ETHIO-MEREJA®
130K subscribers
23.4K photos
447 videos
22 files
11.7K links
Addisababa, Ethiopia🇪🇹

News & Media Company®
.

USA : Washington

.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot
Download Telegram
#Wanted - በወንጀል ይፈለጋሉ!!

እነዚህ ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቷቸው ግለሰቦች አቶ አብዩ በየነ ዋሴ እና አቶ ሰይድ ኢብራሂም አሊ (ቅፅል ስም ጀሚ) በከባድ የማጭበርበር ወንጀል ይፈለጋሉ፡፡

ስለሆነም እነዚህን ግለሰቦች በአካባቢያችሁ ካያችሁ እንድታሳውቁን እያለ የተለመደውን የህብረተሰቡን ትብብር ይጠይቃል፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ

ስ.ቁ
👉0115309002
👉 0115309039
ዘወትር በስራ ሰዓት ከ 2፡30-11፡30

እንዲሁም
👉0111711012
👉0111119475
በማንኛዉም ሰዓት ይደውሉ ሲል ፖሊስ አስታውቋል።
    T.me/ethio_mereja
     
@ethio_mereja
"አርበኛ ዘመነን በተመለከተ የመንግስት አመራሮች በሰከነና በተጀመረው መንገድ በሽምግልና እንዲያልቅ ቢያደርጉ ጥቅሙ በዋናነት ለመንግስት መሆኑን ማስታወስ እፈልጋለሁ። ከዚህ ያለፈው ነገር የሽምግልና ወግና ሥርዓቱንም ዋጋ የሚያሳጣ ነው። በተከበረው የአማራ ሕዝብ የሽምግልና እሴት ላይም መዘባበት ይሆናል።

ወንድማችን ዘመነ የማንደራደርበት የሕዝብ ልጅ መሆኑን ግን ሁሉም ሊያውቀው ይገባል።"

--የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ታደለ
የእንደራሴዎች ምክር ቤት አባል---

    T.me/ethio_mereja
      @ethio_mereja
ፀደይ ባንክ በ11 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ካፒታል ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ!

አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከተቋቋመበት 1989 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ለህብረተሰቡ ሰፊ የቁጠባና የብድር አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶ ወደ ፀደይ ባንክ ማደጉም ነው የተገለጸው፡፡

የፀደይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መኮንን የለውምወሰን በሰጡት መግለጫ ባንኩ 11 ቢሊዮን ጠቅላላ ካፒታል እና ዘመናዊ ቴክኖሎጅን በመያዝ ወደ ሥራ እንደገባ ገልጸዋል፡፡ ትርጉም ያለው መረጃ ለባንክ ኢንዱስትሪው አስፈላጊ በመሆኑ ባንኩ 270 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ዘመናዊ የመረጃ ማዕከል ገንብቶ ስራ መጀመሩንም አንስተዋል፡፡

የባንኩ የቦርድ ሊቀመንበር ገዱ አንዳርጋቸው በበኩላቸው ፀደይ ባንክ ክፍተት የማይፈጥር የቴክኖሎጅ አቅም በመያዝ ሥራውን በተወዳዳሪነት እንደሚያከናውን አመላክተዋል። ባንኩ 148 ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች እንዳለው የገለጹት ሊቀመንበሩ በዓመቱ መጨረሻ ወደ 300 ከፍ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነና በቀጣይ በሁሉም ከተሞች ቅርንጫፎችን ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ጸደይ ባንክ የፊታችን ቅዳሜ በይፋ ስራ ይጀመራልም ነው የተባለው።
ጤና ይስጥልን ነቫ ኮምፒውተር እንባላለን።ጥሩ ላፕቶፕ ለመግዛት አሰበዋል?እንግዲያውስ ነቫ ኮምፒውተር አለሎት
👉እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የ2021/2022 ሞዴል ላፕቶፖችን፣የተለያዩ ጌሚንግ እንዲሁም ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች ከ አስተማማኝ ዋስትና እንዲሁም ከ በቂ መስተንግዶው ጋር ይዘን እንጠብቆታለን
ይህን ሊንክ በ መጫን የሚፈልጉትን ላፕቶፕ ከቴሌግራማችን ይመረጡ👇ጆይን ያርጉ

