FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.6K photos
33 videos
9 files
8.48K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
ተልዕኮ ተኮር የመስክ ላይ ሥልጠናዎች ለላቀ ግዳጅ አፈፃፃፀም ጉልህ ሚና እንዳላቸው ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

በዩናሚስ ሴክተር ኢስት ግዳጁን እየፈፀመ ለሚገኘው የ20ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ ሲሰጥ የነበረው ተልዕኮ ተኮር የመስክ ላይ ስልጠና ልምምድ ተጠናቀቀ።

የመስክ ላይ ስልጠና ልምምዱን የመሩት በደቡብ ሱዳን የሴክተር ኢስት አዛዥ ብርጋዲየር ጀነራል ራዛቅ አህመድ በዩናሚስ የሚሰጡ ተልዕኮ ተኮር ስልጠናዎች በማንኛውም ወቅት የሚኖሩ ግዳጆችን በብቃት ለመፈፀም ጉልህ ሚና አላቸው በማለት ተናግረዋል።

የተሰጠው ስልጠና እንደ አንድ ዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ሠራዊት ተልዕኮን በአስተማማኝ መንገድ ለመፈፀም የሚያስችል አቅምን ለመገንባት ይረዳል ያሉት የሴክተር ኢስት አዛዡ ብርጋዲየር ጀነራል ራዛቅ አህመድ በተለይ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሠራዊት በቀጠናው ያለውን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ እያበረከተ ያለውን ጉልህ ድርሻ የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል የመስክ ስልጠና ልምምድ ለቀጣይ ሥራ ተደማሪ አቅምን እንደሚፈጥርም አስገንዝበዋል።

የ20ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል ሰጥየ አራጌ በበኩላቸው ሥልጠናው በተያዘው ዕቅድ መሠረት መከናዎኑን ጠቅሰው እንደ አንድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ የተሰጠው ሥልጠና ከተልዕኳችን ጋር በቀጥታ ተያያዥነት ያለው ሲሆን በሥልጠና የተገኘውን አቅም ይበልጥ በመጠቀም ግዳጅን በውጤት ለመፈፀም ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል በማለት  አጽንኦት ሰጥተዋል።  ዘጋቢ አንዋር ሁሴን ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
32👍10🔥2
ሚስጢራዊነቱ የተጠበቀ ግንኙነት ለመመስረት የግንኙነት ስርዓቱን ማዘመን ተገቢ መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

ለሰሜን ምዕራብ ዕዝ ስታፍ ከፍተኛ መኮንኖችና መስመራዊ መኮንኖች ሚስጥራዊነቱን የጠበቀ የግንኙነት ዘዴ መጠቀም በሚያስችሉና በተቋሙ በበለፀጉ መተግበሪያዎች የግንኙነት ሲስተም ዙሪያ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል።

ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ የግንኙነት ስርዓትን ለመመስረት የግንኙነት ስርዓቱን ማዘመንና ዲጂታላይዝድ ማድረግ እንደሚገባ ነው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መገናኛና ኢንፎርሜሽን መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ የገለፁት።

አንድ መልዕክት ለብዙ ባለድርሻ አካላት ፈጣንና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ ሚስጥራዊነቱ ተጠብቆ እንዲደርስ የሚያስችሉ የግንኙነት ዘዴዎች ላይ አመራሩ ግንዛቤ እንዲያገኝ የሚያስችል ስልጠና ስለመሆኑም ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ ተናግረዋል።

በአውት ሉክና በሰርኩኒ የሚደረጉ የግንኙነት ዘዴዎች የግንኙነት ስርዓታችንን ከአናሎግ ወደ ዲጅታል ሲስተም የሚያሻግር ነው ያሉት ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ የእነዚህ አፕልኬሽኖች ፋይዳ ተቋሙ ባበለፀገው ዌብሳይት የምንጠቀም በመሆኑ ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀና አስተማማኝም ነው ብለዋል።

ዲጅታል የግንኙነት ስርዓትን መመስረትና መጠቀም መልዕክቶቹ በሰከንዶች ለባለ ድርሻ አካላት  ከመድረሳቸውም ባሻገር ወጪ ቆጣቢ ፣ደህንነቱ የተጠበቀ፣ጊዜና ጉልበትን የሚቆጥብ ፈጣንና አስተማማኝ ስለመሆኑም በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ ተገልጿል።

በተቋሙ የተፈቀደላቸው አካላት የጋራ መልዕክቶችን ለመላክ ለመቀበል እና በአንድ ጊዜ ለብዙ ባለድርሻ አካላት የፅሁፍ፣የድምፅና የቪዲዮ መልዕክቶችን ለመለዋወጥ የሚያስችሉ አፕልኬሽኖች ስለመሆናቸውም በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ተጠቁሟል።

