ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
196K subscribers
279 photos
1 video
16 files
208 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_ሰላሳ_አራት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ማርጋሬት በሰማችው ተንገሸገሸች ‹‹በጣም የሚያስፈራ ነገር ነው
የነገርከኝ፡፡ ለዚህ ነው እንደ ፍራንኪ ጎርዲኖ ያሉ ወሮበሎች የእጃቸውን
ማግኘት አለባቸው የሚባለው

ትንሽ ዝም ብለው ቆዩና ‹‹ኧረ ለመሆኑ በፍራንኪ ጎርዲኖ እና በክላይቭ መምበሪ መካከል ያለው ግንኙነት ምንድን ነው?,,

‹‹እንጃ እኔ አላውቅም›› አላት፡፡

‹‹ፔርሲ መምበሪ ሽጉጥ ይዟል ብሎ ነግሮኛል፡ ፖሊስ ሳይሆን አይቀርም››

‹‹እውነት! እንዴት?››

‹‹እንደዚህ አይነት ልብስ የለበሰው እንዳይታወቅበት ነው››

‹‹ፍራንክ ጎርዲኖን የሚጠብቅ ፖሊስ ይሆናል››

‹‹ለምን? ጎርዲኖ እንግሊዝ አገር ውስጥ ታድኖ የተያዘ አሜሪካን አገር እስር ቤት የሚወስድ ወንጀለኛ ነው፤ ከአይሮፕላኑ ዋጋ ውድነት አንጻር የእንግሊዝ ፖሊስ ኮሚሽን ገንዘቡን ገፍግፎ እስረኛ እንዲያጅብ ፖሊስ
የሚልከው ለምንድነው?››

‹‹አንተን ይሆን የሚከታተለው?›› አለች በጆሮው

‹‹አሜሪካን አገር ድረስ›› አለ ሄሪ ጥርጣሬ ገብቶት ‹‹ለሁለት የወርቅ
አምባሮች ሲል?››

‹‹ታዲያ እዚህ ለምን መጣ?››

‹‹አላውቅም››

‹‹የሆነ ሆነና የጎርዲኖ ጉዳይ ራት ላይ አባቴ ያሳየውን መጥፎ ባህሪ
የሚያረሳሳ ይመስለኛል፡››

‹‹ለምንድን ነው እንደዚያ የሆኑት አባትሽ?›› ሲል ጠየቀ ሄሪ፡

‹‹እኔ እንጃ ከዚህ በፊት እንደዚህ ሆኖ አያውቅም››
‹‹ከዚህ ቀደም የፋሺስት አስተሳሰብ አራማጆች አጋጥመውኛል አለ
ሄሪ ‹‹እነዚህ ሰዎች ፍርሃት አለባቸው››

‹‹እንደዚያ ነው?›› ማርጋሬት አባባሉ ያስደነቃት ከመሆኑም በላይ ሊሆን የማይችል ሆነባት፡፡ ‹‹ፋሺስቶች ሲያይዋቸው ሞገደኛ ይመስላሉ
ውስጣቸው የተረጋጋ አይደለም፡፡ ለዚህ ነው ዩኒፎርም ለብሰው ላይ ታች
የሚሉት፡፡ በቡድን ሲሆኑ ነው ደህንነት የሚሰማቸው ዲሞክራሲ የሚጠሉት ለዚህ ነው፡፡ አየሽ ዲሞክራሲ የተለያየ አስተሳሰብ እንዲንፀባረቅ
ይፈቅዳል ገደብ አይጥልም
አምባገነንነትን ለምን እንደሚወዱ ታውቂያለሽ? ወደፊት የሚሆነው የታወቀ ስለሆነና የፋሺስት መንግስት በቀላሉ ለውጥ ስለማይደረግበት ነው››

‹‹አባቴ ኮሚኒስቶችን ወይም ጽዮናዊያንን ወይም የሰራተኛ ማህበራትን
ያለ ምክንያት አይደለም የሚጠላው እነዚህ ሐይሎች
ያንበረክኳታል ብሎ ይሰጋል፡››

