የምስራቅ ግንባር ሪፈራል ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥና የዝግጁነት ደረጃውን ማሳደጉ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
ማከም ፣ ማስተማር እና ማልማትን መሠረት አድርጎ እየሰራቸው ባሉት ተግባራት አመርቂ ውጤት መገኘታቸውን የምስራቅ ግንባር ሆስፒታል አዛዥ ኮሎኔል ብርሀኑ ዘውዱ ገልፀዋል።
ለምስራቅ ዕዝና በቀጠናው ለሚገኙ ማሰልጠኛዎችና ክፍሎች ለሚገኙ ሰራዊትና ቤተሰቡ ደረጃውን የጠበቀ የህከምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የገለፁት አዛዡ ለቀጠናው ነዋሪዎችም የህክምና አገልግሎቱን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልፀዋል።
ለዚህም የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ በየዘርፉ ያሉ የህክምና ባለሙያዎችንና ዘመናዊ መሳሪያዎችን ማሟላቱንና የሆስፒታሉን የመቀበል አቅም ከአንድ መቶ ሀያ ወደ ሶስት መቶ ሰው ተቀብሎ ለማስተናገድ እንዲችል ማድረጉንም ገልፀዋል።
ተቋሙ ወታደር የህክምና ባለሙያዎችን ለማፍራት እያደረገ ባለው ጥረት የሆስፒታሉ የህክምና ኮሌጅ የበኩሉን ጥረት እየተወጣ እንደሚገኝ የገለፁት የሆስፒታሉ አዛዥ ለዚህም ከመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሆስፒታሉን ውብ ፣ ፅዱና አረንጓዴ ከማድረግ ባለፈ ብዛት ያላቸው ሀገር በቀል ዛፎች፣ ቡና ፣ ፍራፍሬና አትክልት በማምረት ለሆስፒታሉ ማህበረሰብ ጥቅም እንዲሰጡ መደረጉንም ጠቁመዋል።
የሆስፒታሉን መሰረተ ልማት ይበልጥ ለማዘመን የተሰሩት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የገለፁት ኮሎኔል ብርሀኑ የሆስፒታሉን የሀይል ፍላጎት ለማሟላት ከድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ዞን በከፍተኛ ወጪ የኤሌክትሪክ መስመር በማያያዝ የሀይል ፍላጎት ማሟላታቸውና የጀነሬተር ነዳጅ ወጪ ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ በማስቀጠልና ለተቋሙ የህክምና ፍላጎት ስኬት የበኩላቸውን ለመወጣትም የተሟላ ቁመና ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
ለተገኘው ውጤት የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያና የምስራቅ ዕዝ አመራሮች ሚናም ከፍተኛ እንደሆነ ገልፀዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ በላቸው ካሳሁን
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
ማከም ፣ ማስተማር እና ማልማትን መሠረት አድርጎ እየሰራቸው ባሉት ተግባራት አመርቂ ውጤት መገኘታቸውን የምስራቅ ግንባር ሆስፒታል አዛዥ ኮሎኔል ብርሀኑ ዘውዱ ገልፀዋል።
ለምስራቅ ዕዝና በቀጠናው ለሚገኙ ማሰልጠኛዎችና ክፍሎች ለሚገኙ ሰራዊትና ቤተሰቡ ደረጃውን የጠበቀ የህከምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የገለፁት አዛዡ ለቀጠናው ነዋሪዎችም የህክምና አገልግሎቱን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልፀዋል።
ለዚህም የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ በየዘርፉ ያሉ የህክምና ባለሙያዎችንና ዘመናዊ መሳሪያዎችን ማሟላቱንና የሆስፒታሉን የመቀበል አቅም ከአንድ መቶ ሀያ ወደ ሶስት መቶ ሰው ተቀብሎ ለማስተናገድ እንዲችል ማድረጉንም ገልፀዋል።
ተቋሙ ወታደር የህክምና ባለሙያዎችን ለማፍራት እያደረገ ባለው ጥረት የሆስፒታሉ የህክምና ኮሌጅ የበኩሉን ጥረት እየተወጣ እንደሚገኝ የገለፁት የሆስፒታሉ አዛዥ ለዚህም ከመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሆስፒታሉን ውብ ፣ ፅዱና አረንጓዴ ከማድረግ ባለፈ ብዛት ያላቸው ሀገር በቀል ዛፎች፣ ቡና ፣ ፍራፍሬና አትክልት በማምረት ለሆስፒታሉ ማህበረሰብ ጥቅም እንዲሰጡ መደረጉንም ጠቁመዋል።
የሆስፒታሉን መሰረተ ልማት ይበልጥ ለማዘመን የተሰሩት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የገለፁት ኮሎኔል ብርሀኑ የሆስፒታሉን የሀይል ፍላጎት ለማሟላት ከድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ዞን በከፍተኛ ወጪ የኤሌክትሪክ መስመር በማያያዝ የሀይል ፍላጎት ማሟላታቸውና የጀነሬተር ነዳጅ ወጪ ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ በማስቀጠልና ለተቋሙ የህክምና ፍላጎት ስኬት የበኩላቸውን ለመወጣትም የተሟላ ቁመና ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
ለተገኘው ውጤት የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያና የምስራቅ ዕዝ አመራሮች ሚናም ከፍተኛ እንደሆነ ገልፀዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ በላቸው ካሳሁን
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
YouTube
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# የመከላከያ ሠራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
👍17❤12🔥2🥰1
በሩሲያ ሞስኮ ሥራዎቹን ሲያቀርብ የቆየው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ተመሠገነ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
በሩሲያ ሞስኮ የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ ተወዳጅ ሥራዎቹን ያቀረበው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ገነቱ ተሾመ እንዲሁም በሩሲያ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አታቼ ብርጋዲየር ጄኔራል ሀይሉ መኮንን የምስጋና እና የክብር አሸኛኘት አድርገውለታል።
አምባሳደር ዶክተር ገነቱ ተሾመ የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ አባላት የሁለቱን ሀገራት የ127 አመት ግንኙነት የበለጠና የደመቀ እንዲሆን ሥላደረጋችሁ ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል።
የሀገራችንን ድንቅ የሙዚቃ ባህል ለአለም ያሳያችሁ በስራዎቻችሁ ተወዳጅነትን ያተረፋችሁ በመሆኑ ኮርተንባችኋል ያሉት አምባሳደሩ በመዝጊያ ፕሮግራሙ ላይ ተጋብዤ የሀገሬ ስም ተደጋግሞ ሲጠራ በመሥማቴ ትልቅ ክብርና ኩራት ተሰምቶኛል ሲሉ አድናቆታቸውን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ እናንተን በዚህ ደረጃ አዘጋጅቶ አለም አቀፍ መድረክ ላይ እንድትሳተፉ በማድረጉ ላመሰግን እወዳለሁ ያሉት አምባሳደር ዶክተር ገነቱ ተሾመ የዚህ አይነት መድረኮች ለተቋምና ለሀገር ገፅታ ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ ስላላቸው አጠናክራችሁ መቀጠል ይኖርባችኋል ሲሉ ወደ ኢትዮጵያ መልካም ጉዞ ተመኝተውላቸዋል።
