የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.09K subscribers
1.75K photos
4 videos
1 file
52 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የመፀዳጃ ቤት ፍሳሽ ከዋና ፍሳሽ መስመር በማገናኘት ወደ ወንዝ እንዲገባ ያደረጉ የንግድ ቤቶችን 600 ሺህ ብር ተቀጡ

30/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 የመፀዳጃ ቤት ፍሳሽ ከዋና መስመር ትቦ ጋር ባገናኙ ሁለት የንግድ ቤቶች በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት እያንዳንዳቸው 300,000/ሶስት መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 600,000/ስድስት መቶ ሺህ ብር በመቅጣት እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ማንኛውም አይነት ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ ከመልቀቅና ደረቅ ቆሻሻ ወንዝ ውስጥ ከመጣል እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

ተቋሙ ድርጊቱን በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት በደንብ ቁጥር 180/2017 መሠረት እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

የከተማ አስተዳደሩ የአዲስ አበባ ወንዞች ከመጥፎ ሽታ ተላቀው የመዝናኛ ቦታዎች እዲሆኑ የጀመረው ስራ ዳር ለማድረስ ደንብ በማስከበር የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ገልጿል።

ህብረተሰቡም ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ መልዕክቱን ያስተላልፋል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍84
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ ግለሰቦችና ተቋማትን 2,300,000/ሁለት ሚሊየን ሶስት መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ

02/07/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት የገንዘብ ቅጣቶች በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 3 ድርጅቶች እያንዳንዳቸው እያንዳንዳቸው 300,000/ሶስት መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 900,000/ዘጠኝ መቶ ሺህ ብር እና አንድ ግለሰብ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 1 ሚሊዮን ብር ቀጥቷል፡፡

በተያዘ ዜና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 700 ሺህ ብር ፤በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 300 ሺህ ብር ፤ በጉለሌ ክፍለ ከተማ 300 ሺህ ብር በድምሩ በዛሬው እለት 2300,000/ሁለት ሚሊየን ሶስት መቶ ሺህ ብር/ በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ ተቋማት እና ግለሰቦች ማንኛውም አይነት ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ በመልቀቅም ሆነ ደረቅ ቆሻሻ ወንዝ ውስጥ በመጣል ደንብ በመተላለፍ ከሚወሰደው የቅጣት እርምጃ እራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳስቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ድርጊቱን በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ በደንብ ቁጥር 180/2017 መሠረት የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

ህብረተሰቡም ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አስተላልፏል።

ዘገባው ፦ የባስልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
👍11
በደንብ መከላከል 180/2017 ላይ ለአምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ግንዛቤ ተፈጠረ።

02/07 /2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "ንፁህ ወንዝ ለጤናማ ህይወት" በሚል መሪ ቃል
የወንዝ ዳርቻዎች ልማትን እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ለአምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የሁለቱ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት አዳራሽ አካሄደ።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለፁት በከተማው አስተዳደር ስር የሚገኙ ተቋማት በሙሉ 7/24 ስራዎችን በማከናወን የከተማውን እድገት ለማፋጠን እየተጉ ይገኛሉ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እንዲያስፈጽም የተሰጡትን ደንቦች ሁሉ በማስከበር ተልዕኮውን በአግባቡ እየተወጣ እንደሚገኝ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል።

አክለውም በዛሬው ዕለት "ንጹህ ወንዝ ለጤናማ ህይወት!" በሚል መሪ ቃል ለከተማዋ ልማትና እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከምታበረክቱ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅት ጋር በደንብ ቁጥር 180/2017 መግባባት ላይ በመድረስ ከፍተኛ በጀት የወጣበትን የህዝብና የሀገር ሀብቶችን በጋራ መጠበቅ ይገባል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ሌላው በመድረኩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በከተማችን የሚገኙ ወንዞችን የኢኮኖሚያችን ግብዓትና የህዝባችን መዝናኛ ስፍራ ለማድረግ የጀመረውን ልማት ለማስጠበቅ ደንብ ቁጥር 180/2017 ወደ ስራ በማስገባትና በማስፈጸም ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከተማችን ከግብር ከፋዮች በምታገኘው ገቢ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ ትገኛለች። እነዚህን የለሙና የተገነቡ ስፍራዎች ለመጠበቅ የተለያዩ ደንቦች ጸድቀዉ ወደ ስራ ተገብቷል።

በቀጣይም ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው ተጠናክሮ የሚሰራ ሲሆን ደንቡን ተላልፈው በሚገኙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን የአከባቢ ጥበቃ ዋና ስራ አስኪያጅ ገልጸዋል።

በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት እና መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 እና የቅጣት ሰንጠረዥ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።

በደንቡ ዙሪያ በተለያዩ አግባቦች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ አካላትና ተቋማት ላይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር ሲሆን ከፍተኛው እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ የሚያስቀጣ እንደሆነ በሰነዱ ተመላክቷል።

በመድረኩ ተሳታፊ የሆኑ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ከተማዋን ለማልማት በሚደረግ ሂደት ውስጥ ኃላፊነታችንን መወጣታችን እንደለ ሆኖ ሁለቱም ተቋማት ከቅጣቱ በፊት ግንዛቤ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ቢሰራበት የሚል አስተያየታቸውን ተሰጥተዋል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍4