የዛሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ ለ #ጽዱኢትዮጵያ ስራችን ሃምሳ ሚሊዮን ብር ኢትዮጵያውያን ሁሉ ልናዋጣ አቅደን ነበር።
ያሰብነውን ሳናሳካ ጀምበር የሚጠልቅብን አይደለንምና በአንድ ጀምበር ከ154 ሚሊዮን ብር በላይ ማዋጣት ችለናል። ኢትዮጵያን ሲያኮሩ የኖሩ አትሌቶች፣ ስፖርተኞች እና ደጋፊዎች፣ የዘወትር አገልጋይ የታክሲ አሽከርካሪዎች፣ ለኅሊናም ለአካባቢም ንፅህና የሚቀኙ ከያንያን፣ ምሁራን፣ ባለሃብቶች በቴሌቶኑ ስፍራ በመገኘት ላደረጉት አስተዋጽዎ እነሆ ምስጋና።
በመላው አለም ሆነው በዛሬዋ ጀምበር በዲጂታል ቴሌቶኑ የተሳተፉ ከአርባ ሺህ በላይ ዜጎች ለፅዱ ኢትዮጵያ ያላቸው ምኞት መግለጫ የሆነው አስተዋፅዖ በተግባር በየአካባቢው በሚገነቡ የሕዝብ መፀዳጃዎች ይታወሳል።
ይህ ትውልድ ጀምበር ወጥታ በገባች ቁጥር ለመጪው ትውልድ መስፈንጠሪያ የሚሆን ብሩህ እና ፅኑ መሰረት ደልድሎ ያወርሳል። ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ
ያሰብነውን ሳናሳካ ጀምበር የሚጠልቅብን አይደለንምና በአንድ ጀምበር ከ154 ሚሊዮን ብር በላይ ማዋጣት ችለናል። ኢትዮጵያን ሲያኮሩ የኖሩ አትሌቶች፣ ስፖርተኞች እና ደጋፊዎች፣ የዘወትር አገልጋይ የታክሲ አሽከርካሪዎች፣ ለኅሊናም ለአካባቢም ንፅህና የሚቀኙ ከያንያን፣ ምሁራን፣ ባለሃብቶች በቴሌቶኑ ስፍራ በመገኘት ላደረጉት አስተዋጽዎ እነሆ ምስጋና።
በመላው አለም ሆነው በዛሬዋ ጀምበር በዲጂታል ቴሌቶኑ የተሳተፉ ከአርባ ሺህ በላይ ዜጎች ለፅዱ ኢትዮጵያ ያላቸው ምኞት መግለጫ የሆነው አስተዋፅዖ በተግባር በየአካባቢው በሚገነቡ የሕዝብ መፀዳጃዎች ይታወሳል።
ይህ ትውልድ ጀምበር ወጥታ በገባች ቁጥር ለመጪው ትውልድ መስፈንጠሪያ የሚሆን ብሩህ እና ፅኑ መሰረት ደልድሎ ያወርሳል። ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ
👏3❤1👍1
ባለስልጣኑ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ ለቤት ተጠቃሚዎች አስረከበ
ግንቦት 10 /2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው ወረዳ 12 ያስገነባቸው የ3 ደጋፊ የሌላቸው አባወራ እና እማወራ 7 ክፍል ቤቶች በማጠናቀቅ በዛሬው እለት ለቤቶቹ ተጠቃሚዎች ቁልፍ አስረከበ።
በቁልፍ ርክክብ ፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ፣ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፉፋ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዋና ሰራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ኤጀና እና ፣የአቃቂ ቃሊቲ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኣበራ ኢቲቻና ሌሎች የክ/ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር አመራሮች፣ ኦፊሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በፕሮግራሙ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣኑ የበጎ ፈቃድ ሰራ ላይ አየተሰራ ያለው ተግባር የሚደነቅና የሚበረታታ መሆኑ በመግለፅ የአቅመ ደካማውን ማህበረሰብ ማገዝና ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ የማምጣት ሚና የሁሉም ሀላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
የአቃቂ ክ/ከተማ ዋና ሰራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ሜጀና በፕሮግራሙ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ጎን ለጎን የከተማውን ሰላምና ጸጥታ እያስጠበቀኔ በተለያዩ ሰው ተኳር የበጎ ፍቃድ ተግባር ላይ በመሰማራት እየሰራ ያለው ስራ ሊበረታታ የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል ።
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ከተያዙት እቅዶች ውስጥ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መሳተፋ እንደሆነ ገልፀው በክ/ከተማው ወረዳ 12 የአመራሩ እና የኦፊሰሩ የጉልበት ወጪን ሳይካተት 1.5 ሚሊዮን ብር ለቤቶችን ወጪ በማድረግ ቤቶቹ መገንባታቸውን ገልጸዋል ።
አክለውም የበጎ ፈቃድ ተግባራት የብዙዎችን ህይወት እየቀየሩ እንደሚገኝና በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በንግግራቸው የቤት እድሳቱን ላስጀመሩት የቀድሞ የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ ከተማ የአሁኑ አዲስ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ እንዲሁም በግንባታ ወቅት ለተሳተፉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን
ግንቦት 10 /2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው ወረዳ 12 ያስገነባቸው የ3 ደጋፊ የሌላቸው አባወራ እና እማወራ 7 ክፍል ቤቶች በማጠናቀቅ በዛሬው እለት ለቤቶቹ ተጠቃሚዎች ቁልፍ አስረከበ።
በቁልፍ ርክክብ ፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ፣ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ፉፋ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዋና ሰራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ኤጀና እና ፣የአቃቂ ቃሊቲ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኣበራ ኢቲቻና ሌሎች የክ/ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር አመራሮች፣ ኦፊሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በፕሮግራሙ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣኑ የበጎ ፈቃድ ሰራ ላይ አየተሰራ ያለው ተግባር የሚደነቅና የሚበረታታ መሆኑ በመግለፅ የአቅመ ደካማውን ማህበረሰብ ማገዝና ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ የማምጣት ሚና የሁሉም ሀላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
የአቃቂ ክ/ከተማ ዋና ሰራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ሜጀና በፕሮግራሙ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ጎን ለጎን የከተማውን ሰላምና ጸጥታ እያስጠበቀኔ በተለያዩ ሰው ተኳር የበጎ ፍቃድ ተግባር ላይ በመሰማራት እየሰራ ያለው ስራ ሊበረታታ የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል ።
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ከተያዙት እቅዶች ውስጥ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መሳተፋ እንደሆነ ገልፀው በክ/ከተማው ወረዳ 12 የአመራሩ እና የኦፊሰሩ የጉልበት ወጪን ሳይካተት 1.5 ሚሊዮን ብር ለቤቶችን ወጪ በማድረግ ቤቶቹ መገንባታቸውን ገልጸዋል ።
አክለውም የበጎ ፈቃድ ተግባራት የብዙዎችን ህይወት እየቀየሩ እንደሚገኝና በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በንግግራቸው የቤት እድሳቱን ላስጀመሩት የቀድሞ የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ ከተማ የአሁኑ አዲስ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ እንዲሁም በግንባታ ወቅት ለተሳተፉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን
👍1