Ethio Fm 107.8
19.6K subscribers
6.49K photos
16 videos
4 files
2.28K links
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Download Telegram
ሰርጌ ላቭሮቭ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው፡፡

በኢትዮጵያ የሚገኝው የሩስያ ኤምባሲ እንዳስታወቀዉ የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ፡፡

ኢምባሲው በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሐምሌ 19-20 ድረስ በአዲስ አበባ ቆይታ የሚያደርጉ ሲሆን የጉብኝታቸው ዋና ዓላማ እየተጠናከረ የመጣው የራሽያ -አፍሪካ ግንኙነት መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ያላቸውን ጉብኝት እንዳገባደዱ በራሽያ- አፍሪካ ጉባኤ ዝግጅት ዙሪያ ለጋዜጠኞች እና ለዲፕሎማቲክ አባላት ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም በኢምባሲው ግቢ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ጨምሮ ገልጿል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም
የዩክሬኗ ቀዳማዊት እመቤት አሜሪካን ተማጽነዋል፡፡

የዩክሬን ቀዳማዊት እመቤት ኦሌና ዜኔኒስካ የአሜሪካ ኮንገረስን አጥብቀው መማጸናቸው ተነግሯል፡፡

ኦሌና ኮንግረሱን የተማጸኑት ከፍተኛ የጦር መሳርያዎችን ለሀገራቸው እንዲሰጥ ነው ተብሏል፡፡
ከሩስያ ጋር እያደረግነው ያለነው ጦርነት ለኛ ብቻ አይደለም፣ እኛን ለመሳሰሉ ሀገራት ጭምር ነው ሲሉም ተናግረዋል ኦሌና፡፡

አሜሪካ ጦርነቱ ከተጀመረበት ቀን አንስቶ እጅግ ዘመናዊ የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ወደ ዩክሬን መላኳን የተናገሩት ቀዳማዊት እመቤቷ፣ አሁንም ተጨማሪ መሳርያ ያስፍልገናል ብለዋል፡፡
ከሩስያ ጋር በቀላሉ መዋጋት የሚቻል አይደለም፣ በመሆኑም በፍጥነት እርዳታችሁ ያስፈልገናለ ሲሉ ጥሪያቸውን አቀርበዋል፡፡

ኦላና ይህንን የተናገሩት በዋሽንግተን ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ላይ ነው፡፡
ቀዳማዊት እመቤቷ በተደጋጋሚ የጦር መሳርያ የጦር መሳርያ ሲሉ ጥሪያቸውን ለኮንግረሱ አሰምተዋል፡፡
የዩክሬን ቀዳማዊት እመቤት ከዚህ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ስለጦርነቱ ተጠይቀዉ በዚህ ምድር ላይ ባሌን ከኔ የሚነጥቀኝ ማንም የለም ጦርነትም ቢሆን ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡
አሁን ጦርነቱ እቤታቸው የደረሰ የመሰላቸው ቀዳማዊት እመቤቷ የድረሱልን ጥሪያቸውን እያሰሙ እንደሚገኙ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም
ፀሐይ ባንክ ሐምሌ 16 ቀን 2014 በይፋ ሥራ ጀምራለሁ ብሏል፡፡

ባንኩ በ2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር የተፈረመና በ734 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ተቋቁሟል፡፡

“ለሁሉ” በሚል መሪ ቃል የፊታችን ሐምሌ 16 ቀን 2014 በይፋ ሥራ እንደሚጀምር ያስታወቀው ባንኩ፣ ዝቅተኛ የአክሲዮን ግዢውን ከብር 100 ሺህ በመጀመር፣ በ373 ባለአክሲዮኖች መመስረቱን አስታውቋል፡፡

የመስራች ጉባኤውን የካቲት 11 ቀን 2013 በማካሄድ የባንክ ኢንዱስትሪውን መቀላቀሉን የባንኩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ያሬድ መስፍን አስታዉሰዋል፡፡

