ባለስልጣኑ በመንገድ መሠረተ ልማት ጉዳት ጉዳት ባደረሱና ባበላሹ ግለሰቦችን ተጠያቂ አደረገ
ህዳር 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ራስ መኮነን ድልድይ አካባቢ በኦቪድ ኮነስትራክሽን ግንባታ የሚሰሩ ግለሰቦችን በመንገድና በአረንጓዴ መሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ባደረሱና ያበላሹ ግለሰቦችን በህግ ተጠያቂ አደረገ።
ባለስልጣኑ በአካባቢው በመንገድ መሠረተ ልማት ጉዳት ባደረሱና፣አረንጓዴ ቦታዎች በማበላሸትና በመርገጥ የተሠጣቸውን ቅጣት ባለመቀበል በአራዳ ክ/ከ ራስ ደስታ ፖሊስ ጣቢያ በፈፀሙት ጥፋት መሰረት በተሻሻለው የደንብ ቁጥር 167/16 መሠረት ክስ በመመስት ክትትል እያደረገ ይገኛል።
ባለስልጣኑ ክስ የመሠረተባቸው የድርጅቱ ሰራተኞ
1ኛ-አቶ ናሆም ብርሃነ ስላሴ አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት
2ኛ -አቶ ፍቅሩ ፅጌ ሰርቪስ አገልግሎት
3ኛ- አረጋይ በርሄ ፕሮጀክት ማናጀር ናቸው።
ባለስልጣኑ በከተማችን ውስጥ የሚገኙ በግንባታ ስራ ላይ የተሠማሩ ድርጅቶችና ሰራተኞች የከተማ አስተዳደሩ ያወጣቸውን ህግና ደንቦችና አሰራሮችን በመከተል በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅና እንዲሠሩ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
ባለስልጣኑ በደንብ ተላላፊዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ አሳውቋል።
ህዳር 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ራስ መኮነን ድልድይ አካባቢ በኦቪድ ኮነስትራክሽን ግንባታ የሚሰሩ ግለሰቦችን በመንገድና በአረንጓዴ መሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ባደረሱና ያበላሹ ግለሰቦችን በህግ ተጠያቂ አደረገ።
ባለስልጣኑ በአካባቢው በመንገድ መሠረተ ልማት ጉዳት ባደረሱና፣አረንጓዴ ቦታዎች በማበላሸትና በመርገጥ የተሠጣቸውን ቅጣት ባለመቀበል በአራዳ ክ/ከ ራስ ደስታ ፖሊስ ጣቢያ በፈፀሙት ጥፋት መሰረት በተሻሻለው የደንብ ቁጥር 167/16 መሠረት ክስ በመመስት ክትትል እያደረገ ይገኛል።
ባለስልጣኑ ክስ የመሠረተባቸው የድርጅቱ ሰራተኞ
1ኛ-አቶ ናሆም ብርሃነ ስላሴ አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት
2ኛ -አቶ ፍቅሩ ፅጌ ሰርቪስ አገልግሎት
3ኛ- አረጋይ በርሄ ፕሮጀክት ማናጀር ናቸው።
ባለስልጣኑ በከተማችን ውስጥ የሚገኙ በግንባታ ስራ ላይ የተሠማሩ ድርጅቶችና ሰራተኞች የከተማ አስተዳደሩ ያወጣቸውን ህግና ደንቦችና አሰራሮችን በመከተል በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅና እንዲሠሩ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
ባለስልጣኑ በደንብ ተላላፊዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ አሳውቋል።
ባለስልጣኑ በአገልግሎት አሰጣጥ እና ደንበኞች አያያዝ ላይ ስልጠና ሰጠ:
ህዳር 26/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ጥናት ዳይሬክቶሬት ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በደንበኞች አገልግሎት አስጣጥ እና አያያዝ ዙሪያ ለማእከል እና ክፍለ ከተማ ሲቪል ሰራተኞች በባለስልጣኑ መሰብሰባያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማ አስተዳደሩ የተጣለበት ህዝብን በቅንነት በታማኝነት አገልግሎትን በጥራት የመስጠት ኃላፊነትን በመወጣት ላይ የሚገኝ ተቋም እንደመሆኑ እንደነዚ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ይበል የሚያሰኝ ተግባር ነው ብለዋል::
በመ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ ኮ/ር አህመድ መሀመድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ጤናማ ለማድረግ ስልጠናዎች መሰጠታቸው ትልቁን ድርሻ እንዳለው ገልፀዋል::
ስልጠናው ከትምህርት ተቋማት ከምናገኘው እውቀት ባሻገር እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ስራችንን ብቁ እና ተወዳዳሪ ከማድረግ አኳያ ትልቅ አስተዋፆ እንዳለው መረዳት እንደሚገባ ገልፀው ከዛሬው ስልጠና ትምህርት ወስዳችሁ ቅን ታዛዥ ታማኝ የሆነ አገልጋይ እንድትሆኑ መልክቴን አስተላልፋለው በማለት የመክፈቻ ንግግራቸውን አስተላልፈዋል::
የአገልግሎት አሰጣጥ እና የደንበኛ አያያዝ ስልጠና ሰነዱን ያቀረቡት ወ/ሮ ሰላማዊት ይመር ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ምንነት, ስለ ተገልጋይ ስነ-ልቦና አረዳድ ክህሎት, ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት እንዴት ማዘመን ይቻላል,በሚል አቅርበዋል።
ስልጠናው የደንበኛን ቅሬታ ማስተናገጃ መንገዶችን በትክክል ከመረዳት እና የመፍቻ መንገዶች ጋር በተያያዘ እንዲሁም ስለ አጠቃላይ ፅንሰ ሀሳቡ በማንሳት የተቋሙን ባህሪ መሰረት በማድረግ ተሰጥቷል ::
በመጨረሻም ተሳታፊዎችም የመንግስት ተቋም የራሱ የሆነ የአሰራር ስርአት እና የህግ ማዕቀፍ ያለው በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጡ ያንን ማዕከል ያደረገ እንዲሆንና ሰራተኞችም ስራችን በጥራት በመከወን እና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት ይገባናል የሚሉ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተዋል::
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የባለስልጣኑ የኦንላይን ቅሬታ መቀበያ ፎርም ለማግኘት የተዘጋጀ ሊንክ እና አተገባበር በተመለከተ በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አቶ ሚሊዮን ካሳሁን ተዋውቋል::
ምክትል ስራ አስኪያጅ ኮ/ር አህመድ መሀመድ ስልጠናው መሰጠቱ በቀጣይ ከኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እና ስልጠናው ወደ ተግባርም መቀየር እንደሚያስፈልግ ተገንዝበን የአገልግሎት አሰጣጣችንን ልናሻሽል ልናዘምን እንደሚገባ ገልፀዋል።
ህዳር 26/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ጥናት ዳይሬክቶሬት ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በደንበኞች አገልግሎት አስጣጥ እና አያያዝ ዙሪያ ለማእከል እና ክፍለ ከተማ ሲቪል ሰራተኞች በባለስልጣኑ መሰብሰባያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማ አስተዳደሩ የተጣለበት ህዝብን በቅንነት በታማኝነት አገልግሎትን በጥራት የመስጠት ኃላፊነትን በመወጣት ላይ የሚገኝ ተቋም እንደመሆኑ እንደነዚ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ይበል የሚያሰኝ ተግባር ነው ብለዋል::
በመ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ ኮ/ር አህመድ መሀመድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ጤናማ ለማድረግ ስልጠናዎች መሰጠታቸው ትልቁን ድርሻ እንዳለው ገልፀዋል::
ስልጠናው ከትምህርት ተቋማት ከምናገኘው እውቀት ባሻገር እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ስራችንን ብቁ እና ተወዳዳሪ ከማድረግ አኳያ ትልቅ አስተዋፆ እንዳለው መረዳት እንደሚገባ ገልፀው ከዛሬው ስልጠና ትምህርት ወስዳችሁ ቅን ታዛዥ ታማኝ የሆነ አገልጋይ እንድትሆኑ መልክቴን አስተላልፋለው በማለት የመክፈቻ ንግግራቸውን አስተላልፈዋል::
የአገልግሎት አሰጣጥ እና የደንበኛ አያያዝ ስልጠና ሰነዱን ያቀረቡት ወ/ሮ ሰላማዊት ይመር ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ምንነት, ስለ ተገልጋይ ስነ-ልቦና አረዳድ ክህሎት, ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት እንዴት ማዘመን ይቻላል,በሚል አቅርበዋል።
ስልጠናው የደንበኛን ቅሬታ ማስተናገጃ መንገዶችን በትክክል ከመረዳት እና የመፍቻ መንገዶች ጋር በተያያዘ እንዲሁም ስለ አጠቃላይ ፅንሰ ሀሳቡ በማንሳት የተቋሙን ባህሪ መሰረት በማድረግ ተሰጥቷል ::