‹‹ፋሺስቶች ሁልጊዜ ብስጩ ናቸው›› አለ ሄሪ፡፡

‹‹አባቴም እንዲሁ ነው  አያቴ ሲሞቱ ዕዳ ያለበት ርስት ነው ያወረሱት፧ እናቴን እስኪያገባ ድረስ ተቸግሮ ነበር የኖረው፤ከዚያም
ለፓርላማ አባልነት ተወዳድሮ ቢያሸንፍም በሩን አልረገጠም፤ አሁን ደግሞ
ካገሩ ተነቅሎ ተባረረ›› አለች፡፡

ማርጋሬት ‹ሄሪ ማርክስ ከቤተሰብ ጠፍቼ እንድሄድ ይረዳኝ ይሆን?› ስትል አሰበች አሜሪካ ከገቡ በኋላም እንዳሁኑ ይቀርባት እንደሆነ እርግጠኛ
አይደለችም፡፡ ‹‹አሜሪካ የት ነው ልትኖር ያሰብከው?›› ስትል ጠየቀችው።

‹‹ኒውዮርክ ቤት ተከራይቼ እኖራለሁ፤ አሁን እጄ ላይ ጥቂት ገንዘብ አለኝ፤ ሌላም ገንዘብ የሚገኝ ይመስለኛል፡››

ሄሪ ሁሉን ነገር አቅልሎ ነው የሚናገረው ‹‹ምናልባትም ለወንዶች ቀላል ይሆናል፡፡ ሴት ልጅ ግን ረዳት ያስፈልጋታል››

‹‹ናንሲ ሌኔሃን ስራ ልትቀጥረኝ እንደምትችል ነግራኛለች›› አለች፡
‹‹ሆኖም ወንድሟ ኩባንያውን ከወሰደባት የገባችልኝን ቃል ላትጠብቅ
ትችላለች››

‹‹ከፈለግሽ እኔ አግዝሻለሁ›› አላት፡፡

እሷ እንዲህ አይነት ድጋፍ ነው የፈለገችው

‹‹ትረዳኛለህ?›› ስትል
ጠየቀችው፡፡

ሄሪ ምን ሊያደርግላት እንደሚችል ግልፅ ባይሆንለትም ‹‹ቤርጎ ፈልጌ
አሳይሻለሁ›› አላት፡፡

ይህን ቃል ስትሰማ የተሰማት እረፍት ቀላል አይደለም፡፡

‹‹እግዜር ይስጥህ፡፡ እኔ በህይወቴ ቤርጎ ፈልጌ ይዤ አላውቅም፡፡››
‹የቤት ኪራይ ማስታወቂያ እናያለን››

በታይምስ ጋዜጣ ላይ እንዲህ አይነት ማስታወቂያ አይቼ አላውቅም››አለች አባቷ የሚያነቡት ይህን ጋዜጣ ብቻ መሆኑን አስታውሳ፡፡

‹‹ማታ ማታ የሚወጡ ጋዜጦች ላይ ነው ማስታወቂያዎች የሚወጡት››

እንዲህ አይነት ቀላል ነገር እንኳን ባለማወቋ አፈረች፡፡
‹‹እኔ የሚረዳኝ ሰው ያስፈልገኛል››
‹‹አይዞሽ አትፍሪ እኔ የምችለውን ያህል እረዳሻለሁ››
‹‹በእውነት የሚያስደስት ነው›› አለች ማርጋሬት ‹‹ሚስስ ሌኔሃንና አሁን ደግሞ አንተን ካገኘሁ ኑሮውን እቋቋመዋለሁ፡ ውለታ ከፋይ ያድርገኝ፡፡ ምን እንደምል እንጃ፡:››

