ፍሳሽ ቆሻሻን በመልቀቅ ወንዝ የበከለ ድርጅት 300 ሺህ ብር ተቀጣ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በዛሬው ዕለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ይህን ደንብ ተላልፎ በተገኘ ቫይብስ ሆቴልና ስፓ/Vibes Hotel & Spa/ ድርጅት ላይ በደንብ ቁጥር 180/17 የቅጣት ሰንጠረዥ 1 ተራ ቁጥር 3 ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀ ድርጅት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ፈጥሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከተማዋን ውብ ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማት 7/24 በመስራት የወንዞች ዳርቻ የማስዋብ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
ህብረተሰቡም መንግስት ከፍተኛ ወጪ አውጥቶ ያለማቸውን ሀብቶች እንዲንከባከብና ደንብ ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲገኝ በ9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አቅርቧል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ በየትኛውም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ የሚደረጉ የደንብ መተላለፎችን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በዛሬው ዕለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ይህን ደንብ ተላልፎ በተገኘ ቫይብስ ሆቴልና ስፓ/Vibes Hotel & Spa/ ድርጅት ላይ በደንብ ቁጥር 180/17 የቅጣት ሰንጠረዥ 1 ተራ ቁጥር 3 ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀ ድርጅት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ፈጥሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከተማዋን ውብ ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማት 7/24 በመስራት የወንዞች ዳርቻ የማስዋብ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
ህብረተሰቡም መንግስት ከፍተኛ ወጪ አውጥቶ ያለማቸውን ሀብቶች እንዲንከባከብና ደንብ ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲገኝ በ9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አቅርቧል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ በየትኛውም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ የሚደረጉ የደንብ መተላለፎችን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍6
ግንፍሌ ወንዝ ውስጥ ቆሻሻ የጣለው ድርጅት 100 ሺህ ብር ተቀጣ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ግንፍሌ ወንዝ ውስጥ ቆሻሻ የጣለው የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጠቅላይ ቤተክነት የሠንበት ት/ቤት ማደራጃና መምሪያ የማህበረ ቅዱሳን ተቋም በከተማ አስተዳደሩ የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 በመተላለፍ ደረቅ ቆሻሻን ወደ ወንዝ በመጣሉ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠሩ ይታወሳል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ግንፍሌ ወንዝ ውስጥ ቆሻሻ የጣለው የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጠቅላይ ቤተክነት የሠንበት ት/ቤት ማደራጃና መምሪያ የማህበረ ቅዱሳን ተቋም በከተማ አስተዳደሩ የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 በመተላለፍ ደረቅ ቆሻሻን ወደ ወንዝ በመጣሉ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠሩ ይታወሳል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
👏5👍3❤2👎1
ኦፊሰሩን በስነ-ምግባር ለማነጽ የግንዛቤ ስልጠናዎች ሚናቸው የላቀ መሆኑ ተገለፀ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኦፊሰሮችና ሽፍት መሪዎች "መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት" በሚል መሪ ቃል በክፍለ ከተማው አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ የቀረበው ሰነድ ብልሹ አሰራርና የስነምግባር ጉድለት በመልካም አስተዳደር ላይ የሚሳድረውን ተፅኖ እና ችግሩን መፍታት በሚገባው አቅጣጫ ላይ ስልጠና ተሰጨጥቷል።
በሰነዱ መነሻነት ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን ለቀረቡ ሀሳብና አስተያየቶች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።
በተጨማሪም የወንዝ ዳር ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይም በክፍለ ከተማው የአከባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ቡድን መሪ አቶ ለሜሳ ደበላ ደንቡና የቅጣት ሰንጠረዡ ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