ዓላማችን የባንክ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን በፋይናንስ ዘርፉ በቂ ትኩረት ያላገኙትን የስራ ፈጠራን እና የስራ ፈጣሪዎችን፤ የጥቃቅንና አነስተኛ፣ የግብርናውን ዘርፍ እንዲሁም የአምራች ኢንዱስትሪውን ተደራሽ ለመሆን አልመናል ብለዋል፡፡
“ለሁሉም የሆነ ባንክ” እንዲሆን የአገልጋይነትን ዕሴትን ተላብሶ ሃምሌ 16 ስራ ይጀምራል የተባለው ባንኩ፣ በእለቱ 30 ቅርንጫፎች የባንክ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ተገልጿል፡፡

በቅርቡም ባንኩ የቅርንጫፎቹን ቁጥር ከ50 በላይ የማሳደግ እቅድ ያለው መሆኑን የገለፀ ሲሆን፣ በአንድ አመት ውስጥም በመላው የሃገራች አካባቢዎች 100 የሚሆኑ ቅርጫፎችን ወደ ስራ ለማስገባት ማቀዱን ባንኩ ይፋ አድርጓል፡፡

በአብዱሰላም አንሳር
ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም
የኩላሊት ታማሚዎች ለሚደረግላቸዉ የኩላሊት እጥበት በወር እስከ 42 ሽህ ይጠየቃሉ ተባለ፡፡

የኩላሊት ሕመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ፤በዓሁኑ ወቅት ለኩላሊት እጥበት የሚሰጠዉ ትኩረት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም በቂ ግን አይደለም ብለዋል፡፡
ህሙማኑ አሁንም ችግር ውስጥ መሆናቸውን አቶ ሰለሞን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

በድርጅቱ ዉስጥ የክልል እና ገጠር ከተሞችን ሳይጨምር በአዲስ አበባ ብቻ፣ ኩላሊት እጥበት የሚያከናውኑ ከ3 ሽህ 500 በላይ ታማሚዎች ይገኛሉ ነዉ ያሉት፡፡
እነዚህ ታማሚዎችም በግል ሆስፒታሎች ለአንድ ጊዜ እጥበት በትንሹ ከ1 ሽህ 950 እስከ 3 ሽህ 500 ብር በሳምንት ለሶስት ጊዜ እንደሚያወጡ ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡

ይህም በወር በትንሹ ከ23 ሺህ 400 እስከ 42 ሺህ ብር የሚጠጋ ወጭ ለኩላሊት ለዕጥበት እንደሚያወጡ ተናግረዋል፡፡
ሁሉም ነገር ዋጋዉ በጨመረበት በዚህ ወቅት እነዚህ ህሙማን የሚደርስባቸዉን የፋይናንስ ጫና ለማቃለል ሁሉም የቻለዉን ትብብርና ድጋፍ ቢያደርግ መልካም መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በረድኤት ገበየሁ

ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም
ትኩረት

የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦት፡-

የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አርብ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም በመካከለኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ መስመር ላይ የማሻሻያ ስራ ያከናውናል፡፡

በዚህም ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ድረስ በሲቪል ሰርቪስ ፊት ለፊት፣ በሲ ኤሚ ሲ ልዩ ቤቶች፣ በተባበሩት፣ በሲ ኤ ሚ ሲ ሚካኤል እና አካባቢዎች፤

እንዲሁም በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ በአያት 49 ማዞርያ፣ በአየር መንገድ ቤቶች፣ በአያት 2፣ 3፣ 4 ኮንደሚኒየም፣ በቦሌ አራብሳ እና አካባቢዎቻቸው ኤሌክትሪክ ይቋረጣል፡፡

በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞቹ ይህንን ተገንዝበዉ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም
የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በኮቪድ 19 መያዛቸዉ ተነገረ፡፡

ነጩ ቤተመንግስት በዛሬዉ እለት እንዳስታወቀዉ፣ባይደን በኮቪድ 19 መያዛቸዉ የተረጋገጠዉ በዛሬዉ እለት ነዉ፡፡

ፕሬዝዳንቱ የኮቪድ 19 ክትባትን በተሟላ መልኩ መዉሰዳቸዉና ማጠናከሪያ/ቡስተር/ ወስደዉ እንደነበርም ተነግሯል፡፡

የ79 ዓመቱ ባይደን በአሁኑ ወቅት ደረቅ ሳል፣ድካምና ሌሎች የህመም ስሜቶች እንደሚታዩባቸዉም ሲ ኤን ቢሲ ዘግቧል፡፡

በሙሉቀን አሰፋ
ሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም
Audio
የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 15-11-14
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ታጣቂዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸሙት ጭፍጨፋ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ አምነስቲ ጠየቀ፡፡

ድርጅቱ በጥቃቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደተገደሉ ከዓይን ምስክሮችና በሕይወት ከተረፉ ሰዎች ሰምቻለሁ ብሏል፡፡
የጥቃቱ ፈጻሚዎች የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መሆናቸውን ከጥቃት የተረፉ ሰዎች ነግረውኛል ሲልም አምነስቲ አክሏል።

ጥቃቱ እንደተጀመረ የአካባቢው አስተዳደር መረጃው ቢደርሰውም፣ መንገዱ ተዘግቷል በማለት ጸጥታ ኃይል ሳይልክ እንደቀረ አምነስቲ ከምንጮቹ ማረጋገጡን መጥቀሱን ዋዜማ ሬድዮ ዘግባለች፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም
ናይጂሪያ ሞተር ብስክሌትን ለደህንነት ስትል ልታግድ ነው፡፡

ናይጂሪያ ይህንን አይነት ውሳኔ ለመወሰን የተገደደችው በሞተር ብስክሌት እየተጓዙ ጥቃት የሚፈጽሙ እስላማዊ ታጣቂዎች በመበራከታቸው መሆኑ ተነግሯል፡፡
ይህ ወሳኔ የተሰማው ከቀናት በፊት በሞተር ብስክሌት የሚጓዙ ታጣቂዎች በሰሜን ምዕራብ የናይጄሪያ ግዛት ካትሲና ውስጥ፣ በተለያዩ ስፍራዎች ላይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች አምስት ፖሊሶችን ጨምሮ 17 ንጹሀን ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ነው፡፡

በዚሁ በያዝነው ሳምንት ረቡዕ ዕለት 300 የሚሆኑ በሞተር ብስክሌት የመጡ ታጣቂዎች ካንካራ በሚባል ቦታ ላይ የሚገኝን ፖሊስ ጣቢያ ኢላማ አድርገው ጥቃት ፈጽመዋል።
እንደ ቢቢሲ አፍሪቃ ዘገባ ከሆነ እነዚሁ ታጣቂዎች በፖሊስ ጣቢያው አቅራቢያ በሚገኝ አንድ መንደር ውስጥ በመግባት ሦስት ሰዎችን ገድለዋል፤ከብቶችን ጨምሮ ሌሎች ንብረቶችንም ዘርፈዋል።

በተመሳሳይ ሌላ ጥቃት ደግሞ ታጣቂዎች ፋሳካሪ በሚባለው አካባቢ በሚገኙ በርካታ መንደሮች ውስጥ በፈጸሙት ጥቃት ዘጠኝ ሰዎችን ገድለዋል፡፡

ካትሲና ግዛት በናይጄሪያ በታጣቂዎች ከፍተኛ ጥቃት ከሚፈጸምባቸው ቦታዎች አንዷ ስትሆን የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሙሐመዱ ቡሃሪ ትውልድ ስፍራ ናት።

በያይኔአበባ ሻምበል
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም
የሲራላካ ወታራዊ ሀይል የተቃውሞ ካምፖችን ወሯል ..የተቃውሞ መሪዎችንም ማሰራቸው ተሰምቷል፡፡

