የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.12K subscribers
1.85K photos
4 videos
1 file
54 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አዋኪ ተግባር ማስጠቀሚያ እቃዎች አስወገደ።

ግንቦት 1/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው በተለያዩ ቦታዎች አዋኪ ድርጊቶች ሲከናወን እርምጃ በመውሰድ የወረሳቸውን የሺሻ ማስጨሻ እቃዎችን በማቃጠል አስወገደ ።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ፣ ከሰላምና ጸጥታ እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በተለያዩ ጊዜያቶች ከተለያዩ ንግድ ቤቶች ፣ ሆቴሎች ፣መኖሪያ ቤቶችና ከፔንሲዮኖች በተደረገ ክትትልና ድንገተኛ ኦፕሬሽን ከ1000 በላይ የሺሻ ማስጨሻ እቃዎችን በመውረስ በዛሬው ዕለት በማቃጠል
እንዲወገዱ ተደረገ።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን እንደገለፁት በጊዜው ድርጊቱን ሲያከናውኑ የተገኙ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ በመውሰድ እቃዎቹ የተወረሱ መሆኑን ገልጸዋል ።

አክለውም ህብረተሰቡ መሰል አዋኪ ድርጊቶች ሲፈጽሙና ሲያስጠቅሙ ከተመለከተም በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት በመጠቆምና በነፃ የስልክ መስመር 9995 ትብብሩን ሊያደርግ እንደሚገባም ኃላፊው ተናግረዋል ።

የክ/ከተማው የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ም/ኢንስፔክተር ፍፁም ወልደ አንደተናገሩት አዋኪ ተግባራት ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ የክትትል ስራዎችን በማጠናከር እንዲቀንሱ ማድረግ ይገባል ብለዋል ።

ህብረተሰቡ በአሁኑ ሰዓት ህገ ወጥነትን ለመከላከል እያደረገ ያለውን ስራ በማጠናከርና በባለቤትነት ተባባሪ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባና ከመሰል አዋኪ ተግባራት ራሳቸውን በማራቅ ለሌሎች አርዓያ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የትዊተር/X/ ሚዲያ ገፃችን
https://x.com/Addis_Denb?t=u8wW3qnxWk48GYzJ4RD96Q&s=09
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
2👍1
የዛሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ ለ #ጽዱኢትዮጵያ ስራችን ሃምሳ ሚሊዮን ብር ኢትዮጵያውያን ሁሉ ልናዋጣ አቅደን ነበር።

ያሰብነውን ሳናሳካ ጀምበር የሚጠልቅብን አይደለንምና በአንድ ጀምበር ከ154 ሚሊዮን ብር በላይ ማዋጣት ችለናል። ኢትዮጵያን ሲያኮሩ የኖሩ አትሌቶች፣ ስፖርተኞች እና ደጋፊዎች፣ የዘወትር አገልጋይ የታክሲ አሽከርካሪዎች፣ ለኅሊናም ለአካባቢም ንፅህና የሚቀኙ ከያንያን፣ ምሁራን፣ ባለሃብቶች በቴሌቶኑ ስፍራ በመገኘት ላደረጉት አስተዋጽዎ እነሆ ምስጋና።

በመላው አለም ሆነው በዛሬዋ ጀምበር በዲጂታል ቴሌቶኑ የተሳተፉ ከአርባ ሺህ በላይ ዜጎች ለፅዱ ኢትዮጵያ ያላቸው ምኞት መግለጫ የሆነው አስተዋፅዖ በተግባር በየአካባቢው በሚገነቡ የሕዝብ መፀዳጃዎች ይታወሳል።

ይህ ትውልድ ጀምበር ወጥታ በገባች ቁጥር ለመጪው ትውልድ መስፈንጠሪያ የሚሆን ብሩህ እና ፅኑ መሰረት ደልድሎ ያወርሳል። ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ
👏31👍1
ባለስልጣኑ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ ለቤት ተጠቃሚዎች አስረከበ

ግንቦት 10 /2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው ወረዳ 12 ያስገነባቸው የ3 ደጋፊ የሌላቸው አባወራ እና እማወራ 7 ክፍል ቤቶች በማጠናቀቅ በዛሬው እለት ለቤቶቹ ተጠቃሚዎች ቁልፍ አስረከበ።

በቁልፍ ርክክብ ፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ፣ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፉፋ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዋና ሰራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ኤጀና እና ፣የአቃቂ ቃሊቲ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኣበራ ኢቲቻና ሌሎች የክ/ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር አመራሮች፣ ኦፊሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።

በፕሮግራሙ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣኑ የበጎ ፈቃድ ሰራ ላይ አየተሰራ ያለው ተግባር የሚደነቅና የሚበረታታ መሆኑ በመግለፅ የአቅመ ደካማውን ማህበረሰብ ማገዝና ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ የማምጣት ሚና የሁሉም ሀላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።

የአቃቂ ክ/ከተማ ዋና ሰራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ሜጀና በፕሮግራሙ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ጎን ለጎን የከተማውን ሰላምና ጸጥታ እያስጠበቀኔ በተለያዩ ሰው ተኳር የበጎ ፍቃድ ተግባር ላይ በመሰማራት እየሰራ ያለው ስራ ሊበረታታ የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል ።

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ከተያዙት እቅዶች ውስጥ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መሳተፋ እንደሆነ ገልፀው በክ/ከተማው ወረዳ 12 የአመራሩ እና የኦፊሰሩ የጉልበት ወጪን ሳይካተት 1.5 ሚሊዮን ብር ለቤቶችን ወጪ በማድረግ ቤቶቹ መገንባታቸውን ገልጸዋል ።

አክለውም የበጎ ፈቃድ ተግባራት የብዙዎችን ህይወት እየቀየሩ እንደሚገኝና በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በንግግራቸው የቤት እድሳቱን ላስጀመሩት የቀድሞ የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ ከተማ የአሁኑ አዲስ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ እንዲሁም በግንባታ ወቅት ለተሳተፉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።

ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን
👍1