Ethio-Terit SACCOS Official Channel
445 subscribers
681 photos
39 videos
183 links
አልመው ይቆጥቡ አቅደው ይበደሩ!
Kaayyoon qusadhaa, karooraan liqeeffadhaa!

Save purposely, borrow strategically!
Download Telegram
Forwarded from Aboma Ejara
ኢትዮ ጥሪት ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/መ/ህ/ስ/ማህበር  22 አዳዲስና ብቃት ያላቸው ሰራተኞችን አወዳድሮ እና ተገቢውን ፈተና ፈትኖ ቀጠረ

አዲስአበባ 28/11/2017
👍2
Forwarded from Aboma Ejara
Aboma Ejara
ኢትዮ ጥሪት ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/መ/ህ/ስ/ማህበር  22 አዳዲስና ብቃት ያላቸው ሰራተኞችን አወዳድሮ እና ተገቢውን ፈተና ፈትኖ ቀጠረ አዲስአበባ 28/11/2017
ኢትዮ ጥሪት ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/መ/ህ/ስ/ማህበር  22 አዳዲስና ብቃት ያላቸው ሰራተኞችን አወዳድሮ እና ተገቢውን ፈተና ፈትኖ ቀጠረ

አዲስአበባ 28/11/2017

የደንበኞችን እርካታ ከፍ አድርጎ አገልግሎቱን ለማስፋት በዕቅድ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ኢትዮ ጥሪት  ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/መ/ህ/ስ/ማህበር  22 አዳዲስና ብቃት ያላቸው ሰራተኞችን በዛሬው ዕለት ወደ ማህበሩ በመቀላቀል የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አደረገላቸው።

  አዳዲስ የተቀጠሩት ሰራተኞችም በህግ፣ በማርኬቲንግ  ፣ በአካውንቲንግ ፣ በፋይናንስ እንዲሁም በአይሲቲ እና ቴክንሎጂ ዘርፎች የተረጋገጠ ዕውቀት እና ልምድ ያላቸው እንዲሁም ንቁ እና ቀልጣፋ እንደሆኑም በውድድሩ እና በፈተናው ተለይቷል።

  በእንኳን ደህና መጣችሁ ፕሮግራሙ ላይም የማህበሩ የስራ አስፈፃሚ አካላት ተገኝተው ትውውቅ አድርገዋል ።

  የማህበሩ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ እንደሻው ተገኝም ሰራተኞች ወደ ትልቅ እና ባለራዕይ ተቋም በመምጣታቸው ዕድለኛ እንደሆኑ እንዲሁም እያንዳንዱ ሰራተኛ የተቋም ባለቤት ፣ ቤተሰብ ፣ቆጣቢ ተበዳሪ እንዲሁም ኢንቬስተር እንደሚሆን ተናግረዋል ። ሁሉም ሰራተኞች በግብ እና በዕቅድ እየተመሩ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸውና የማህበሩ ነባር ሰራተኞችም ከጎናቸው እንደ ቤተሰብ እንደሚያግዙ ተናግረዋል ። አቶ እንደሻው አክለውም ሰራተኞች በታማኝነት እና በታታሪነት ሰርተው ማህበሩን ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያደርሱ መልዕክትም አደራም አስተላልፈዋል ።

  በመቀጠል ኢትዮ ጥሪት ለአዳዲስ ሰራተኞቹ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ስልጠና በመስጠት ስለማህበሩ አገልግሎትና እና አሰራር በተጨማሪም የስራ ባህል እንዲያውቁ ይደረጋልም ተብሏል። የስልጠናው ሳምንትም በዛሬው ዕለት ተጀምሯል ።

   ሰራተኞች እንኳን መሶቧ ወደ ሚያጠግበው በራዕይ እና በግብ ልጇቿን ወደምትመራው ውዷ እና ዕንቁዋ ኢትዮ ጥሪት በሰላም መጣችሁ ።🤝🤝🤝

    መልካም የስራ ዘመን ይሁንላችሁ 🙏
Forwarded from Aboma Ejara
Waldaan Hojii Gamtaa Qusannoo fi Liqii Itiyoo-Xirriit, tajaajiloota si'atoo fi quubsaa kennuuf hojjettoota haaraa qacareef leenjii kennuu eegale.

Finfinnee, 28/11/2017 ALI
2