FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.5K subscribers
30.8K photos
36 videos
9 files
8.51K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች እና የሠራዊት አባላት በምስራቅ ሸዋ ዞን በሎሜ ወረዳ ችግኝ ተከሉ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሀመድን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በምስራቅ ሸዋ ዞን በለሚ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር ተካሂዷል።

የመከላከያ ሚኒስትሯ ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሀመድ  ዛሬ  በአፈር ላይ የተከልነው ችግኝ  ነገ የተስፋ ሀውልት ሆኖ ለጥላነት እና ለምግብነት ይውላል ብለን እናምናለን፤ ነገ የተሻለ እንደሆነ የሚያመላክት የአረንጓዴ አሻራ ፊርማችንም ይሆናል ብለዋል።

ዛሬ አፈር በነካው እጃችን የምንተክለው ችግኝ ነገ ለማንሰራራት እና ለመታደስ መሆኑን እርግጠኛ የምንሆነው ዛሬ የተከልናቸው ችግኞች ነገ ሺህ ቅርንጫፎች ሆነው ለጥላና ለፍሬ እንደሚበቁ ጥርጥር ስሌለለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ ጥላ የሚሰጥ ዛፍ የሚተክለውን አይረሳም እንደሚባለው ዛሬ በዚህ የተገኘነው ሁሉ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር አሻራ እያስቀመጥን መሆኑን ለአፍታም መዘንጋት የለብንም ብለዋል።

በመትከል ማንሰራራት የዘንድሮው አረንጓደ አሻራ መሪ ቃል መሆኑን ጠቅሰው ለውጥ የሚመጣው እጅን አጣጥፎ በመቀመጥ ሳይሆን ጠንክሮ በመስራት እንደሆነ አመላክተዋል። ይህ ለውጥ እውን ይሆን ዘንድም እንደመከላከያ ከ18 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል የተያዘውን እቅድ ለመፈፀም በርትተው እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ዘጋቢ ብርሃን እንዳየሁ
ፎቶ ግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
21👏14👍13
የደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አመራርና አባላት የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አከናወኑ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

የደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ "በመትከል ማንሰራራት" የሚለውን ሀገራዊ መሪ ሀሳብ መሰረት በማድረግ የዕዙ ዋና አዛዥ ፤ምክትል አዛዥ እንዲሁም የኮር እና ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት "የሰራዊቱ መሪ ቃል በሆነው ከካምፓችን ወደ ህዝባችን" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል።

መርሃ-ግብሩን የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ሰለሞን ኢተፋ ችግኝ በመትከል ያስጀመሩ ሲሆን ሠራዊታችን የተሰጠውን ተልዕኮ እያስቀጠለ እንደሚገኝ በመግለፅ ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ነገ በሀገራችን የተስተካከለ የአየር ንብረት እንዲኖር ከማሥቻልም በተጨማሪ ለምግብነት የሚያገለግሉ የተለያዩ ፍራፍሬዎችን ለመትከል በመዘጋጀት ጭምር እንደሆነ  ገልፀዋል።  ዘጋቢ እዮብ ሰለሞን ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
30👏9👍5
የሀገራችንን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ በተግባር  የተገለጠ ስራዎችን መስራታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል።
    ክብርት ወይዘሮ ሐና አርዓያስላሴ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ፣የፍትህ ፣ የሰላም ሚኒስትሮች እና ተጠሪ ተቋማት በመተባበር ባዘጋጁት የክረምት የበጎ ፍቃደኝነት ተግባር ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ላይ  የተገኙት የፍትህ ሚንስትሯ ክብርት ወይዘሮ ሐና አርዓያስላሴ ፣ የክረምት የበጎ ፍቃድና የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴው የሀገራችንን ብልፅግናና ልማት ለማረጋገጥ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

የተተከሉት ችግኞች በወረዳው የተጀመሩትን የግብርና ስራዎች ከማገዝ ባለፈ ለመጪው ትውልድ ጥሩ መሰረትን የሚጥሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል የኑስ ሙሉ በበኩላቸው ከመከላከያ ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ እንደሚሰሩ ገልፀው ፣በወረዳው በተከናወነው የችግኝ ተከላና የበጎ ተግባር ስራ በመሳተፋቸው ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

በምስራቅ ሸዋ ዞን በሎሜ ወረዳ በተካሄደው ዝግጅት ላይ  አምስት ሺህ የተለያዩ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን  ለ1500 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍና የአስራ ስድስት የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጀምሯል።

በዝግጅቱ ላይ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጂነር ሀይሻ መሃመድ ፣ የሎሜ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታዬ ዶሪን ጨምሮ ሚኒስትር ዲኤታዎች ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ፣ የምስራቅ ሸዋና የወረዳው የስራ ሀላፊዎችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👏2120🎉1