ሃምሳ አባላት ያሉትና የማርችንግ ባንድ የሙዚቃ ሥራውን በሩሲያ ሲያቀርብ የቆየው የማርችንግ ባንድ ቡድኑ ነገ ማክሰኞ ወደ ሀገሩ እንደሚመለስ ተገልጿል
በውብሸት ቸኮል
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
በሩሲያ ሞስኮ የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ ተወዳጅ ሥራዎቹን ያቀረበው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ገነቱ ተሾመ እንዲሁም በሩሲያ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አታቼ ብርጋዲየር ጄኔራል ሀይሉ መኮንን የምስጋና እና የክብር አሸኛኘት አድርገውለታል።
አምባሳደር ዶክተር ገነቱ ተሾመ የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ አባላት የሁለቱን ሀገራት የ127 አመት ግንኙነት የበለጠና የደመቀ እንዲሆን ሥላደረጋችሁ ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል።
የሀገራችንን ድንቅ የሙዚቃ ባህል ለአለም ያሳያችሁ በስራዎቻችሁ ተወዳጅነትን ያተረፋችሁ በመሆኑ ኮርተንባችኋል ያሉት አምባሳደሩ በመዝጊያ ፕሮግራሙ ላይ ተጋብዤ የሀገሬ ስም ተደጋግሞ ሲጠራ በመሥማቴ ትልቅ ክብርና ኩራት ተሰምቶኛል ሲሉ አድናቆታቸውን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ እናንተን በዚህ ደረጃ አዘጋጅቶ አለም አቀፍ መድረክ ላይ እንድትሳተፉ በማድረጉ ላመሰግን እወዳለሁ ያሉት አምባሳደር ዶክተር ገነቱ ተሾመ የዚህ አይነት መድረኮች ለተቋምና ለሀገር ገፅታ ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ ስላላቸው አጠናክራችሁ መቀጠል ይኖርባችኋል ሲሉ ወደ ኢትዮጵያ መልካም ጉዞ ተመኝተውላቸዋል።
ሃምሳ አባላት ያሉትና የማርችንግ ባንድ የሙዚቃ ሥራውን በሩሲያ ሲያቀርብ የቆየው የማርችንግ ባንድ ቡድኑ ነገ ማክሰኞ ወደ ሀገሩ እንደሚመለስ ተገልጿል
በውብሸት ቸኮል
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
YouTube
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# የመከላከያ ሠራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
❤26👍12🥰2🔥1
በሰሜን ሸዋ ዞን መርሀ-ቤቴ ወረዳ 62 የፅንፈኛ አባላት ከነ ትጥቃቸው እጅ ሰጡ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
በሰሜን ሸዋ ዞን መርሀ-ቤቴ ወረዳ በአፈዘዝ በርቃቶና በገረን ቀበሌ 62 የፅንፈኛው አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ለኮማንዶ ሬጅመንት እጅ መስጠታቸውን የአየር ወለድ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ሀይሌ ጥሩነህ ገልፀዋል።
የኮማንዶ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል ፀጋዬ ፍትዊ በበኩላቸው ህዝብን እና ሀገርን በማስቀደም የሰላም ጥሪ የሚቀበሉትን የፅንፈኛ አባላት በሙሉ እስከ አላችሁበት ድረስ ተጉዘን በክብር እየተቀበልን ነው ብለዋል።
ለሠላም ቆመን የአካባቢውን ሰላም በጋራ ማረጋገጥ አለብን በማለት እጅ ለሠጡ የቡድኑ አባላትም አስገንዝበዋል።
እጅ የሠጡ የፅንፈኛው አባላት በበኩላቸው በመንግስታችን ላይ ከመጀመሪያም ቅሬታ አልነበረንም እኛ ወደ ጫካ እንድንገባ የተገደድነው መንግስት የለም ፈርሷል ራሳችሁን አድኑ የሚል የፅንፈኛው ፕሮፖጋንዳ አሳስቶን ተቸግረን ነው ብለዋል።