ተቃዋሚዎች አርብ ማለዳ ላይ ወታደሮች የዋና ከተማዋ ኮሎምቦ አከባቢዎችን ከተቁጣጠሩ በኃላ፣ በአንዳንዱች ላይ 'በአሰቃቂ ሁኔታ ጥቃት ደርሶባቸዋል' ብለዋል።
በስሪላንካ የሚገኘው ጦር በተቃዋሚዎች ላይ ጭካኔ በተሞላበት ሆኔታ ድብደባን ከፈጸመ በኋላ በዋና ከተማው የሚገኘውን የፕሬዚዳንቱን ሴክሬታሪያት ተቆጣጥሯል።
በጎታጎጋማ የተቃውሞ ቦታ ላይ በወታደሮቹ በርካታ ድንኳኖች ወድመዋል፣ከ100 በላይ የተቃውሞ ሰልፈኞች ታስረዋል፤ በርካቱችም ተከበዋል ብሏል፤ የአልጀዚራ ዘገባ፡፡
የሲሪላንካው አዲሱ ፕሬዝዳንት ራኒል ዊክርሜሲንግህ በመላው አገሪቱ የሚጸና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጃቸው ብዙዎችን ያስቆጣ ነበር።

ይህን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች ተላልፈውታል። በወቅቱ ዊክርሜሲንግህ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተላለፉትን “ፋሺስቶች” ሲሉ ጠርተዋቸዋል።

ፕሬዝደንቱ ጨምረውም ወታደራዊ ኃይሉ የሀገሪቱን ሰላም እና ጸጥታ እንዲያስጠብቅ መመሪያ ማሳለፋቸውን ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ የተጠናከረ የቁጥጥር ስራ እየተሰራ ስለመሆኑ አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

በያይኔአበባ ሻምበል
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም
በኦሪገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 800 ሜትር ግማሽ ፍፃሜ ውድድር ድርቤ ወልተጂ ወደ ፍፃሜ አልፋለች።
ፀሐይ ባንክ በዛሬዉ እለት በይፋ ስራ ጀምሯል፡፡

ባንኩ በ30 ቅርንጫፎቹ ዛሬ ወደ ስራ መግባቱን ነዉ ያስታወቀዉ፡፡

ባንኩ በ2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር የተፈረመና በ734 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ተቋቁሟል፡፡
“ለሁሉ” በሚል መሪ ቃል ዛሬ ሐምሌ 16 ቀን 2014 በይፋ ሥራ የጀመረዉ ባንኩ፣ ዝቅተኛ የአክሲዮን ግዢውን ከብር 100 ሺህ በመጀመር፣ በ373 ባለአክሲዮኖች መመስረቱን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

“ለሁሉም የሆነ ባንክ” እንዲሆን የአገልጋይነትን ዕሴትን ተላብሶ ስራ ጀምሯል የተባለው ባንኩ፣ ዛሬ 30 ቅርንጫፎች የባንክ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ተገልጿል፡፡
በምረቃ ስነስርአቱ ላይ የተገኙት የብሄራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ፣30 ባንክ እና 40 የማይክኦሮ በአጠቃላይ ከ80 በላይ የፋይናንስ ተቋማት እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡
የባንኮች ተልእኮ የህዝብን የቁጠባ ባህል ለማዳበር እና የብድር አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ መሆኑን ጠቁመዉ፣ በአሁኑ ወቅት ለባንኮች በገበያ ደረጃ የሚያሳስብ ነገር እንደሌለም አመልክተዋል፡፡

ዘግይተው ገበያውን የተቀላቀሉ ባንኮች በቀላሉ ስኬታማ መሆን የሚችሉበት የቴክኖሎጂ ዘመን ላይ እንገኛለን ያሉት ዋና ገዥዉ፣
ገበያው ለውጭ ባንኮች የሚከፈት መሆኑ አይቀሬ በመሆኑ ለሚገጥማቸዉ ዉድድር ራሳቸዉን አዘጋጅተዉ እንዲጠብቁም አሳስበዋል፡፡
ጸሃይ ባንክ በይፋ ስራ መጀመሩን ምክንያት በማድረግ ለ4 ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ማለትም፤
ለጌርጌሴኖን 300ሺህ ብር፣ለኒያ ፋውንዴሽን 300ሺህ ብር፣ለኩላሊት ህመምተኞች በጎአድራጎት ድርጅት 500ሺህ ብር እንዲሁም ለኢትዮጲያ የልብ ህሙማን ማእከል 500ሺህ ብር የስጦታ ገንዘብ አበርክቷል፡፡

