በደንብ መከላከል 180/2017 ላይ ለአምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ግንዛቤ ተፈጠረ።
02/07 /2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "ንፁህ ወንዝ ለጤናማ ህይወት" በሚል መሪ ቃል
የወንዝ ዳርቻዎች ልማትን እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ለአምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የሁለቱ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት አዳራሽ አካሄደ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለፁት በከተማው አስተዳደር ስር የሚገኙ ተቋማት በሙሉ 7/24 ስራዎችን በማከናወን የከተማውን እድገት ለማፋጠን እየተጉ ይገኛሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እንዲያስፈጽም የተሰጡትን ደንቦች ሁሉ በማስከበር ተልዕኮውን በአግባቡ እየተወጣ እንደሚገኝ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
አክለውም በዛሬው ዕለት "ንጹህ ወንዝ ለጤናማ ህይወት!" በሚል መሪ ቃል ለከተማዋ ልማትና እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከምታበረክቱ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅት ጋር በደንብ ቁጥር 180/2017 መግባባት ላይ በመድረስ ከፍተኛ በጀት የወጣበትን የህዝብና የሀገር ሀብቶችን በጋራ መጠበቅ ይገባል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሌላው በመድረኩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በከተማችን የሚገኙ ወንዞችን የኢኮኖሚያችን ግብዓትና የህዝባችን መዝናኛ ስፍራ ለማድረግ የጀመረውን ልማት ለማስጠበቅ ደንብ ቁጥር 180/2017 ወደ ስራ በማስገባትና በማስፈጸም ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ከተማችን ከግብር ከፋዮች በምታገኘው ገቢ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ ትገኛለች። እነዚህን የለሙና የተገነቡ ስፍራዎች ለመጠበቅ የተለያዩ ደንቦች ጸድቀዉ ወደ ስራ ተገብቷል።
በቀጣይም ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ተጠናክሮ የሚሰራ ሲሆን ደንቡን ተላልፈው በሚገኙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን የአከባቢ ጥበቃ ዋና ስራ አስኪያጅ ገልጸዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት እና መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 እና የቅጣት ሰንጠረዥ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
በደንቡ ዙሪያ በተለያዩ አግባቦች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ አካላትና ተቋማት ላይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር ሲሆን ከፍተኛው እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ የሚያስቀጣ እንደሆነ በሰነዱ ተመላክቷል።
በመድረኩ ተሳታፊ የሆኑ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ከተማዋን ለማልማት በሚደረግ ሂደት ውስጥ ኃላፊነታችንን መወጣታችን እንደለ ሆኖ ሁለቱም ተቋማት ከቅጣቱ በፊት ግንዛቤ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ቢሰራበት የሚል አስተያየታቸውን ተሰጥተዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
02/07 /2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "ንፁህ ወንዝ ለጤናማ ህይወት" በሚል መሪ ቃል
የወንዝ ዳርቻዎች ልማትን እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ለአምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የሁለቱ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት አዳራሽ አካሄደ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለፁት በከተማው አስተዳደር ስር የሚገኙ ተቋማት በሙሉ 7/24 ስራዎችን በማከናወን የከተማውን እድገት ለማፋጠን እየተጉ ይገኛሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እንዲያስፈጽም የተሰጡትን ደንቦች ሁሉ በማስከበር ተልዕኮውን በአግባቡ እየተወጣ እንደሚገኝ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
አክለውም በዛሬው ዕለት "ንጹህ ወንዝ ለጤናማ ህይወት!" በሚል መሪ ቃል ለከተማዋ ልማትና እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከምታበረክቱ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅት ጋር በደንብ ቁጥር 180/2017 መግባባት ላይ በመድረስ ከፍተኛ በጀት የወጣበትን የህዝብና የሀገር ሀብቶችን በጋራ መጠበቅ ይገባል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሌላው በመድረኩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በከተማችን የሚገኙ ወንዞችን የኢኮኖሚያችን ግብዓትና የህዝባችን መዝናኛ ስፍራ ለማድረግ የጀመረውን ልማት ለማስጠበቅ ደንብ ቁጥር 180/2017 ወደ ስራ በማስገባትና በማስፈጸም ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ከተማችን ከግብር ከፋዮች በምታገኘው ገቢ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ ትገኛለች። እነዚህን የለሙና የተገነቡ ስፍራዎች ለመጠበቅ የተለያዩ ደንቦች ጸድቀዉ ወደ ስራ ተገብቷል።