https://t.me/nevacomputer

ቀድመው ይደውሉ
☎️+251912759900
+251920153333


👉አድራሻ:- አዲስአበባ፣ መገናኛ ማራቶን የገበያ ማእከል(አትሌት ሃይሌ ህንጻ)ምድር ላይ በ ዋናው በር መግቢያ ፊት ለፊት እንገኛለን።Neva computer ማለቱን ያረጋግጡ።
❇️ 2pcs Silicone Dish Washing Glove
💯 High Quality

👉አመቺና ቀላል ጽዳት ማጠቢያ ጓንት
🍀በፅዳት ወቅት እጅዎ በሳሙና እና በውሀ ብዛት🚿 እንዳይጎዳ የሚከላክል እጅግ አስፈላጊ ጓንት🧤የሚለጠጥ

#በቀላሉ👇
🌷እቃዎችን🍽 ወለሎችን🌫፣ መኪናን🚗፣ የቤት እንሰሳትን🐩🐈 ለማጠብ የሚያስችልዎ
🍀 ከፍተኛ ሙቀት መቋቋም የሚችል

በጣም ምርጥ እና የእጆን ውበት እና ጤንነት ለመጠበቅ የሚረዳ ፍቱን መላ።
💦 ዋጋ፦ 599 ብር

️ በስልክ :- 0901882392
💬 በTelegram @antenehg1
👉 @em_gebeya
🚧የchannel ጥቆማ ‼️

~በ ስልክዎ ላይ የሚወጡትን የተረጋገጡ

~ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣

~ የግንባታ ጨረታዎች፣

~ የግንባታ ዕቃዎችን ወቅታዊ ዋጋ፣

~software course በdiscount ለማገኘት

~design እንሰራለን ,የconsulting አገልግሎት በነፃ እንሰጣለን

~እነዚህን እና የተለያዩ የኮንስትራክሽን ዘርፍ
ባለሙያዎችን አድራሻ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማገኘት ይቀላቀሉ‼️

👇👇

https://t.me/ethioengineers1

https://t.me/ethioengineers1
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ!!

የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያና ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ:-

2014/15 የኢትዮ ዩኒቨርሲቲ መግቢያና
የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደ ተመደቡበት ካምፖስ ጉዞ ሲያደርጉ #መያዝ #የተፈቀደላቸው#መያዝ #የተከለከሉ እና #የጊዜ #ሠሌዳ እንደሚከተለው ያለው ሲሆን ተማሪዎች ከወዲሁ ራሣችሁን እንድታዘጋጁ ይሁን።

#መያዝ #የተፈቀደላቸው
✡️አንሶላ፣
✡️ትራስ ጨርቅ፣
✡️የማታ ልብስ፣
✡️ደረቅ ምግብ፣
✡️ልብስ፣ቦርሳ፣
✡️የመፈተኛ ካርድ፣እርሳስ፣ላጲስ፣የማስታወሻ ደብተር፣ባዶ ወረቀት፤መጽሐፍ

❷፣#መያዝ #የተከለከሉ
☸️ማንኛውም ድምፅ የሚቀዳ፤ቪዲዮ የሚቀዳ ወይም ፎቶግራፍ የሚያነሳ፤
☸️ካሜራ
☸️ማንኛውም ከቴሌ መስመርም ይሁን ከቴሌ ውጭ መልዕክት በድጂታል ቴክኖሎጂ መቀበያ ወይም ማስተላለፊያ ውጤቶች(ታብሌት፣ኮሚፕዩተር፣ላብቶፕ፣ ስልክ፣አይፓድ፥ሃርድ ዲስክ፣ፍላሽ)