ህዝባችን ይቅር ይበለን፤ ሌብነት፣ ዝርፊያ እና ወንጀል መስራትን የዘወትር ስራ ያደረጉት አሁንም እጅ መስጠት አልፈለጉም እንደ እኛ እጅ እስካልሰጡ ድረስ እኛ ከዛሬ ጀምሮ ከመንግስት ጎን ሆነን ታግለን እናጠፋቸዋለን ሲሉ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የፅንፈኛው አባላት ተናግረዋል።
ዘጋቢ ፈለቀ ዋሲሁን
ፎቶግራፍ አዲሱ አለሙ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
በሰሜን ሸዋ ዞን መርሀ-ቤቴ ወረዳ በአፈዘዝ በርቃቶና በገረን ቀበሌ 62 የፅንፈኛው አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ለኮማንዶ ሬጅመንት እጅ መስጠታቸውን የአየር ወለድ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ሀይሌ ጥሩነህ ገልፀዋል።
የኮማንዶ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል ፀጋዬ ፍትዊ በበኩላቸው ህዝብን እና ሀገርን በማስቀደም የሰላም ጥሪ የሚቀበሉትን የፅንፈኛ አባላት በሙሉ እስከ አላችሁበት ድረስ ተጉዘን በክብር እየተቀበልን ነው ብለዋል።
ለሠላም ቆመን የአካባቢውን ሰላም በጋራ ማረጋገጥ አለብን በማለት እጅ ለሠጡ የቡድኑ አባላትም አስገንዝበዋል።
እጅ የሠጡ የፅንፈኛው አባላት በበኩላቸው በመንግስታችን ላይ ከመጀመሪያም ቅሬታ አልነበረንም እኛ ወደ ጫካ እንድንገባ የተገደድነው መንግስት የለም ፈርሷል ራሳችሁን አድኑ የሚል የፅንፈኛው ፕሮፖጋንዳ አሳስቶን ተቸግረን ነው ብለዋል።
ህዝባችን ይቅር ይበለን፤ ሌብነት፣ ዝርፊያ እና ወንጀል መስራትን የዘወትር ስራ ያደረጉት አሁንም እጅ መስጠት አልፈለጉም እንደ እኛ እጅ እስካልሰጡ ድረስ እኛ ከዛሬ ጀምሮ ከመንግስት ጎን ሆነን ታግለን እናጠፋቸዋለን ሲሉ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የፅንፈኛው አባላት ተናግረዋል።
ዘጋቢ ፈለቀ ዋሲሁን
ፎቶግራፍ አዲሱ አለሙ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
YouTube
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# የመከላከያ ሠራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
👏34❤28👍7👎3🔥1🥰1
ሙሉጌታ ምህረት የመቻል እግር ኳስ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን ፈረመ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
ለ2018 የውድድር አመት ቡድኑን እያጠናከረ የሚገኘው የመቻል አዋቂ እግር ኳስ ቡድን ወጣቱን አሰልጣኝ ሙልጌታ ምህረትን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሹሟል።
ከአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ ጋር በስምምነት የተለያየው መቻል ያለፈውን አመት ሀዋሳ ከተማን ከወራጅ ቀጠና በማውጣት የዋንጫ ተፎካካሪ ማድረግ የቻለው እና በብዙ አሰልጣኞች እና አብረውት ከተጫወቱት ተጫዋቾች አመለ ሸጋው የሚባለው ሙልጌታ ምህረት በቀጣይ መቻልን ለማሠልጠን ተስማምቷል።
መቻል እግር ኳስ ቡድን ለ2018 የውድድር አመት ተቋሙን እና ክለቡን የሚመጥን ውጤት ለማስመዝገብ የዋና አሰልጣኝ እና ምክትል አሰልጣኝ እንዲሁም የቡድን መሪን ጨምሮ በርካታ ተጫዋቾችን በማስፈረም ለውድድር አመቱ ዝግጅቱን በቢሾፍቱ ከተማ ጀምሯል።
በገረመው ጨሬ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
