FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.7K photos
34 videos
9 files
8.5K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
ዕዙ የሻለቃ፣ የሻምበል እና ልዩ ልዩ የስታፍ ክፍሎችን አሰልጥኖ አስመረቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የ6ኛ ዕዝ ለወራት በዕዙ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን የሻለቃ፣ የሻምበል፣ የሠራዊት ስነ ልቦና ግንባታ እና የፋይናንስ ዘርፍ ሙያተኞችን አስመርቋል።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው የስራ መመሪያ የሰጡት የዕዙ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን በየጊዜው የሚያጋጥሙ ፈተናዎች በአሸናፊነትና ድል አድራጊነት በመሻገር ሃገርን ከነ ሙሉ ክብሯ ለማስቀጠል በሁለንተናዊ አቅምና ችሎታ ልቆ መገኘት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

ሜጀር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ዕዙ ከዚህም ከዚያም  ብቅ ብቅ እያሉ የሃገራችንን ሰላምና ልማት ለማደናቀፍ የሚሞክሩ ፣ከትናንት የማይማሩ ተላላኪ ባንዳዎችና ታሪካዊ ጠላቶቻችን አደብ እንዲገዙ ለማድረግ ከምንጊዜውም በላይ አስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል።

ዕዙ ውስብስብ እና አስቸጋሪ ግዳጆችን በፅናት ተወጥቷል ያሉት ዋና አዛዡ አሁን ላይም ህገ መንግስታዊ እምነቱ የፀና ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ ክብር የሚዋደቅ አመራርና አባላት መገንባት እንደተቻለም አስረድተዋል።

ስልጠናው የሠራዊቱን አመራሮች ሙያዊ ብቃት ከፍ ለማድረግና ተልዕኮና ግዳጆችን በብቃት እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ
ሁሉም አመራር በየደረጃው በቀጣይ በክፍሉ በሚመራው ሠራዊት አርዓያ በመሆን አስከ ታችኛው ክፍል ድረስ ስልጠናዎችን በመስጠት ማብቃት እና ማስተማር ለፕሮፌሽናል ሠራዊት ግንባታ ሂደት አጋዥ ሆኖ መገኘት የእለት ተእለት ስራችሁ ልታደርጉ ይገባል ብለዋል።

ዋና አዛዡ የስታፍ ከፍሎችም ለዕዙ ስኬታማ የግዳጅ አፈፃፀም ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ያገኛችሁትን ሙያዊ አቅም ተጠቅማችሁ ሃላፊነታችሁን በቅንነትና በታታሪነት ልትወጡ ይገባል ነው ያሉት።

የስልጠናውን ሪፓርት ያቀረቡት የማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሌተናል ኮሎኔል ታምራት ሌንጅሶ ማሠልጠኛ ማዕከሉ የዕዙን የሠራዊት አመራሮችና አባላት በመሪነት ሚና እንዲሁም ልዩ ልዩ ሙያዎች አሰልጥኖ በማብቃት የዕዙን የግዳጅ አፈፃፀም የተሳካና ሁሌም በድል የሚቋጭ እንዲሆን በማድረግ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ዘጋቢ ደባልቅ አቤ
ፎቶግራፍ ይህዓለም አታላይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍2916🔥2🥰1👏1
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ጋር በመሆን ችግኝ ተከሉ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የሠራዊት አባላት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል ሀገራዊ መሪ ቃል ነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ያከናወኑት።

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማትና ዉበት ቢሮ ሃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ እንዳሉት ሰራዊቱ  የአገርን አንድነት እና ሰላም ከማረጋገጥ ባሻገር በሃገራዊ ልማቱ የሚያደርገዉ ተሳትፎ ህዝባዊነቱን አጉልቶ የሚያሳይ ነዉ።

ኃላፊው ሠራዊቱ ህይወትን ሰጥቶ ህይወትን ያሚያኖር ከመሆኑም በላይ ከህብረተሰቡ ጋር የሚያደረገው ልማታዊ ተሳትፎ የሚያኮራ ነው ለዚህም የላቀ ክብርና ምስጋና ይገባዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ግርማ ሰይፉ የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ እና ለታለመለት ደረጃ እንዲበቃ ማድረግ ከሁላችንም የሚጠበቅ ተግባር ነው ሲሉ አሳስበዋል፡፡ 

ዘጋቢ ምህረት ስመኝ
ፎቶ ግራፍ አብዱራህማን ሃሰን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
34👍12🔥3
ክፍለጦሩ በሽብር ቡድኑ ላይ በወሰደው ጠንካራ እርምጃ በርካቶች ተደምስሰዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የ6ኛ ዕዝ ጋሻ ክፍለጦር በሰሜን ሽዋ ዞን አቦቴ ወረዳ በአለቆች ቀሬ እና በያያ ማርያም ቀበሌዎች ሲንቀሳቀስ በነበረው አሸባሪ የሸኔ ቡድን ላይ በወሰደው የማያዳግም እርምጃ በርካታ የሽብር ቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ የጦር መሳሪያና ተተኳሽ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክፍለጦሩ አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ጌትነት ተድላ ተናግረዋል።

የሽብር ቡድኑ ራሱን የህዝብ ነፃ አውጭ ነኝ በማለት እየነገደና አሉባልታ እየነዛ ህዝቡን ለአመታት እረፍት በመንሳት ሃብትና ንብረቱን ሲዘርፍ የቆየ መሆኑን አንስተው አሁን ላይ በተወሰደበት እርምጃ ተደምስሷል ብለዋል።

የሽብር ቡድኑ ሲጠቀምበት የቆየው መሳሪያ እና ተተኳሽ እንዲሁም የወገብ ትጥቅ በቁጥጥር ስር መዋሉንም ገልፀዋል።  ዘጋቢ ውበቴ አማረ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
39👍12🔥3
በኢትዮጵያ የህንድ ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ሳሚር ማህዋል ጉብኝት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

በኢትዮጵያ የህንድ ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ሳሚር ማህዋል የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ጎበኙ

የተደረገው ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ወታደራዊ ግንኙነት ለማጠናከር እና የሁለትዮሽ ወታደራዊ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ያለመ ነው ሲሉ የኮሌጁ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አበበ ዋቅሹማ ገልፀዋል፡፡

በእትዮጵያ የህንድ ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ሳሚር ማህዋል የኮሌጁን የመማር ማስተማር ሂደት እና የመማሪያ ሾፖችን ጎብኝተዋል። ኮሌጁ በሚያስተምራቸው የሙያ ዘርፎች አጠቃላይ ገለጻ በኮሌጁ አመራሮች ተደርጎላቸዋል። በኮሌጁ የተሰሩ የፈጠራ እና የምርምር ስራዎችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡

ኮሎኔል ሳሚር ማህዋል ሁለቱ ሀገራት የቆየ ጠንካራ ዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላችው መሆኑን ገልጸው ለቀጣይም የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ ግንኙነት አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ አፍወርቅ በቀለ
ፎቶግራፍ ጥሩወርቅ አናጋው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍2719🔥3
ዋና መምሪያው በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ስራዎችን በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን አሥታወቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የዋና መምሪያው የሠራዊት አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሠራተኞች በአመቱ በመናበብ አሠራር እና መመሪያን በመከተል የተሳካ ውጤታማ ተግባር መከናወናቸውን የመከላከያ ሠው ሃብት አመራር ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አጫሉ ሸለመ ተናግረዋል።

እንደ ዋና መምሪያ በመደጋገፍና በመረዳዳት የጋራ ሥራ መሥራት ውጤታማ እንደሚያደርግ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ሥራዎች ማሳያ መሆናቸውን የገለፁት ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ መምሪያዎች እና ቡድኖች የተሠጣቸውን ሃላፊነት በአግባቡ ተወጥተዋል ብለዋል።