በመጨረሻም የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎች በመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ደሳለኝ እውቅና ሰጥተዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኦፊሰሮችና ሽፍት መሪዎች "መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት" በሚል መሪ ቃል በክፍለ ከተማው አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ የቀረበው ሰነድ ብልሹ አሰራርና የስነምግባር ጉድለት በመልካም አስተዳደር ላይ የሚሳድረውን ተፅኖ እና ችግሩን መፍታት በሚገባው አቅጣጫ ላይ ስልጠና ተሰጨጥቷል።
በሰነዱ መነሻነት ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን ለቀረቡ ሀሳብና አስተያየቶች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።
በተጨማሪም የወንዝ ዳር ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይም በክፍለ ከተማው የአከባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ቡድን መሪ አቶ ለሜሳ ደበላ ደንቡና የቅጣት ሰንጠረዡ ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
በመጨረሻም የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎች በመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ደሳለኝ እውቅና ሰጥተዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍5
"የከተማ አስተዳደሩ የሰጠንን ተልዕኮ በአግባቡ መፈፀም ይጠበቅብናል" ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ
የካቲት 29 /2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች፣ የ11ዱም ክፍለ ከተማ እና የ119ኙ የወረዳ ሀላፊዎች እና የማዕከሉ ዳይሬክተሮች በድን መሪዎች በተገኙበት የካቲት ወር የስራ ክንውን ግምገማ አካሄደ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የከተማ አስተዳደሩ በሰጠን ተልዕኮ እና በጣለብን እምነት መሠረት የደንብ መተላለፎችን በመከላከል፣ በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ ደንብ ቁጥር 167/2016 እና 180/2017 በመፈጸም ተልዕኮውን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ-አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በበኩላቸው የደንብ መተላለፎችን በተመለከተ እርምጃ መውሰድ ብቻ ሳይሆን የፈፀመው አካል ተገቢውን ቅጣት ማግኘተ እንዳለበትና የተጠናከረ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ማሳደግ እንደሚገባ ገልፀዋል
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በበኩላቸው የተቋሙ ገጽታ ለመቀነስ የተጠናከረ የሶሻል ሚዲያ ስራ እና ህብረተሰቡ ያሳተፈ ስራ በመግባባት መስራት እንደሚያስፈልነግ ።
በግምገማው በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመልካም አስተዳደር ዙርያ የተሰሩ ስራዎች በደንብ መተላለፍ የቅድመ መከላከልና የእርምጃ አወሳሰድተግባራትና የ6ኛ ዙር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ምልመላን አስመልክቶ የተሰሩ ሰራዎችን በተመለከተ የተሰሩ ሰራዎች ላይ ግምገማው ተካሂዷል።
በመድረኩ ከክፍለ ከተማ የልደታ፣የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች እና ከወረዳ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 እና የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 የተሰሩ ሰራዎችን ሪፖርት በዝርዝር እንደማሳያ አቅርበዋል።
በእለቱ በ11 ክፍለ ከተሞች ሙስናና ብልሹ አሰራርን አስመልክቶ እየተሰጠ ያለውን የስልጠና ሪፓርት አስመልክቶ የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ በሶሻል ሚዲያ የሚለቀቁ የስነ ምግባር ግድፈቶች እንደ ማሳያ በማቅረብ በቀጣይ መስተካከል እንዳለበት አሳስበዋል።
በባለስልጣኑ በየካቲት ወር የተሰሩ ሰራዎችን አስመልክቶ ሪፖርት ያቀረቡት የባለስልጣኑ የእቅድና በጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ በሪፖርቱ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና ፣በወንዞች ዳርቻ ልማትን አስመልክቶ እየተሰሩ ያሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች በትኩረት መሰራቱን ጠቅሰዋል።
በመድረኩ የ6ኛ ዙር የአዲስ ምልምል ኦፊሰሮች ምልመላ ሂደት በእቅዱ መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የቀጣይ ስራዎች በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት ተመላክቷል።
በመጨረሻም የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የቀጣይ ስራ የትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
የካቲት 29 /2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች፣ የ11ዱም ክፍለ ከተማ እና የ119ኙ የወረዳ ሀላፊዎች እና የማዕከሉ ዳይሬክተሮች በድን መሪዎች በተገኙበት የካቲት ወር የስራ ክንውን ግምገማ አካሄደ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የከተማ አስተዳደሩ በሰጠን ተልዕኮ እና በጣለብን እምነት መሠረት የደንብ መተላለፎችን በመከላከል፣ በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ ደንብ ቁጥር 167/2016 እና 180/2017 በመፈጸም ተልዕኮውን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ-አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በበኩላቸው የደንብ መተላለፎችን በተመለከተ እርምጃ መውሰድ ብቻ ሳይሆን የፈፀመው አካል ተገቢውን ቅጣት ማግኘተ እንዳለበትና የተጠናከረ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ማሳደግ እንደሚገባ ገልፀዋል