#የጊዜ #ሠሌዳ
✡️ማህበራዊ ሳይንስ $social science dep't
➤26_28/1/2015 ዩኒቨርስቲ መግቢያ
➤29/01/2015 ኦሬንተሽን
➤30/01/2015_02/02/2015 ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ይሆናል።

✡️የተፈጥሮ ሳይንስ Natural Science dep't
➤05_06/2/2015 ዩኒቨርስቲ መግቢያ
➤07/02/2015 ኦሬንተሽን
➤08/02/2015_11/02/2015 ፈተናው
የሚሰጥበት ጊዜ ይሆናል።

ተማሪዎች መረጃው እንዲደርሳቸው ሼር ያድርጉ።
መረጃው ከትምህርት ሚኒስተር ነው የተገኘው።
    T.me/ethio_mereja
     
@ethio_mereja
ዘመነ ካሴ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ10 ቀናት ቀጠሮ ተሰጠው!!

በትላንትናው እለት በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋለው ዘመነ ካሴ በከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ከሰዓት ቀርቧል።

ትላንትና በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋለው ዘመነ ካሴ ፍርድ ቤት ቀርቦ የአስር ቀናት ቀጠሮ የተሰጠው ሲሆን ምርመራውን የያዘው የክልሉ ፖሊስ ዘመነ ካሴን "ህገ ወጥ ቡድን በማደራጀት እና "ኬላ ዘርግቶ ገንዘብ በመሰብሰብ" እንዲሁም "በፌስ ቡክ ቅስቀሳ ማድረግ" በሚሉ ወንጀሎች ጠርጥሬዋለሁ በማለት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

የዘመነ ካሴ ጠበቆችም እነዚህን ወንጀሎች ለማጣራት በሚል ፖሊስ ላለፉት አራት ወራት ምርመራ ያደረገ መሆኑን እና ሌሎችን መከራከሪያዎችን በማቅረብ የጊዜ ቀጠሮ መስጠት ሳያስፈልግ አርበኛ ዘመነ በዋስ እንዲለቀቅ ጥያቄ አቅርበዋል።

ፍርድ ቤቱ የምርመራ ቡድኑ ያቀረበው ምክንያት በቂ አለመሆኑን ጠቅሶ የ10 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ በመስጠት ፖሊስ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
    T.me/ethio_mereja
     
@ethio_mereja
ትግራይ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ 72 አገር ዓቀፍና ክልላዊ ሲቪል ማኅበራት መንግሥትና ሕወሃት የሚያካሂዱትን ጦርነት አቁመው ንግግር እንዲጀምሩ በጋራ መግለጫቸው ጥሪ ማድረጋቸውን ዶቸቨለ ዘግቧል።

ከነሐሴ ወዲህ የተቋረጠው የዕርዳታ እህል እንደገና ወደ ትግራይ መግባት እንዲጀምር፣ "የሰብዓዊ ዕርዳታ ኮርደሮች እንዲከፈቱ" ሲቪል ማኅበራቱ ጠይቀዋል። ሲቪል ማኅበራቱ በቅርቡ በአዲስ አበባ 35 ሲቪል ማኅበራት በጋራ ያቀረቡትን የሰላም ጥሪ አድንቀዋል። ከሽራሮና ሌሎች ከኤርትራ ድንበር አቅራቢያዎች በሚካሄደው ውጊያ ሳቢያ በርካታ የክልሉ ነዋሪዎች እየተፈናቀሉ መሆኑን ማኅበራቱ በመግለጫቸው ጠቅሰዋል።