በአብዱሰላም አንሳር
ሐምሌ 16 ቀን 2014 ዓ.ም
የአላሰካ አየር መንገድ በረራ በአብራሪዎቹ ጸብ ምንክኒያት መዝግየቱ ተገለጸ።

ከዋሽንግተን ተነስቶ ወደ ሳንፍራንሲስኮ ሊበር የነበረዉ የአላስካ አዉሮፕላን ቦይንግ 737 በአብራሪቹ ፀብ ምክንያት ወደ ተርሚናሉ እንዲመለስና ተጨማሪ ሰአት እንዲዘይ መገደዱን አየር መንገዱ አስታውቋል ፡፡

ጸቡ ሲፈጠር ተሳፋሪዎች በአዉሮፕላኑ ውስጥ ሆነው ጉዟቸውን ሲጠባበቁ ነበር።

7፡05 የበረራ ሰአቱን ይጨርሳል የተባለዉ አዉሮፕላን ከታቀደለት ሰአት ዉጪ ሁለት ሰአት በመዘግየት 9፡34 በረራዉን አጠናቋል ነው የተባለው።

ካፒቴኑና የመጀመሪያ መኮንኑ ለምን በረራዉ ዉስጥ ጸብ እንደተፈጠሩ ግልጽ ምክንያት አልተነገረም።

አየር መንገዱ ግን ድርጊቱን የሙያ አለመግባባት በማለት ጉዳዩን ቀለል ለማድረግ መሞከሩን ሀፊንግተን ፖስት ዘግቧል።

በቤዛዊት አራጌ
ሐምሌ 16 ቀን 2014 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
ዌብሳይት https://ethiofm107.com/
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
በኬንያ የድምጽ መሰብሰብ ሂደቱን ለማጨበርበር ሙከራ ያደረጉ ሶስት ባለሞያዎች በቁጥጥር ስራ ዋሉ፡፡

በኬኒያ ሊደረግ ከታሰበው ሃገራዊ ምርጫ ቀደም ብሎ በሚሰበሰበው ድምጽ ላይ የማጭበርበር ሙከራ ያደረጉ ሶስት ተጥርጣሪዎች በሃገሪቱ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ተነግሯል፡፡

የምርጫ ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው፣ ተጠርጣሪዎቹ “ስማርት ማቲ” የተባለ የምርጫ ቴክኖሎጂ ድርጅት ሰራተኞች ናቸው፡፡
ኮሚሽኑ አክሎም በፈረንጆቹ ነሃሴ 9 ከሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ ቀደም ብሎ የተሰበሰበው ድምጽ በርካታ ትችቶች እየተሰነዘሩበት ይገኛል፡፡

ከዚህም የተነሳ ተጠርጣሪዎቹ ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ ከሆነ ከፍተኛ ቅጣት እንደሚጥብቃቸው ዘገባው አመላክቷል፡፡
በሌላ በኩል የተጠርጣሪዎቹ ለእስር መዳረግ በምርጫው ላይ ከፍተኛ የሆነ ውጥረትን ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋቶች እየተሰሙ መሆኑ ተግልጿል።

በዚህ ድርጊት ላይ ተሳታፊ ናቸው ከተባሉ ሰዎች መካከል እንዱ የውጪ ሃገር ዜጋ ሲሆን፤ስለተቀሩት ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ግን የተባለ ነገር እንደሌለ የአልጀዚራ ዘገባ አመላክቷል፡፡

በመሳይ ገ/መድህን
ሐምሌ 16 ቀን 2014 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
ዌብሳይት https://ethiofm107.com/
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።