FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.7K photos
34 videos
9 files
8.49K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ከኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር የጋራ ሥልጠና ሰጡ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሀሴ 09 ቀን 2017 ዓ.ም 

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ከኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር ያዘጋጀው ስልጠና ሰራዊቱ ተላላፊ በሽታዎችን ቀድሞ ለመከላከል እንደሚረዳ እና ሰራዊቱን ከተለያየ በሽታ ለመከላከል እንደሚያስችል በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የደቡብ ዕዝ ጤና መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ግርማይ ከበደ ገልፀዋል።

ሙያተኞችን በስልጠና ለማብቃት የተቋሙና የሲቪል ተቋማት ርብርብ ማድረጋቸው የሚበረታታ መሆኑን
የሀገር አቀፍ የናሙና ቅብብሎሽ አስተባባሪ ሬድዋን መሀመድ ገልፀዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ የሰራዊት አባላትም ስልጠናውን በመውሰዳቸው ጥሩ እውቀት መጨበጣቸውን እና ወደ ክፍላቸውም ሲመለሱ ባገኙት እውቀት ሰራዊቱን ለማገልገል ዝግጁ መሆናችውን አረጋግጠዋል::

ስልጠናው የተሰጠው ከተለያዩ ዕዞች፣ ማሰልጠኛዎች እና ከልዩ ልዩ ከፍሎች ለተውጣጡ የሜዲካል ላብራቶሪ ቴክኒሺያን ሙያተኞች ነው።

ዘጋቢ እዮብ ሰለሞን
ፎቶግራፍ አብረሃም ወርቁ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
32🥰2🔥1
የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ከፍተኛ አመራሮች ጉብኝትና ማዕረግ የማልበስ ሥነ-ሥርዓት።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 09 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ብሄራዊ ቤተ-መንግስትን ጎብኝተዋል።

ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ዛሬ የተመለከትነው የጉብኝት ቦታ ሀገራችን ተከብራ ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ የዘለቀች ሥለመሆኗ ትውልድ የሚማርበት መሆኑን ገልፀዋል።

ታሪክን በአግባቡ እና ትውልድ በሚያስተምር መንገድ ሰንዶ በማዘጋጀት በዚህ መልኩ ለጉብኝት ክፍት እንዲሆን የሰራ አካል በእጅጉ ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል።

አያት አባቶቻችን ያስረከቡንን ሀገር ሉዓላዊነቷንና ብሄራዊ ጥቅሟን በማስጠበቅ ለመጭው ትውልድ ለማስረከብ ሰራዊታችን ተልዕኮውን በብቃት እየፈፀመ እንደሚገኝ የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ ጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ሀገርን ከውስጥ ባንዳና ከውጭ ጠላት በመጠበቅ እና የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የማስከበር ተልዕኮውን ከመቸውም ጊዜ በላይ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ገልፀዋል።

ከጉብኝቱ በኋላ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ በተገኙበት የመቆያ ጊዚያቸውን የሸፈኑና ማዕረግ መልበስ የሚያስችላቸውን መስፈርት ላሟሉ የዋና መምሪያው አመራሮችና አባለት የማዕረግ የማልበስ ስነ ስርአት ተካሂዷል።

የማዕረግ ዕድገት የበለጠ ሀላፊነት በመሆኑ የዛሬ ተሿሚዎች ይህንን ግምት ውስጥ በማስገባት የተሻለ የግዳጅ አፈፃፀም ለማስመዝገብ መትጋት ይጠበቅባችኋል ሲሉ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ አሳስበዋል።

የዛሬ ተሿሚዎች መምሪያው እየፈፀመ ለሚገኘው ሁሉን አቀፍ ስራ ተጨማሪ አቅም በመሆን የበኩላቸውን ሚና ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው አቅጣጫ ሰጥተዋል።

ዘጋቢ ማሙሸት አድነው
ፎቶግራፍ ገነት አወቀ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
61🔥5😡3
150 የሸኔ አባላት በተደረገላቸው የሠላም ጥሪ መሰረት በሰላማዊ መንገድ እጅ ሰጡ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የደቡብ ዕዝ ኮር ግዳጅ እየተወጣበት በሚገኘው ምዕራብ ጉጅ ዞን 150 የሸኔ አባላት የተደረገላቸውን የሠላም ጥሪ በመቀበል በሰላማዊ መንገድን እጅ ሰጥተዋል፡፡

የደቡብ ዕዝ ኮር ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሎኔል አባዲ ልዑል፣ የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አዶላ ሂርጳዬ ፣የዞንና የወረዳ አመራሮች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እጅ ለሰጡ የሸኔ አባላት አቀባበል አድርገዋል።

የኮሩ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሎኔል አባዲ ልዑል፣ እና የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አዶላ ሂርጳዬ፣
በሠላማዊ መንገድ እጅ የሠጡ የሸኔ አባላት ሠላም መርጠው እና የሠላም ጥሪውን ተቀብለው መግባታችው ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ ለሠላም መሥራት እንደሚገባቸው አመላክተዋል።

በሰላማዊ መንገድ የገቡት የሸኔ አባላትም እስካሁን ድረስ በሀገር እና በህዝብ ላይ ለፈፀሙት ያልተገባ ድርጊት መፀፀታቸውን ገልፀው ከእንግዲህ ሠላምን የማሥቀደም ሥራ እንደሚሠሩና ለሠላም እንደሚቆሙ ተናግረዋል፡፡

በዕለቱ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የሠራዊቱ አመራሮች አባገዳዎች የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። ዘገባው የኮሩ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
52👏12👍8🕊6🔥2🫡1
ዝግጁነቱን ያረጋገጠና በጠንካራ ስነ-ልቦና የተገነባ  ሠራዊት ተልዕኮዉን ለመፈጸም አስተማማኝ ነው።
‎     ሌተናል ጀኔራል መሰለ መሰረት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

‎የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሰለ መሰረት በቴዎድሮስ ኮር አንድ ክፍለጦር በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ተገኝተዉ  አጠቃላይ የወትሮ ዝግጁነት እና የግዳጅ አፈፃፀም የመስክ ምልከታ ባደረጉበት ወቅት ዝግጁነቱን ያረጋገጠና በጠንካራ ስነ-ልቦና የተገነባ  ሠራዊት ሀገራዊ ተልዕኮዉን ለመፈጸም አስተማማኝ  መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዋና አዛዡ ሠራዊታችን ከህዝብ የወጣ ለህዝብ የሚኖር እና ለህዝብ የሚሞት፣ አላማውን የማይሸጥ፣ ሃላፊነቱን የማይዘነጋ፣ ለህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ የታመነ በተቋማዊ እሴቶች ብቻ የሚመራ የሰላም እና የልማት ሃይል ነው ብለዋል።

‎አገርን መውደድ መዳረሻው ለሀገር ሰላም መስዋዕትነት መክፈል በመሆኑ በሰራዊታችን ዘንድ ሁሌም የሚፈፀም ሃቅና ተግባር ነው ያሉት ሌተናል ጀኔራል መሰለ መሰረት፤ የነፃነት ተምሳሌት የሆነችውን አገራችን ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ ማሻገር በሚችል በደማቅ መስዋዕትነት የህዝቦችን ዘላቂ ሰላም በማፅናት የአገሩን ሉዓላዊነትና ደህንነት እያስከበረ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።

‎የክፍለጦሩ የሠራዊት አባላት የኢትዮጵያን ሠላም ለማናጋት ሌት ተቀን በሚያሴሩ ፀረ ሰላም ሃይሎች ላይ ፈጣን ምላሽ በመስጠት የሚታወቅ ድል አድራጊ የህዝብ ልጅ መሆኑን የገለፁት ጀኔራል መኮንኑ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንቅፋት የሆነው አሸባሪው ሸኔ ላይ እርምጃ በመውሰድ ዞኖችን፣ ወረዳዎችን እና ቀበሌዎችን ከሸኔ በማፅዳት ህዝቡ በነፃነት ተንቀሳቅሶ ሰርቶ መግባት እንዲችል ከፍተኛ ሚና የተጫወተ ክፍለጦር መሆኑን ገልፀዋል።  

ዝግጁነቱን ያረጋገጠና በጠንካራ ስነ-ልቦና የተገነባ  ሠራዊት ሀገራዊ ተልዕኮዉን ለመፈጸም አስተማማኝ በመሆኑ በየትኛዉም ሁኔታ ዉስጥ እየተዋጋና እየሰለጠነ በተሰማራባቸው የግዳጅ ቀጠናዎች ሁሉ ጠንካራ አሃድን በስልጠና በማብቃት የማድረግ አቅሙን በየጊዜው በተግባር እያረጋገጠ የሚሰጠውን ማንኛውም ግዳጅ በጀግንነት በመፈፀም ዘላቂ ሰላም በማምጣት ኢትዮጵያን ማፅናት ከሁሉም የሠራዊታችን አመራርና አባላት ይጠበቃል ብለዋል።

‎ዘጋቢ ጋብዘው ዳና
‎ፎቶ ግራፍ ጋብዘው ዳና

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
19👏10👍6🔥2🏆1