በመጨረሻም ተሳታፊዎችም የመንግስት ተቋም የራሱ የሆነ የአሰራር ስርአት እና የህግ ማዕቀፍ ያለው በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጡ ያንን ማዕከል ያደረገ እንዲሆንና ሰራተኞችም ስራችን በጥራት በመከወን እና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት ይገባናል የሚሉ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተዋል::
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የባለስልጣኑ የኦንላይን ቅሬታ መቀበያ ፎርም ለማግኘት የተዘጋጀ ሊንክ እና አተገባበር በተመለከተ በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አቶ ሚሊዮን ካሳሁን ተዋውቋል::
ምክትል ስራ አስኪያጅ ኮ/ር አህመድ መሀመድ ስልጠናው መሰጠቱ በቀጣይ ከኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እና ስልጠናው ወደ ተግባርም መቀየር እንደሚያስፈልግ ተገንዝበን የአገልግሎት አሰጣጣችንን ልናሻሽል ልናዘምን እንደሚገባ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ በለውጥ አመራር እና በውሳኔ ሰጪነት ላይ ስልጠና ሰጠ
05/04/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከማዕከል እስከ ወረዳ ለሚገኙ አመራሮች በስልታዊ አስተቃቀድ፣ በአስተዳደር ፣ውሳኔ ሰጪነትና እና የለውጥ አመራር ላይ ስልጠና ሰጠ።
የስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረኩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማችን የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ በእቅድ ውስጥ በመያዝ የአመራሮችን አቅም ይገነባል ተብሎ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
አክለውም ሰልጣኝ አመራሮ በሚኖረው የ3 ቀናት ቆይታ በስልጠናው መሰረት የተቋሙን ፍላጎት እና አላማ አውቆ ወደ ስራ መግባት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ስልጠናው ከኢትዮጲያ ስራ አመራር ኢንሰቲትዩት በመጡ አሰልጣኝ ዶ/ር ጀቤሳ ተሾመ እና በአቶ ሀገር መኩሪያ ለቀጣይ 2 ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሀመድ ስልጠናው በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር ለመፍጠር ወሳኝነት እንዳለው ተናግረው ስልጠናው ለቀጣይ ሁለት ቀናት በጥብቅ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
05/04/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከማዕከል እስከ ወረዳ ለሚገኙ አመራሮች በስልታዊ አስተቃቀድ፣ በአስተዳደር ፣ውሳኔ ሰጪነትና እና የለውጥ አመራር ላይ ስልጠና ሰጠ።
የስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረኩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማችን የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ በእቅድ ውስጥ በመያዝ የአመራሮችን አቅም ይገነባል ተብሎ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
አክለውም ሰልጣኝ አመራሮ በሚኖረው የ3 ቀናት ቆይታ በስልጠናው መሰረት የተቋሙን ፍላጎት እና አላማ አውቆ ወደ ስራ መግባት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ስልጠናው ከኢትዮጲያ ስራ አመራር ኢንሰቲትዩት በመጡ አሰልጣኝ ዶ/ር ጀቤሳ ተሾመ እና በአቶ ሀገር መኩሪያ ለቀጣይ 2 ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሀመድ ስልጠናው በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር ለመፍጠር ወሳኝነት እንዳለው ተናግረው ስልጠናው ለቀጣይ ሁለት ቀናት በጥብቅ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።