በቀጣይም ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ተጠናክሮ የሚሰራ ሲሆን ደንቡን ተላልፈው በሚገኙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን የአከባቢ ጥበቃ ዋና ስራ አስኪያጅ ገልጸዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት እና መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 እና የቅጣት ሰንጠረዥ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
በደንቡ ዙሪያ በተለያዩ አግባቦች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ አካላትና ተቋማት ላይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር ሲሆን ከፍተኛው እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ የሚያስቀጣ እንደሆነ በሰነዱ ተመላክቷል።
በመድረኩ ተሳታፊ የሆኑ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ከተማዋን ለማልማት በሚደረግ ሂደት ውስጥ ኃላፊነታችንን መወጣታችን እንደለ ሆኖ ሁለቱም ተቋማት ከቅጣቱ በፊት ግንዛቤ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ቢሰራበት የሚል አስተያየታቸውን ተሰጥተዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍4
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት ወንዝና የወንዝ ዳርቻ የበከሉ ተቋማትን 2,600,000/ሁለት ሚሊየን ስድስት መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
02/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ፍሳሽና በካይ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት የገንዘብ ቅጣቶች በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጆ ጥቁር አንበሳ እስፒሻላይዝድ ልዩ የካንሰር ህክምና ተቋም 400,000 ብር፤ በወረዳ 7 ኤክስትሪም ሆቴል 300,000 ብር እና ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን 100,000 ብር ቅጣት ተቀጥተዋል።
በተጨማሪም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሙኒዝ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት 300,000 ብር፣ አል ሐኪም ቢዝነስ ድርጅት 400,000 ሺህ ብር እና ታዬ ቦጋለ የግል ድርጅት 100,000 ሺህ ብር ሲቀጡ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ፍቅር ፕላዛ 100,000 ሺህ ብር ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ድሬ ኢንዱሰትሪ ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር 300,000 ብር ፤በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የነገ ሰው ጽዳት ድረጅት 300,000 ብር እና በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ሰንሴት ሆምስ ድርጅት 300,000 ብር ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአጠቃላይ 2,600,000/ሁለት ሚሊየን ስድስት መቶ ሺህ/ ብር ቅጣት መቅጣቱ ገልጿል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
02/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ፍሳሽና በካይ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት የገንዘብ ቅጣቶች በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጆ ጥቁር አንበሳ እስፒሻላይዝድ ልዩ የካንሰር ህክምና ተቋም 400,000 ብር፤ በወረዳ 7 ኤክስትሪም ሆቴል 300,000 ብር እና ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን 100,000 ብር ቅጣት ተቀጥተዋል።
በተጨማሪም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሙኒዝ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት 300,000 ብር፣ አል ሐኪም ቢዝነስ ድርጅት 400,000 ሺህ ብር እና ታዬ ቦጋለ የግል ድርጅት 100,000 ሺህ ብር ሲቀጡ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ፍቅር ፕላዛ 100,000 ሺህ ብር ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ድሬ ኢንዱሰትሪ ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር 300,000 ብር ፤በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የነገ ሰው ጽዳት ድረጅት 300,000 ብር እና በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ሰንሴት ሆምስ ድርጅት 300,000 ብር ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአጠቃላይ 2,600,000/ሁለት ሚሊየን ስድስት መቶ ሺህ/ ብር ቅጣት መቅጣቱ ገልጿል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
👍10