ዴቪ ወዳሉበት መጣና ‹‹በመስኮት ተመልከቱ አንድ ነገር ታያላችሁ›› አለ።

ማርጋሬት አይሮፕላኑ ለአስራ አምስት  ደቂቃ ያህል ሳይወዛወዝ
እንደተጓዘ ተገነዘበች፡

ማርጋሬት በመስኮት አሻግራ ተመለከተች፡፡ ሄሪ የመቀመጫ ቀበቶውን
ፈታና በማርጋሬት ጀርባ በኩል አሻግሮ አየ፡፡

‹‹ለእኛ ብለው ይሆናል መብራቱን ሁሉ ያበሩት›› አለ አንዱ፡፡

ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ የአየር ጥቃቱን በመፍራት በጨለማ ነው የሚጓዙት፡ ማርጋሬት ሄሪ በጣም ወደሷ መጠጋቱን አልጠላችውም:
የአይሮፕላኑ የመገናኛ ሰራተኛ ከመርከቡ የመገናኛ ሰራተኛ ጋር በሬዲዮ
ሳይነጋገር አልቀረም፡፡ የመርከቡ ተሳፋሪዎች ወደ መርከቡ በረንዳ ላይ
ወጡና እጃቸውን አውለበለቡ፡፡ አይሮፕላኑ ከመርከቡ በቅርብ ርቀት የሚበር በመሆኑ ወንዶቹ ነጫጭ የራት ልብስ፤ ሴቶቹ ደግሞ ቅልጥም የሚታከክ
ልብስ መልበሳቸውን በግልጽ ይታያል፡፡

መርከቡ ማዕበሉን በሹል አፍንጫው እየሰነጠቀ ሲጓዝ አይሮፕላኑ አልፎት በረረ፡፡ ማርጋሬት ሁኔታው አስደስቷታል፡ ሄሪን ስታየው እሱም አያትና ተሳሳቁ፡፡ ሰዎች እንዳያዩት በሰውነቱ ከልሏት እጁን ወገቧ ላይ ጣል አድርጓል፡፡ በእጁ ገላዋን ነካ ያደረጋት ቢሆንም በመላ ሰውነቷ ላይ
የኤሌክትሪክ ሞገድ ያህል ሙቀት ለቆባታል፡ ይህ ሁኔታ በመጠኑ ድንግርግር እንዲላት ቢያደርግም እጁን እንዲያነሳ ግን አልፈለገችም ከትንሽ ጊዜ በኋላ ቁልቁል የሚያዩትን መርከብ አልፈው ሲሄዱ ከመርከቡ የሚፈነጥቀው መብራትም እየራቃቸው ሄደ፡፡ የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች ወደ
ቦታቸው ሲመለሱ ሄሪም ወደ ቦታው ሄደ፡፡

ዋናው ሳሎን ውስጥ ካርታ ከሚጫወቱት ጋር ማርጋሬትና ሄሪ ብቻ
ሲቀሩ ሌሎቹ ተሳፋሪዎች ወደ መኝታቸው ሄዱ፡ ማርጋሬት ከሄሪ ብቻዋን ተቀምጣ እፍረት ተሰማትና ‹‹መሽቷል ብንተኛ ይሻላል›› አለች ወዲያው ለምን እንዲህ አልኩ? አለች ለራሷ መተኛት አልፈለገችም: ሄሪ
ከእሷ መለየቱ ደስ ስላላለው ‹‹እኔም ትንሽ ቆይቼ እሄዳለሁ›› አለ
ማርጋሬት ከመቀመጫዋ ተነሳች ‹‹ወደፊት አሜሪካ ውስጥ እረዳሻለሁ
ስላልከኝ አመሰግናለሁ›› አለች፡፡
" ምንም አይደል"
"መልካም ምሽት"
"ለአንቺም እንዲሁ" አለ ሄሪ
ከመሄዷ በፊት ዞር አለችና እረዳሻለሁ ያልከኝ ከአንጀትክ ነው አይደል?

"አይዞሽ አታስቢ›› አላት፡፡

ማርጋሬት ለሄሪ ያላት ፍቅር እየጨመረ መጥቷል፡፡  ከዚያም  በደመነፍስ እዚያው ቁጭ ባለበት ከንፈሩን ሳም አደረገችው፡፡ ይህም ደስ የሚል ስሜት አጭሮባታል፡፡ ግን ደግሞ ወዲያውኑ ባደረገችው ነገር ክው አለች ያጫረባት ደስታ ጉልበቷን አብረክርኳታል፡፡ ዙሪያ ገባውን
ስትመለከት ሚስተር መምበሪ የላይኛውን አልጋ ሲይዝ የታችኛውን ሄሪ
ይዟል፧ ፔርሲም የላይኛው አልጋ ላይ ተኝቷል፡፡ መጋረጃውን ጋረደች፡፡

መብራቱን አጠፋችና ብርድ ልብስ ውስጥ ገብታ ተኛች። መኝታው ይሞቃል፡፡ በመስኮት ስታይ ከጨለማና ከዝናብ በስተቀር ምንም የሚታይ ነገር የለም፡፡ እሷና ኤልሳቤት ትንንሽ ልጆች ሆነው በበጋ ውስጥ እውጭ ድንኳን ተክለው የሚተኙት ትዝ አላት፡፡

ኤልሳቤት የት ትሆን ያለችው?
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_ሰላሳ_አራት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ብርጭቆውን አንስታ ተጎነጨችለትና መልሳ በማስቀመጥ መልስ ለመሰጠት  ተዘጋጀች….
ኬድሮን በምታየው ነገር  በጣም ደንዝዛለች …አላማዋንም ዘንግታ ….የሚበላትንም ነገር ችላ ብላ በምስጠት እየተከታተለችው ነው..በሌላ እይታ…. በሌላ መነጽር
ቀጠለች ልጅቷ‹‹የእኔ ፍቅር በጣም እኮ ነው የምትገርመኝ…. ዛሬም ተስፋ አትቆርጥም፡፡ በቃ እኔን እኮ ከዚህ በሽታዬ ለማዳን ለአመታት ለፋህ..ያለህን ንብረት ጨረስክ ..እስራኤል፤ህንድ፤አሜሪካም ጭምር ወስደህ በአለምአቀፍ ደራጃ አሉ በተባሉ የህክምና ተቋምና ምርጥ ጠቢቦች እድታከም አድርገሀል…በቃ አልተሳካም …እንደውም በአንተ ጥረት ነው የአንድ እና የሁለት አመት ቀሪ እድሜ ማግኘት የቻልኩት..ስለዚህ ይህቺን ባንተ ጥረት ያገኘኋትን ቀሪ ዕድሜዬን እንዳልከው በፍቅር እናጣጥምና ከዛ በሰላም ሸኘኝ …ባይሆን እዛ ጎጆ ቀይሼ መኖሪያ ቦታ  አመቻችታ እጠብቅሀላሁ..››አለችና ጉንጩን በመሳም ስሩ ውሽቅ አለችበት..እሱም አጥብቆ አቀፋትና በአንድ እጁን  ከአይኖቹ ሚንጠባጠበውን  እንባ ማበስ ጀመረ ..

ከዚህ በላይ መቆየትም ሆነ  በአላማዋ መግፋት አልቻለችም ….መኪናዋን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው..ተቀጣጥሎ የነበረው የወሲብ ስሜቷ አሁን ከስሟል.‹‹.በዚህ አይነት ፍቅር ውስጥ እንዴት መግባት እችላለሁ?››..ይህቺንስ ሞት ፊት ለፊቷ የቆመባትን ሴት እንዴት መፎካከር ይቻላል… ?ከእሷ መንጠቅ ወይም መስረቅ በየትኛው ሞራል….?
እንደውም ከዚህ በላይ ታሪካቸውን ማወቅ ፈለገች..ልታግዛቸው ፡፡ከቻለች ለመሞከር….ግን ዛሬ አይደለም… ሌላ ቀን …በዚህን ሰዓት በዚህ የጨፈገገ ስሜቷ ውስጥ ሆና ምንም ማድረግ አልቻለችም..አሁን እቤቷ ገብታ ጥቅልል ብላ መተኛት ብቻ ነው የምትፈልገው…መኪናዋን እያከነፈች ነው… ንስሯ ክንፉን እያርገፈገፈ ጨለማውን በመሰንጠቅ ከፊቷ ይከንፋል..ሁኔታው የደስታ ነው….መጀመሪያም አካሄዷ ደስ አላሰኘውም ነበር….ሀሳቧን ቀይራ በቁዘማም ቢሆን ወደቤቷ መመለሷ እሱን እያስፈነጠዘው ነው…፡፡
""""

ምቾት የሌላው ምሽት ነበር ያሳለፈችው….ደግሞ ርዝመቱ እንደተለመደው 11 ሰዓት ከእንቅልፏ ተነሳችና እቤቷ ውሰጥ የተወሰነ የሰውነት እንቅስቃሴ ከሰራች  በኃላ ወደበረንዳዋ ወጣች…ንሰሯ አብሯት ነበር የወጣው…..ለተወሰነ ደቂቃ ሀሳቧን ከራሷ ጋር ነበር ያደረገችው.. ኤርፎኗን ጆሮዋ ላይ ሰክታ ከሞባይሏ ለስለስ ያለ ሙዚቃ ከፍተችና  እያዳመጠች ንጽህ የጥዋት  አየር ወደ ሳንባዋ  እየማገች ነው፡፡

ግን በመረጋጋት ውስጥ ሆና በጽሞና ሙዚቃውን ብቻ ማዳመጡን  ቡዙም ልትዘልቀበት አልቻለችም..ሀሳቧ አሁንም ትናንት ላይ እንደተጣበቀ  ነው…የብልቷ መብላት ቢተዋትም አዕምሮዋ ግን አሁንም ድረስ እያሳከከት ነው….እሷ እኮ ወንድ ልጅን ለዚህን ያህል ጊዜ ርዝመት በልቧ አዝላ አታውቅም… ፎክራ ስላላሳካችው ዝታ  ስላልፈፀመች የመሸነፍ ቁጭት የፈጠረባት መብሰልሰል  ይሆናል……….?
አዎ ከንስር ጋር እየኖሩ ሽንፈትን አሜን ብሎ በመቀበል አንገትን መድፋት የማይታሰብ ነው…በምክንያቱም ለንስር መታገል.. ታግሎም ማሸነፍ ተፈጥሮ ያደለው የብቻ  ፀጋቸው ነው…ንስር የሞተ እንስሳ ንክች አያደርግም…የሚገድለውን ለማጥመድ ወይም ኢላማውን ለማግኘት መቶ ኪሎ ሜትር ሊያስስ ይችላል ..አስሶ አንዴ ራዳር ውስጥ ካስገባ ግን ንቅንቅ አይልም..ምንም ተአምር አያዘናጋውም…ግዳዩን ሳይጥል ውልፍች የለም…አዎ አድኖ አሳዶና ታግሎ በመጣል የገደለውን ብቻ ነው የሚበላው….፡፡እይታው ጠሊቅና እሩቅ ነው፡ካአለበት ቆሞ በአምስት ኪሎ ሜተር እርቀት ያለ ነገር ላይ ማነጣጠር ይችላል፡፡ልፋቱ የሌለበትን… አሸናፊነቱ የማይዘመርበትን ንክች አያደርግም… …ይህ የሰው ልጅም የህይወት መስመሩን ለማግኘት የተፈጠረበትን አለማ ለመገንዘብ የእድሜውን እሩብ ሊያባክን ይችላል…. ማባከኑም አግባብ ነው..መስመሩን ከያዘ በኃላ ግን አይኑም ቀልቡም መቶ ፐርሰንት መስመሩ ላይ መሆን አለበት፡፡ ትኩረቱም ጥረቱም ወደዛ ወደህይወት ግብ መዳረሻው የሚያደርሰው ሊሆን ይገባል…. የንስር ህይወት ይሄንን ነው የሚያስተምረው…
እሷም የሰለጠንችው  በንስራ ስለሆነ ኢላማ ያደረገችበትን  ነገር ከግብ ካላደረሰች ያማታል….አሁን እየተሰማት ያለው ስሜት ግን የተለየ ይመስላታል … ምክንያቱም  ከባሪያው ልጅ  ባልተናነሰ ቀዮ እጮኛውንም ከምናቧ ልታስወግዳት አልተቻለትም፡፡
‹‹አዎ መሞት የለባትም….በዚህ ዕድሜዋ መሞት አይገባትም››…ብላ በውስጧ ደመደመች…መልሳ ደግሞ እራሷን ሞገተች፡፡

‹‹ …በዚህ ዕድሜዋ መሞት የለባትም ስል ምን ማለቴ ነው..
…….?ሰው በስንት አመቱ ነው መሞት ያለበት……….?››ስትል አሰበች፡፡

ወጣት ሆኖ የሞተ ሰው ለምን በዛ ዕድሜዬ ሞትኩ ብሎ ይቆጫል ወይም ፈጣሪውን ይወቅሳል….? አይመስለኝም፡፡.ምን አልባት ይሄኛው አለም እና ከሞት ወዲያ ያለው ያኛው አለም ተብሎ ሚከፈል ዓለም ያለ ቢሆን እንኳን   ያኛው አለም  በእግዜር ሙሉ ቁጥጥር እና ፍቃድ የሚተዳደር ነው ሚሆነው..እንደዛ ከሆነ ደግሞ  ከዚህኛው  ዓለም ፍጽም የተሻለ ነው የሚሆነው..ያ ማለት ደግሞ ሞቶ ወደዛኛው አለም የተሸጋገረ ሰው በህፃንነቱም ሆነ በወጣትነቱ ቢሄድ ተገላገልኩ በምድር ከመሰቃየት፤ከመራብ፤ከመጠማት፤ከመጋዝና ከመታሰር እንኳንም በጊዜ ወደዚህ መጣሁ የሚል ይመስለኛል፡፡ሞት ማለት ሙሉ በሙሉ በስጋ መበስበስ እና በነፍስ መክሰም ወይም  ወደ ምንምነትም መቀየር ከሆነ  ደግሞ ለመፀፀት እና  ለምን ቶሎ ሞትኩ …….?ብሎ ለማሰብም የሚያስችል ዕድልም አይኖርም  ….ሞች በቋሚው አዕምሮ  ሲመዘን ነው በልጅነቱ ተቀጨ..በወጣትነቱ ተቀጠፈ የሚባለው….እና አሁንም እሷ የልጅቷ እሞታለሁ ማለት ለምን ይሄን ያህል እንዳሳሰባት አልገባትም .. …….?ነው ወይስ ለተመኘችው ልጅ ስትል ይሆናል..…….?
‹‹እሱ እንዲያዝንብኝ  ስላልፈለኩ ይሆን….?››ስትል እራሷን ትጠይቃለች ..ለጠየቀችው መልስ ከመፈለግ ይልቅ ግን  ሌላ ጥያቄ እየጨመረችበት ነው….
እሷ እንደሆነ በመግደልም ሆነ በማዳን አታምንም…እንደእሷ እምነት  ሰው የኖረበትን ጊዜ አጭርም ሆነ ረጅም ዋናው የኖረውን ያህል ተደስቶ መኖሩ ነው…..እርግጥ መግደል   የእግዜያብሄር  የአታድርግ ክልከላ ውስጥ ከሚካተቱ ትዕዛዞች መካከል አንዱ እንደሆነ ታውቃለች፡፡ቢሆንም ህይወት ከመግደልና ከመገደል ውጭ ህልውናዋ ፀንቶ እንደማይቆምም በተግባር አይታለች….ብዙ መግደል የቻለ ብዙ ይኖራል….ለመግደል የሰነፈ በጠንካራው ተገድሎ በሞቱ ለሌላው መኖር ምክንያት  ሆኖ ያልፋል፡፡ይሄንን ከህይወት ተምራለች፡፡

ግን እግዚያብሄር  አትግደል ሲል ለሰው ብቻ ነው እንዴ  የሚሰራው..…….?ሰውን መግደል ብቻ ነው በኃጥያት የሚያስጠይቀው….? ለምን ….?ሰው በእግዜያብሄር ሀምሳል  ስለተፈጠረ ልዩ መብት ስላለው….?፡፡ነው ወይስ ሰው የእግዜያብሄር ቤተ መቅደስ ነው የእግዜያብሄርን ቤተ መቅደስ ማፍረስ ደግሞ ያው ቀጥታ እሱን መዳፈር ነው…..ከእሱ ጋር መላተም ነው……ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ  ተብሎ ስለሚታሰብ…..?  …አትግደል የተባለው ነፍስ ያለውን ሁሉ ከሆነስ ……….?ያማ የማይቻል ከባድ ትዕዛዝ ይሆናል…፡፡ምክንያቱም እንስሳት ነፍስ አላቸው… ተክሎች ነፍስ አላቸው…ለመኖር ደግሞ ህይወት ያለው ነገር ሁሉ መመገብ  አለበት..ለመመገብ ደግሞ አንዱ ዝርያ ሌላውን እየበላ ነው ነፍሱን የሚያቆየው…ለመብላት ደግሞ የግድ መግደል