ስልጠናው ከንድፈ ሃሳብ ባሻገር በተግባር ልምምድ የተደገፈና በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራው ለመግባት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ነው።
ዘገባው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
47👍20🔥3
ክፍለጦሩ ከአሸባሪው ኦነግ ሸኔ በርካታ መሳሪያዎች መማረኩን አሥታወቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

የማዕከላዊ ዕዝ አይበገሬ ክፍለጦር በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቶሌ ወረዳ በርካታ የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎችን እና ተተኳሾችን መማረኩን የክፍለጦሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ወልደ ገርማ ብርሃኔ ገልፀዋል።

ክፍለጦሩ በተሠማራባቸው ቀጠናዎች የሽብር ቡድኑን እግር በእግር ተከታትሎ በመደምሰስ ለዘረፋ ሲጠቀምበት የነበረውን መሳሪያና ተተኳሽ በመማረክ ቡድኑን ከጥቅም ውጪ ማድረግ መቻሉንም አሥረድተዋል።

ሠራዊቱ በየጊዜው በሚያደርገው የተቀናጀ ዘመቻ የአሸባሪውን የዘረፋ ተግባር በማክሸፍ እና ከህዝቡ ነጥሎ በመምታት በርካቶችን ሙትና ቁስለኛ ማድረጉንም ምክትል አዛዡ ተናግረዋል።

ዘጋብ ፍቃዱ አበራ
ፎቶግራፍ ዘውዱ አቡኔ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
62👍29👏5🔥4🕊3
የኢትዮጵያ ሠራዊት ለሀገር እና ለህዝብ ክብር ራሱን አሳልፎ የሠጠ ነው።
    ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሠራዊት ለህዝቦችና ለሀገር እንዲሁም ለሠንደቅ ዓላማው ክብር ራሱን አሳልፎ የሠጠ በጠንካራ ሀገራዊ ፍቅር የተገነባ መሆኑን የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል።

አዛዡ ዕዙ የአቅም ግንባታ ስልጠና አየሠጣቸው ለሚገኙ የሻምበልና የሬጅመንት አመራሮች በሠራዊት ግንባታ ሂደትና አቅጣጫ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥተዋል።

የማይሸነፍ ዘመናዊና ጠንካራ ሠራዊት መሠረቱ የጠንካራ አመራር የግንባታ ስራ ውጤት መሆኑን የገለፁት አዛዡ እያንዳንዱ መሪ ይህንን ተገንዝቦ የማያቋርጥ እና ከዕለት ዕለት አየዳበረ የሚሄድ የሠራዊት ግንባታ ስራን መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ ሠራዊቷን የምትገነባበት የራሷ የሆነ መልካም ዕሴት ያሉት ሀገር መሆኗን የገለፁት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የዜጎችን ክብርና ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅና ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆነ ሠራዊት መገንባት የመሪው የዘወትር ስራ መሆኑን አስረድተዋል።

አዛዡ በአንድ ሀገር ዴሞክራሲያዊ ስርአት ስር ሰዶ የሚያብበው ጠንካራ ሠራዊት ሲኖር መሆኑን ጠቁመው ይህ ከልሆነ ግን አምባገነኖችና የባዕዳን ተፅዕኖ ያረፈባቸው ተላላኪዎች የህዝብን የስልጣን ባለቤትነት በመቀማት መከራን እንደሚዘሩ ሩቅ ሳንሄድ ጎረቤቶቻችን አስረጅ ናቸው ብለዋል።

የሀገሩንና የህዝቡን ፍላጎትና ብሔራዊ ጥቅም ጠንቅቆ የሚያውቅ ሊመጡ የሚችሉትን አደጋዎች ተረድቶ በላቀ ሀገራዊ ፍቅር የኢትዮጵያንና የህዝቦቿን ብሔራዊ ጥቅም የሚጠብቅ ፕሮፌሽናል ሰራዊት የመገንባቱ ስራ አጠናክሮ መቀጠል በየደረጃው የሚገኝ አመራር ሃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል።

በስልጠና ላይ የሚገኙ የክፍሉ አመራሮችም ተቋሙ እየሠራ ያለውን የፕሮፌሽናል ሠራዊት ግንባታን በማጠናከር የለማች ኢትዮጵያንና በትውልድ ቅብብሎሽ  ለቀጣዩ ትውልድ ለማሸጋገር ያለመታከት እንደሚሠሩ በመድረኩ አረጋግጠዋል። ዘገባው የአብዱራህማን ሀሰን ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
39👍15👏10🔥2👎1
ጠንካራ ወታደራዊ ሥልጠና ግዳጅን በድል ለመወጣት እንደሚያሥችል ሌተናል ጀኔራል ይመር መኮነን ገለፁ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ሃላፊ  ሌተናል ጀኔራል ይመር መኮንን በደቡብ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል በስልጠና ላይ ለሚገኙ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል፡፡
   
