም የላቀ ክህሎት መፍጠር መቻላችሁ የሚመሠገን ነው ብለዋል።

‎የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ የጥበቃ ብርጌድ አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ሁሴን ሀሠን በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ለመስራት የሚያስችል ሁለንተናዊ አቅም መፍጠር መቻሉን ገልፀው ተጣጣፊና ሁለገብ የሆነ ክፍል መገንባቱን አረጋግጠዋል።

‎በዕለቱ በሥራ አፈጻጸማቸው የላቀ ዉጤት ላስመዘገቡ  አባላት የምስጋና እና የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሂዷል።

‎ዘጋቢ ወርቅነህ ተስፋው
‎ፎቶግራፍ በድሩ መሀመድ

‎የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👏2214👍10🔥2