አሥቀድሞ በመዘጋጀት በሠራዊት ምልመላ ላይ በሁለት ዙር የተደረገው ሥራ እጅግ የተሳካና ውጤት ያለው መሆኑን ብሎም በተፈለገው ልክ መከናወኑን የመምሪያ ሃላፊዎች ገልፀዋል።

የካዴት ሥልጠናን ጨምሮ አመራሩን በትምህርት ዕድል በየደረጃው የማብቃት ስራ ከሀገር ውስጥ ባለፈ ተቋሙ በከፍተኛ ወጪ ወደውጭ ሃገር በመላክ እያሥተማረና እያበቃ እንደሚገኝ የገለፁት ኃላፊዎቹ የትምህርትም ሆኑ ሌሎች ምልመላዎች አሠራር እና ሥርዓትን የተከተሉ ሥለመሆናቸውም አንስተዋል።

በአገልግሎት አሰጣጥ በኩልም ለተገልጋዩ የተጣራ መረጃ በመስጠትና የሰው ሃይል በመቆጣጠር ዳታን በማደራጀትና ሠራዊቱ በግዳጅ ላይ ደስተኛ እንዲሆን በማድረግ በኩል ሁሉም የሰው ሃይል ሙያተኛ በላቀ ደረጃ ስራውን በመስራት ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ሌላዉ የአገልግሎት አሰጣጡ ተደራሽ መሆኑን ለማረጋገጥ ሰራዊቱ ባለበት ቦታ ድረስ በአካል በመገኘት በኢንስፔክሽን በዳታዎች ምልከታና በውይይት የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል።

ከጡረታና  ከስንብት አንፃር ለተቋሙ አገልግሎት ሰጥተው የሚሠናበቱ የሠራዊት አባላትን በመመሪያና በአሰራሩ መሠረት በመተግበር የተቀመጠለትን በወቅቱ እንዲያገኝ እና በደስታ ሲያገለግል እንደነበር ሲሰናበትም ደስተኛ ሆኖ እንዲወጣ በማድረግ በኩል የተሻለ ስራ መሠራቱን የመምሪያ ሃላፊዎች ገልፀዋል።

ዘጋቢ መልካሙ ያደታ
ፎቶግራፍ ትግስት ሙላት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
39🔥3👍2
ዘመኑን የሚመጥን የኢንፎርሜሽን ሲስተም የመዘርጋት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

ዋና መምሪያው በበጀት አመቱ  በርካታ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወኑን የገለፁት የመከላከያ መገናኛና ኢንፎርሜሽን ሲስተም ዋና መምሪያ ሀላፊ ብርጋዲየር ጀነራል አዱኛ ዴሬሳ ፣ ተቋሙ የያዘውን የዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ ለማጠናከር በወታደራዊ ግንኙነት መስኩ ብቁ የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ እየገነባ መሆኑን ገልፀዋል።

መምሪያው የሰው ሃይልን የማብቃት ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን የገለፁት ሀላፊው ፣ዘመኑን የሚመጥን የኢንፎርሜሽን ሲስተም በመታጠቅ ፣ በመዘርጋትና በመጠቀም ተቋሙን ወደላቀ ደረጃ  የማሳደግ ጥረቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

የውጊያ አቅምን ከፍ ሊያደርጉ የሚችሉና ከፍተኛ ወጪ ያወጡ የነበሩ ሶፍትዌሮችን በራስ አቅም በመጠቀም በመስራት ለተቋሙ የሚጠቅሙ ቀላልና ዘመናዊ ሶፍትዌሮችን በማበልፀግ ወደ ስራ የተገባ መሆኑንም ብርጋዲየር ጀነራል አዱኛ ዴሬሳ ገልፀዋል።

በእለቱ በስራ አፈፃፀማቸው ብልጫ ላመጡ አባላት የእውቅና ሰርተ-ፊኬት እና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ከሰራዊቱ በክብር ለተሰናበቱ አባላትም የክብር ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

ዘጋቢ ራሔል ዮሐንስ
ፎቶግራፍ አበረ አየነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
26👍10🔥3