ለ2018 የውድድር አመት ቡድኑን እያጠናከረ የሚገኘው የመቻል አዋቂ እግር ኳስ ቡድን ወጣቱን አሰልጣኝ ሙልጌታ ምህረትን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሹሟል።
ከአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ ጋር በስምምነት የተለያየው መቻል ያለፈውን አመት ሀዋሳ ከተማን ከወራጅ ቀጠና በማውጣት የዋንጫ ተፎካካሪ ማድረግ የቻለው እና በብዙ አሰልጣኞች እና አብረውት ከተጫወቱት ተጫዋቾች አመለ ሸጋው የሚባለው ሙልጌታ ምህረት በቀጣይ መቻልን ለማሠልጠን ተስማምቷል።
መቻል እግር ኳስ ቡድን ለ2018 የውድድር አመት ተቋሙን እና ክለቡን የሚመጥን ውጤት ለማስመዝገብ የዋና አሰልጣኝ እና ምክትል አሰልጣኝ እንዲሁም የቡድን መሪን ጨምሮ በርካታ ተጫዋቾችን በማስፈረም ለውድድር አመቱ ዝግጅቱን በቢሾፍቱ ከተማ ጀምሯል።
በገረመው ጨሬ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
YouTube
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# የመከላከያ ሠራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
❤29👍7😭1
የዘመናት ዕንባዋን ያበሰው የህዳሴ ግድብ ገድል
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ/ም
ከአውሮፓ እስከ መካከለኛው ምስራቅ ተንሰራፍቶ አይነቃነቄ የመሠለው የሮማ ኢምፖየር አይኗ ስር ሲፈራርስ በአርምሞ ታዝባለች።
የእነ ፔርሺያን አይነኬ ይባል የነበረ የጊዜው ሃያል ሀገራትን አካልሎ የዋጠ እናም የገዘፈ ግዛት እንክትክት ብሎ ሲወድቅ የተመለከተች ትዝታ ብዙ ነች። ኢትዮጵያ።
ከጥንት እስከ ዛሬ ስሟን አስጠብቃ ነበረች፣ አለች፣ ትኖራለች።
በሀገረ-መንግስት ግንባታ ታሪኳ ከዓለም ሀገራት አኳያ ጉምቱ ብትሰኝ የማይበዛባት ናት የሀገራት አንጋፋዋ ኢትዮጵያችን።
የዚህችን ቀልብ ሳቢና እምቅ ታሪኳ በቅጡ ያልተጠናላት ሚስጢረ-ብዙ ሀገርን ድብቅ እውነታ ለማወቅ የቋመጡ አውሮፓውያን በብዙ ስለመልፋታቸው ሀገራትንና ታሪካቸውን አሳሽ ነን ከሚሉቱ መካከል ጀምስ ብሩስን ማስታወስ በቂ ነው።
ኢትዮጵያ በአሁናዊዋ ሉላዊት /Global/ዓለማችንም አስፈላጊነቷና በወሳኝ ስትራቴጂክ አቀማመጧ ዓይን የሚጣልባት መሆኗ የቀጠለ ብቻ ሳይሆን መዓት ዋጋዎችን እያስከፈላት...ወሳኝ ብሄራዊ ጥቅሞቿን እንድታጣ መደረጓም አብሰልሳይ የታሪክ እውነታዋ ነው።
እኛ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከምንም በላይ አጽንኦት ሰጥተን ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ለሰከንድ የማናቅማማበት ጉዳይ ቢኖር...የውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ነው።
በስኬት ተጠናቆ በቅርቡ ለምርቃት ዝግጁ የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድባችን ዕውን እንዲሆን በጽናት የከፈልነውን ውድ መስዋዕትነት በኩራት የምናስታውሰው ብቻ ሳይሆን የግድቡ አርማታ ሲላቆጥ ውሃ ብቻ ሳይሆን የእኛም ደም እንደነበረበት ስናስብ ታላቅ ደስታ እየተሰማን ነው።
ለህላዌዋ ስለምንሞትላት ኢትዮጲያችን ብሄራዊ ጥቅም መረጋገጥ ለአፍታ የማንዘናጋ ከመሆናችንም በላይ የህዳሴው ግድብ ድል በቀይ ባህርም ተደግሞ የተነጠቅነው እውነታችን እንደሚመለስልን በልበ - ሙሉነት እናምናለን።
ስንሞትላት በደመ - ነፍስ አይደለም።አካላችንን ስንገብርላትም እንዲሆ በተራ ጀብድ ሳይሆን ታሪኳን ጠንቅቀን ስለምናውቅ ነው።
በባዕድና ባንዳ እኩል ሴራ እንዴት ከቀይ ባህር ተገፍተን የበዙ ጂኦ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ወሳኝ ብሄራዊ ጥቅሞቻችንን እንዳጣን ነጋሪ ሳንሻ ጠንቅቀን የምናውቀው ጉዳይ ነውና የኢትዮጵያችንን ዕንባ ለማበስ ሁሌም ዝግጁ ነን።
"የቀይ ባህር የታሪክ ስብራቷ ታክሞ የታላቅ ሀገርነት እውነቷ ይመለሳል" ብለን በጽኑ ስናምንም ያለ አንዳች ጥርጥር ነው።
በአስቻለው ሌንጫ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 26 ቀን 2017 ዓ/ም
ከአውሮፓ እስከ መካከለኛው ምስራቅ ተንሰራፍቶ አይነቃነቄ የመሠለው የሮማ ኢምፖየር አይኗ ስር ሲፈራርስ በአርምሞ ታዝባለች።
የእነ ፔርሺያን አይነኬ ይባል የነበረ የጊዜው ሃያል ሀገራትን አካልሎ የዋጠ እናም የገዘፈ ግዛት እንክትክት ብሎ ሲወድቅ የተመለከተች ትዝታ ብዙ ነች። ኢትዮጵያ።
ከጥንት እስከ ዛሬ ስሟን አስጠብቃ ነበረች፣ አለች፣ ትኖራለች።
በሀገረ-መንግስት ግንባታ ታሪኳ ከዓለም ሀገራት አኳያ ጉምቱ ብትሰኝ የማይበዛባት ናት የሀገራት አንጋፋዋ ኢትዮጵያችን።
የዚህችን ቀልብ ሳቢና እምቅ ታሪኳ በቅጡ ያልተጠናላት ሚስጢረ-ብዙ ሀገርን ድብቅ እውነታ ለማወቅ የቋመጡ አውሮፓውያን በብዙ ስለመልፋታቸው ሀገራትንና ታሪካቸውን አሳሽ ነን ከሚሉቱ መካከል ጀምስ ብሩስን ማስታወስ በቂ ነው።
ኢትዮጵያ በአሁናዊዋ ሉላዊት /Global/ዓለማችንም አስፈላጊነቷና በወሳኝ ስትራቴጂክ አቀማመጧ ዓይን የሚጣልባት መሆኗ የቀጠለ ብቻ ሳይሆን መዓት ዋጋዎችን እያስከፈላት...ወሳኝ ብሄራዊ ጥቅሞቿን እንድታጣ መደረጓም አብሰልሳይ የታሪክ እውነታዋ ነው።
እኛ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከምንም በላይ አጽንኦት ሰጥተን ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ለሰከንድ የማናቅማማበት ጉዳይ ቢኖር...የውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ነው።
በስኬት ተጠናቆ በቅርቡ ለምርቃት ዝግጁ የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድባችን ዕውን እንዲሆን በጽናት የከፈልነውን ውድ መስዋዕትነት በኩራት የምናስታውሰው ብቻ ሳይሆን የግድቡ አርማታ ሲላቆጥ ውሃ ብቻ ሳይሆን የእኛም ደም እንደነበረበት ስናስብ ታላቅ ደስታ እየተሰማን ነው።
ለህላዌዋ ስለምንሞትላት ኢትዮጲያችን ብሄራዊ ጥቅም መረጋገጥ ለአፍታ የማንዘናጋ ከመሆናችንም በላይ የህዳሴው ግድብ ድል በቀይ ባህርም ተደግሞ የተነጠቅነው እውነታችን እንደሚመለስልን በልበ - ሙሉነት እናምናለን።
ስንሞትላት በደመ - ነፍስ አይደለም።አካላችንን ስንገብርላትም እንዲሆ በተራ ጀብድ ሳይሆን ታሪኳን ጠንቅቀን ስለምናውቅ ነው።
በባዕድና ባንዳ እኩል ሴራ እንዴት ከቀይ ባህር ተገፍተን የበዙ ጂኦ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ወሳኝ ብሄራዊ ጥቅሞቻችንን እንዳጣን ነጋሪ ሳንሻ ጠንቅቀን የምናውቀው ጉዳይ ነውና የኢትዮጵያችንን ዕንባ ለማበስ ሁሌም ዝግጁ ነን።
"የቀይ ባህር የታሪክ ስብራቷ ታክሞ የታላቅ ሀገርነት እውነቷ ይመለሳል" ብለን በጽኑ ስናምንም ያለ አንዳች ጥርጥር ነው።
በአስቻለው ሌንጫ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
YouTube
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# የመከላከያ ሠራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
❤36👍13🏆3👎2🥰1