የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.1K subscribers
1.79K photos
4 videos
1 file
53 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ የሶስተኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አከናውኗል ።

07- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የሶስተኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አከናወነ።

በመርሀ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቂርቆስ፣ የአራዳ እና የልደታ ክ/ከተሞች ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አመራሮችና ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።

የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ደንብ ጥሰትን ከመከላከል ከመቆጣጠርና እርምጃ ከመውሰድ ጎን ወደ ህብረተሰቡ በመውረድ የሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኝ መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ተናግረዋል ።

ዘንድሮ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር "በመትከል ማንሰራራት " በሚል መሪ ቃል የተጀመረውን የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ባለስልጣኑ ለተከታታይ 3 ቀናት በዛሬው ዕለትም በደማቅ ሁኔታ ያካሄደ ሲሆን በቀጣይም የደም ልገሳ መርሐ ግብርና የተጀመረውን የቤት ዕድሳት አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ዋና ሰራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።

በችግኝ ተከላ መርኃ ግብሩ የተገኙት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብር እንደሀገር ያለንን አረንጓዴ ሽፋን ለማሳደግ ተጠናክሮ በዛሬው ዕለትም በባለስልጣኑ ቀጥሏል በማለት ሁሉም አካል በአግባቡ በተዘጋጀው ቦታ በመትከልና አሻራውን በማሳረፍ ኃላፊነቱን መወጣትና በቀጣይም መንከባከብ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍2