Ethio Fm 107.8
20.3K subscribers
7.39K photos
16 videos
4 files
2.3K links
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Download Telegram
#ዉሻዎቻችሁን አስከትቡ!

በአዲስ አበባ የእብደት ዉሻ በሽታ ክትባት ተጀምሯል፡፡

በኢትዮጵያ የእብደት ዉሻ በሽታን በቀጣዮቹ ስምንት ዓመታት ለማጥፋትና ለመቆጣጠር በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ክትባት እየተሰጠ እንደሚገኝ የግብርና ሚንስቴር ተናግሯል፡፡

በሚኒስቴሩ የቬተርነሪ ፐብሊክ ሄልዝ ዳይሬክተር ዶክተር ሲሳይ ጌታቸው በሽታውን ለማጥፋትና ለመቆጣጠር የግንዛቤ ፈጠራ፣ የህዝብ ንቅናቄ ስራዎችና የውሾች ክትባት ዘመቻ ወሳኝ ነዉ ማለታቸዉን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።

በከተማዋ ባለቤት ያላቸውንና ባለቤት አልባ ውሾችን ለማስከተብ ስራዎች ተጀምረዋል፡፡

የክትባት ዘመቻው በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዲያመጣ ውሻ ያላቸው የከተማዋ ነዋሪዎች በሚቀጥሉት አምስት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ውሾቹን በኃላፊነት እንዲያስከትቡም ሚንስቴሩ ተጠይቋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም


Twitter https://twitter.com/EthioFM


YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።