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በበኩላቸው የተቋሙ ገጽታ ለመቀነስ የተጠናከረ የሶሻል ሚዲያ ስራ እና ህብረተሰቡ ያሳተፈ ስራ በመግባባት መስራት እንደሚያስፈልነግ ።
በግምገማው በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመልካም አስተዳደር ዙርያ የተሰሩ ስራዎች በደንብ መተላለፍ የቅድመ መከላከልና የእርምጃ አወሳሰድተግባራትና የ6ኛ ዙር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ምልመላን አስመልክቶ የተሰሩ ሰራዎችን በተመለከተ የተሰሩ ሰራዎች ላይ ግምገማው ተካሂዷል።
በመድረኩ ከክፍለ ከተማ የልደታ፣የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች እና ከወረዳ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 እና የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 የተሰሩ ሰራዎችን ሪፖርት በዝርዝር እንደማሳያ አቅርበዋል።
በእለቱ በ11 ክፍለ ከተሞች ሙስናና ብልሹ አሰራርን አስመልክቶ እየተሰጠ ያለውን የስልጠና ሪፓርት አስመልክቶ የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ በሶሻል ሚዲያ የሚለቀቁ የስነ ምግባር ግድፈቶች እንደ ማሳያ በማቅረብ በቀጣይ መስተካከል እንዳለበት አሳስበዋል።
በባለስልጣኑ በየካቲት ወር የተሰሩ ሰራዎችን አስመልክቶ ሪፖርት ያቀረቡት የባለስልጣኑ የእቅድና በጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ በሪፖርቱ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና ፣በወንዞች ዳርቻ ልማትን አስመልክቶ እየተሰሩ ያሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች በትኩረት መሰራቱን ጠቅሰዋል።
በመድረኩ የ6ኛ ዙር የአዲስ ምልምል ኦፊሰሮች ምልመላ ሂደት በእቅዱ መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የቀጣይ ስራዎች በጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት ተመላክቷል።
በመጨረሻም የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የቀጣይ ስራ የትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍4
ባለስልጣኑ የመሬት ባንክ የገባ መሬት በመውረር በተገነባ ግንባታ ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ
የካቲት 30/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 2 መሬት ባንክ ገብቶ ሲጠበቅ የነበረ 1000 ካ.ሜ. የህዝብና የመንግስትን መሬት በህገወጥ መንገድ ሁለት ግለሰቦች የ2012 ዓ.ም ካርታ አለን በማለትና ከወረዳው የግንባታ ፍቃድ በማውጣት ቦታውን አጥረው ህገ-ወጥ ግንባታ ለመገንባት ሙከራ ሲያደርጉ መያዛቸው ተገለፀ ።
ባለስልጣኑ መሬት ባንክ ገብቶ ሲጠብቀው በነበረን መሬት ላይ የተገነባውን ግንባታ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ደንብ ማስከበረ ጽ/ቤት ከክፍለ ከተማና ከወረዳ አመራሮች ጋር በመቀናጀት የጸጥታ አካላትን በማሳተፍ ግንባታውን በማፍረስ የመንግስትና የህዝብ መሬት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ማድረጉ አስታውቋል።
ጥፋተኞችን ለህግ ለማቅረብ መረጃውን በማደራጀት በቁጥጥር ስር በማዋል በሊዝ አዋጁ ተጠያቂ ለማድረግ በሂደት ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል።
ባለስልጣኑ በህገ-ወጦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፀ ሲሆን ደንብ የሚተላለፉ አንዳንድ ግድ የሌሽ ግለሠቦችን ልማት ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪውን ያቀርባል ።
የካቲት 30/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 2 መሬት ባንክ ገብቶ ሲጠበቅ የነበረ 1000 ካ.ሜ. የህዝብና የመንግስትን መሬት በህገወጥ መንገድ ሁለት ግለሰቦች የ2012 ዓ.ም ካርታ አለን በማለትና ከወረዳው የግንባታ ፍቃድ በማውጣት ቦታውን አጥረው ህገ-ወጥ ግንባታ ለመገንባት ሙከራ ሲያደርጉ መያዛቸው ተገለፀ ።
ባለስልጣኑ መሬት ባንክ ገብቶ ሲጠብቀው በነበረን መሬት ላይ የተገነባውን ግንባታ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ደንብ ማስከበረ ጽ/ቤት ከክፍለ ከተማና ከወረዳ አመራሮች ጋር በመቀናጀት የጸጥታ አካላትን በማሳተፍ ግንባታውን በማፍረስ የመንግስትና የህዝብ መሬት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ማድረጉ አስታውቋል።
ጥፋተኞችን ለህግ ለማቅረብ መረጃውን በማደራጀት በቁጥጥር ስር በማዋል በሊዝ አዋጁ ተጠያቂ ለማድረግ በሂደት ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል።
ባለስልጣኑ በህገ-ወጦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፀ ሲሆን ደንብ የሚተላለፉ አንዳንድ ግድ የሌሽ ግለሠቦችን ልማት ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪውን ያቀርባል ።
👍11❤2