ጄኔራል መኮንኑ በየደረጃው የሚገኘውን የሠራዊታችንን አመራሮች በተደጋጋሚ በማሰልጠን የአመራር ችሎታውን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። ጠንካራ ወታደራዊ ስልጠና ግዳጅን በድል ለመወጣት እንደሚያስችል ገልፀው በዚህም የሃገርን ሰላምና የአሃድን ደህንነት ማስጠበቅ  እንደተቻለ ተናግረዋል።
  
አሁን ላይ የሃገራችንን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ በስልጠና የበቃ የመከላከያ ኃይል መገንባቱን የተናገሩት ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮነን አመራሩ ተልዕኮውን  የሚረዳና ግዳጅን በአግባቡ የሚወጣ የተሰጠውን  ንብረትና የሰው ኃይል አቀናጅቶ በመምራት ደህንነትን በመጠበቅ በታጠቀው መሳሪያ የመጠቀም ችሎታ ያለው አዋግቶ ድል ማምጣት የሚችል ሥለመሆኑም አስገንዝበዋል።
   
ተቋሙ የዘመኑን ቴክሎጂ ውጤቶች የሚጠቀም ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ፕሮፌሽናል ሠራዊት መገንባቱን የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ በወታደራዊ ስነ-ምግባር  የታነፀና በዓላማው የፀና ሥለመሆኑም አንስተዋል።
    
ሠራዊታችን ለማንኛውም ግዳጅና ሁኔታ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ወታደራዊ አቅሙን ለማሣደግ በንድፈ ሃሳብና በተግባር በማሰልጠን የማድረግ ችሎታውን ከፍ ማድረግ እንደተቻለም አስረድተዋል።

ፈጣንና ተነቃናቂ ተልዕኮውን በብቃት መወጣት የሚችል በአካል ብቃት፣ በስነ- አዕምሮው የዳበረ ፣ሞራል ያለው ኃይል መገንባቱን የገለፁት ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮነን በቀጣይም ዘመናዊ ሠራዊት የማፍራቱ ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል፡፡

ዘጋቢ በላይ ታደለ
ፎቶ ግራፍ ቦጋለ አዲሴ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
27👏13👍6👎1
የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ለሠራዊቱ አቅም ግንባታ  ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮችና የአካዳሚ ስታፍ አባላት በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ከባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ እያካሄዱ ይገኛሉ።

በውይይቱ የየክልሉ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ ተቋማት የዕዝ አመራሮች የመከላከያ ሠራዊት አባላት ተገኝተዋል።

የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አላማና ተልዕኮውን ለማሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

ባለድርሻ አካላት የኮሌጁን ቁመና የማስተማር አቅም  መረዳት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የኮሌጁ አመራሮችና የአካዳሚ ክፍሉ አባላት በሲዳማ፣ በአፋር  በሀረሪ፣ በዲ
ድሬዳዋ ፣በጋምቤላ፣ በአማራ ክልሎች በመዘዋወር ለክልል አመራሮችና ለከተማ መስተዳድሮች እንዲሁም ለዕዝ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጡ ይገኛሉ።

አጠቃላይ ወደ ኮሌጁ የሚመለመሉና ተምረው ሲመረቁ ባገኙት የአመራር ብቃት ሀገራቸውን ማገልገል በሚያስችል የአመራር ጥበብ ተክነው እንዲወጡ ኮሌጁ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በአለማቀፋዊና አህጉራዊ እንዲሁም ቀጠናዊ  ጆኦ-ፖለቲካ የኢትጵያን  ጥቅም ማስጠበቅ በሚያስችል መንገድ መቃኘት እንዳለበትም ተገልጿል።

ዘመናዊ ሰራዊት መገንባት የሠራዊታችንን አቅም ከማሳደጉም ባሻገር  ለሀገራዊ ጥቅም አስቻይ ሁኔታ በመፍጠር ሀገረ-መንግስትን ማፅናት የሚችል አመራር መፍጠር እንደሚቻልም ተነስቷል። 

የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ቡልቲ ታደሰ የመከላከያ ዋር ኮሌጅ የመከላከያ ስትራቴጂክ አመራሮችን ከማስተማርና ከማስልጠን በተጨማሪ ከየክልሉ ተመልምለው የሚመጡ የሲቪል አመራሮችን  አስተምሮ በማስመረቅ ሀገራዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ ያለ ኮሌጅ እንደሆነ አስረድተዋል። ዘጋቢ አሰፉ ግርማይ ናት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
37👍16