በሌላ ዜና አውሮፓ ኅብረት "የኤርትራ ወታደሮች ወደ ትግራይ ክልል ገብተዋል መባሉ ግጭቱን ይበልጥ ያባብሳል" ሲል ስጋቱን ገልጧል። ይህንኑ ስጋታቸውን በትዊተር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የገለጡት፣ የኅብረቱ ኮሚሽን የውጭ ጉዳዮችና የጸጥታ ፖሊሲ ሃላፊ ጆሴፕ ቦሬል ናቸው።ቦሬል "አውሮፓ ኅብረት አሁንም ሁሉም ወገኖች ልዩነታቸውን በወታደራዊ መፍትሄዎች ለመፍታት የሚከተሉትን አካሄድ ርግፍ አድርገው በመተው ለሕዝባቸው ሲሉ ለሰላም እንዲሰሩ ጥሪ ያደርጋል" ብለዋል።
    T.me/ethio_mereja
     
@ethio_mereja
🚧የchannel ጥቆማ ‼️

~በ ስልክዎ ላይ የሚወጡትን የተረጋገጡ

~ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣

~ የግንባታ ጨረታዎች፣

~ የግንባታ ዕቃዎችን ወቅታዊ ዋጋ፣

~software course በdiscount ለማገኘት

~design እንሰራለን ,የconsulting አገልግሎት በነፃ እንሰጣለን

~እነዚህን እና የተለያዩ የኮንስትራክሽን ዘርፍ
ባለሙያዎችን አድራሻ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማገኘት ይቀላቀሉ‼️
👇👇

https://t.me/ethioengineers1

https://t.me/ethioengineers1
ጤና ይስጥልን ነቫ ኮምፒውተር እንባላለን።ጥሩ ላፕቶፕ ለመግዛት አሰበዋል?እንግዲያውስ ነቫ ኮምፒውተር አለሎት
👉እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የ2021/2022 ሞዴል ላፕቶፖችን፣የተለያዩ ጌሚንግ እንዲሁም ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች ከ አስተማማኝ ዋስትና እንዲሁም ከ በቂ መስተንግዶው ጋር ይዘን እንጠብቆታለን
ይህን ሊንክ በ መጫን የሚፈልጉትን ላፕቶፕ ከቴሌግራማችን ይመረጡ👇ጆይን ያርጉ

https://t.me/nevacomputer

ቀድመው ይደውሉ
☎️+251912759900
+251920153333


👉አድራሻ:- አዲስአበባ፣ መገናኛ ማራቶን የገበያ ማእከል(አትሌት ሃይሌ ህንጻ)ምድር ላይ በ ዋናው በር መግቢያ ፊት ለፊት እንገኛለን።Neva computer ማለቱን ያረጋግጡ።
ከመፈተኛ ዩኒቨርሲቲዎች ለራቁ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የትራንስፖርት ወጪ እንደሚሸፈን ተገለጸ

ከመፈተኛ ዩኒቨርሲቲ ከ50 ኪሎ ሜትር በላይ ለሆነ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የትራንስፖርት ወጪን ትምህርት ቤቶቻቸው የሚገኙባቸው ወረዳዎች እንደሚሸፍኑ ተገለጸ፡፡

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 በኹለት ዙር ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።

በዚህም ፈተና ማተምን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች ከወዲሁ መጠናቀቃቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ለኤፍ ቢ ሲ ተናግረዋል። ትራንስፖርትን በተመለከትም ከመፈተኛ ዩኒቨርሲቲዎች በ50 ኪሎሜትር ርቀት ውስጥ ያሉ ተፈታኝ ተማሪዎች ወጪን በራሳቸው እንደሚሸፍኑም ተገልጿል።

ሆኖም ከ50 ኪሎ ሜትር ርቀት በላይ የሚገኙ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርት ቤቶቻቸው የሚገኙባቸው ወረዳዎች እንደሚያመቻቹም ተጠቁሟል፡፡
    T.me/ethio_mereja
     
@ethio_mereja
ሩሲያ አውሮፓንና አሜሪካን በሀይፐርሶኒክ ሚሳኤል ልትመታ እንደምትችል አስጠነቀቀች!!

ሰባት ወራትን ያስቆጠረው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት አሁን ደግሞ አዳዲስ ክስተቶችን ወደ ማስተናገድ በመሸጋገር ላይ ይገኛል።

.......
በአሜሪካ እና ምዕራባዊያን የጦር መሳሪያ እርዳታ በመታገዝ ዩክሬን በሩሲያ የተያዙ ግዛቶችን በማስለቀቅ ላይ ስትሆን ሩሲያ ደግሞ አራት የዩክሬን ግዛቶችን ወደ ራሷ ለመጠቅለል ከዛሬ ጀምሮ ህዝበ ውሳኔ ታካሂዳለች።

ለዚህ ተልዕኮዋ እንዲረዳትም 300 ሺህ ተጠባባቂ ጦሯን የጠራችው ሩሲያ ብሄራዊ ደህንነቷ ስጋት ውስጥ ከገባ ደግሞ የኑክሌር ጦሯን ጨምሮ ማንኛውንም መንገድ እንደምትጠቀም ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናግረዋል።

የሩሲያን አዲስ ውሳኔ ተከትሎ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት እና ኔቶ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ በመስጠት ላይ ሲሆኑ በአውሮፓ የተሰማራው የቀድሞው የአሜሪካ ጦር ጀነራል ቤን ሆጅስ ሩሲያ የምትመካበትን ጦር ኔቶ ማውደም ይችላል ብለዋል። ሩሲያ በዩክሬን ኑክሌር ጦር ከተጠቀመች ሞስኮ የምትመካበት እና በጥቁር ባህር ላይ ያሰፈረችው ጦር አውሮፓ ያለው የአሜሪካ ጦር ሊያወድመው ይችላል ሲሉ ተናግረዋል።

የሩሲያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት እና የአሁኑ የሀገሪቱ ምክትል የጸጥታ ሀላፊ  ለአሜሪካው የጦር ጀነራል አስተያየት ምላሽ ሰጥተዋል።ሩሲያ ሀይፐር ሶኒክ በተሰኘው ሚሳኤል ብቻ የአውሮፓ እና አሜሪካ ከተሞችን ልትመታ እንደምትችል አስጠንቅቀዋል ሲል ራሺያን ቱዴይ ዘግቧል።
የ6 ዓመት ሕፃን በማገት 200 ሺህ ብር የጠየቀው ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ!

የ6 ዓመት ሕፃን በማገት 200 ሺህ ብር የጠየቀው ግለሰብ በቁጥጥር ሰር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የሸኔ አባል እንደሆነ የተጠረጠረው ግለሰቡ የ6 ዓመት ሕፃን በማገት 200 ሺ ብር ከሕጻኑ ወላጆች በመቀበል ልጁን ሆለታ ከተማ ጫካ ውስጥ ጥሎ መሄዱ ተገልጿል፡፡ ከዚያም ዘነበ ወርቅ መናኸሪያ በመሳፈር ወደ ጅማ ከተማ ሊያመልጥ ሲል በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ጅማ በር ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ሥር መዋሉን የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገብሬ መሰል ወንጀሎችን ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ የሚፈፅሙ ፀጉረ ልውጦች በመኖራቸው ማህበረሰቡ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
    T.me/ethio_mereja
     
@ethio_mereja
ባህር ዳር ከተማ በጸሃይ ብርሃን የሚሰሩ የመንገድ ላይ መብራቶችን መገንባት ጀመረች፡፡

በከተማዋ በጸሃይ ብርሃን ወይም ሶላር ሲስተም የሚሰሩ እና 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የመንገድ ላይ መብራቶችን ግንባታ እንደተጀመረ የከተማዋ ኮሙኒካሽን አስታዉቋል፡፡

ከሃያ አራት ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ወጪ የሚደረገበት በከተማው አምስት ቦታዎች ላይ የመንገድ ላይ መብራቶችን ግንባታ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ዶክተር ድረስ ሳህሉ አስጀምረዋል። ይህም የባህርዳር መንገዶችን ምንጊዜም መብራታቸው የማይጠፋ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል፡፡
    T.me/ethio_mereja
      @ethio_mereja