EECMY Youth Ministry
1.83K subscribers
3.51K photos
8 videos
269 links
Fellowship - Discipleship - Evangelism

1Thimothy 4:12

This is the official telegram channel of EECMY Head Office - Youth Ministry
Download Telegram
ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን!

"ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ: ይህንም አዘውትር።"
1ጢሞ. 4:15

#EECMY #SouthSynod #ChildrenandYouthMinistry #Training #Dilla
https://t.me/eecmyyouthministry
https://t.me/MYSundaySchool
የልጆች  እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች ስልጠና በደቡብ ሲኖዶስ- ዲላ

Children & Youth Ministry Leaders Training @EECMY South Synod- Dilla

LEENJII TAJAAJILTOOTA IJOOLLEE FI DARGAGGOO SINOODOOSII KIBBAATTI- DIILLAA


''የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤ ...'' ነህምያ 2:20

"...Nuuti garbooti Isaa kaanee ijaaruu ni jalqabna, Waaqayyo Gooftaan samii immoo nuuf qajeelcha;..." Nah. 2:20


"“The God of heaven will give us success. We His servants will start rebuilding,...” Neh. 2:20

👇👇👇
#EECMY #SouthSynod #Dilla #Children #Youth #Leadership #Training
t.me/eecmyyouthministry
https://t.me/MYSundaySchool
EECMY Youth Ministry
Photo
የልጆች  እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች ስልጠና በደቡብ ሲኖዶስ- ዲላ
Children & Youth Ministry Leaders Training @EECMY South Synod- Dilla
                          * *      * * *     * *
የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ደቡብ ሲኖዶስ መሪዎች እና ከሲኖዶሱ ሰበካዎች እና ማ/ምዕመናናት ለመጡት የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት አስተባባሪዎች "ሁለንተናዊ ዕድገት እና ለውጥ" በሚል ርዕስ ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ ላይ መሰረት በማድረግ ስልጠና ተሰጥቷል: በተጨማሪም ከስልጠናው በኋላ ለመላው ምእመናን በቤተሰብና በልጆች እድገት ላይ በዲላ ማ/ም ትምህርት ተሰጥቷል። ስልጠናውን የሰጡት የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሣ ሲሆኑ: የሲኖዶሱ ፕረዝደንት ቄስ ወልዴ አየለም በስልጠናው በመገኘት ለልጆች እና ወጣት አገልግሎት መሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል:: ከስልጠናው ጎን ለጎን ለሁለንተናዊ አገልግሎቱ የሚጠቅም የልጆች አገልግሎት እንዲሁም ለወጣቶች እና አጠቃላይ የቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚሆኑ መጽሐፍት በቤተክርስቲያኒቱ የምስራች ድምጽ በኩል ተሰራጭቷል:: በተጨማሪም የስልጠናው ሞጁል እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን: በስልጠናው ማጠቃለያ በአጠቃላይ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ላይ ውይይት ተካሂዷል:: ሰልጣኞች የወሰዱትን ስልጠና ወደየ ማ/ምዕመናኖቻቸው በማውረድ የሚተገብሩት ይሆናል::

ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን!

''የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤ ...'' ነህምያ 2:20
                          * *      * * *     * *

The Children and Youth Ministry Department of the Ethiopian Evangelical Church Mekane gave training for the South Synod (Dilla) coordinators of the children and youth ministries from the synod parishes and the congregations based on the Wholistic Ministry Package of Children and Youth of the EECMY entitled "Wholistic Growth and Transformation." The training was given by the Director of the church's children and youth ministry department, Brother Wondmagegn Udessa. After the training, he gave teachings on family and child development to all believers @Dilla Congregation. The President of the Synod, Rev. Wolde Ayele delivered a message to the leaders of the children and youth ministry of the synod. Beside the training, different books that will help for the holistic children and youth ministry and overall church service are distributed to the trainers through the EECMY Yemisrach Dimts Communication Service , and the module of the training, 'Wholistic Ministry Package of Children and Youth', is distributed to them. At the conclusion of the training, a discussion was held on the overall ministries of children and youth of the church. The trainees will apply the training they have received to their respective congregations.

Wholistic Growth and Transformation for Our Children and Youth!

"“The God of heaven will give us success. We His servants will start rebuilding,...” Neh. 2:20

Photo Credit: South Synod Media, Dilla

#EECMY #SouthSynod #Dilla
#Children #Youth #Leadership #Training
t.me/eecmyyouthministry
https://t.me/MYSundaySchool
ልጆች እና ወጣቶች ላይ መስራት በዛሬዋና በነገዋ ቤ/ክ ላይ መስራት ነው!
The SundayService@EECMY; #Dilla Congregation
===
"ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም" እንደሚለው የእግዚአብሔር ቃል (ምሳሌ 22:6): ልጆችን በትክክለኛው እና በእውነተኛው የዕድገት አቅጣጫ ለመምራት የልጆች አገልግሎትን በሚገባ ማደራጀት: የልጆች መምህራንን መደገፍ: እንዲሁም ቤተሰብን በአገልግሎቱ ማሳተፍ አስፈላጊ እና ወሳኝ ነው::

-ልጆች እና ወጣቶች የዛሬ/የአሁን እና የነገ/የወደፊት ቤተክርስቲያን ናቸው::
-ልጆች እና ወጣቶች የሌሉባት ቤተ ክርስቲያን የሞተች ናት::
-ነባሩን እና የሚመጣውን ውስብስብ ዓለም (ዘመናዊነት) እንዲቋቋሙ እና እንዲያልፉ በጊዜው በቃሉ እውነት ማስታጠቅ አስፈላጊ ነው::
-ልጆች ከአዋቂዎች የበለጠ በቀላሉ የሚነኩበት የልጅነት የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በጣም አስፈላጊ ስለሆኑ ትኩረት ሰጥቶ: ቀድሞ በእነርሱ ላይ መስራት አስፈላጊ ነው::

"ልጆች ሆይ፥ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ፥ ይህ የሚገባ ነውና።መልካም እንዲሆንልህ ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም አባትህንና እናትህን አክብር፤ እርስዋም የተስፋ ቃል ያላት ፊተኛይቱ ትእዛዝ ናት። እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጡአቸው።" ኤፌ. 6:1-4

Equipping Family in a Holistic Way (Children, Youth & Parents)

📷: EECMY Dilla Congregation Media

#EECMY #SouthSynod #Dilla #Leadership #Training #Children #Youth #Family