አዋኪ ድርጊት በሚፈፀምባቸው ንግድ ቤቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ፡፡
በቦሌ ክፍለ ከተማ በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ
በከተማችን በተለያዩ አካባቢዎች በህጋዊ ንግድ ሽፋን የሚፈፀሙ አዋኪ ድርጊቶች እና ሌሎች ህገ ወጥ ተግባራት ለወንጀል መስፋፋት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ከደንብ ማስከበር አባላትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለማስወገድ እየሰራ ይገኛል፡፡
በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ንግድ ቤቶች ላይ በተከናወነ የኦፕሬሽን ስራ ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ተገኝተው እርምጃ እንደተወሰደባቸው እና በህገ ወጥ ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ በርካታ ግለሰቦች ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ሰሞኑንም በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች ፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አባላትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በጋራ ባከናወኑት ተግባር በህገ ወጦች ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር በማዋል ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የማስወገድ ስራ ተሰርቷል፡፡
ድንገተኛ ቁጥጥር የተደረገባቸው እና ለወንጀል መስፋፋት መንስዔ የሆኑ ድርጊቶች ሲፈፀምባቸው የነበሩት
መኖሪያ ቤትን ጨምሮ ፔንሲዮኖች፣ ማሳጅ ቤቶች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ይገኙበታል፡፡
(የአዲስ አበባ ፖሊስ)
በቦሌ ክፍለ ከተማ በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ
በከተማችን በተለያዩ አካባቢዎች በህጋዊ ንግድ ሽፋን የሚፈፀሙ አዋኪ ድርጊቶች እና ሌሎች ህገ ወጥ ተግባራት ለወንጀል መስፋፋት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ከደንብ ማስከበር አባላትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለማስወገድ እየሰራ ይገኛል፡፡
በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ንግድ ቤቶች ላይ በተከናወነ የኦፕሬሽን ስራ ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ተገኝተው እርምጃ እንደተወሰደባቸው እና በህገ ወጥ ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ በርካታ ግለሰቦች ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ሰሞኑንም በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች ፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አባላትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በጋራ ባከናወኑት ተግባር በህገ ወጦች ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡
ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሺሻ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጨስባቸው ከተገኙ ቤቶች 3ሺህ 80 የሺሻ ዕቃ እና 80 ኪሎ ግራም አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር በማዋል ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የማስወገድ ስራ ተሰርቷል፡፡
ድንገተኛ ቁጥጥር የተደረገባቸው እና ለወንጀል መስፋፋት መንስዔ የሆኑ ድርጊቶች ሲፈፀምባቸው የነበሩት
መኖሪያ ቤትን ጨምሮ ፔንሲዮኖች፣ ማሳጅ ቤቶች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ይገኙበታል፡፡
(የአዲስ አበባ ፖሊስ)
👍5
“ንፁህ ከተማ - ጤናማ ማኅበረሰብ ለመገንባት”
ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የከተማ ንፅህና ከውበት ባለፈ በበርካታ መንገዶች ከህዝብ ጤና ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው።
ንፁህ እና ፅዱ ከተማ በሚተገብረው ከተማን ንፁህ በሚያደርጉ ተግባራት እና ፖሊሲዎች አካላዊ፣ አዕምሯዊ እና ማኅበራዊ ጤናን በማጠናከር ለነዋሪዎቹ ደኅንነት ቅድሚያ ይሰጣል።
ከመገለጫዎቹም መካከልም በቂ የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት እና አገልግሎቶችን ለሁሉም ነዋሪዎች ዝግጁ እና ተደራሽ ማድረግ እንዲሁም ንፁህ አየር፣ ውኃ እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን መገንባት ይገኝበታል።
ንፁህ እና ፅዱ ከተማ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ አካባቢያዊ እና ባህላዊ ሁኔታዎች የእርስ በርስ መስተጋብር ላይ በጎ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ይነገራል።
የንፁህ ከተማ እና አካባቢ የጤና ጥቅሞች፦
1. የአየር ብክለትን መቀነስ - ንፁህ ከተሞች ዝቅተኛ የአየር ብክለት ያላቸው ሲሆን ይህም በአየር ብክለት ሳብያ ሊከሰት የሚችልን የመተንፈሻ አካላት ሕመም፣ የልብ እና የደም ቧንቧ በሽታዎች እንዲሁም ያለጊዜ የመሞት ዕድል እንዲቀንስ ያስችላል።
2. የውኃ ወለድ በሽታዎችን መከላከል - በንፁህ ከተሞች የሚተገበሩ የቆሻሻ አወጋገድ እና የንፅህና አጠባበቅ አሠራሮች የውኃ ምንጮችን ከመበከል ይከላከላሉ። ይህም እንደ ኮሌራ፣ ታይፎይድ፣ ትኩሳት እና ተቅማጥ ያሉ የውኃ ወለድ በሽታዎችን ለመከላከል ያግዛል።
3. ወባን የመሰሉ ትንኝ ወለድ በሽታዎችን መቆጣጠር - ንፁህ ከተሞች እንደ ትንኝ እና ዝንብ በመሳሰሉ ነፍሳት አማካኝነት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመከላከል ጠንካራ ቁጥጥር ያደርጋሉ።
ንፁህ ከተሞች ነፍሳቱ በከተሞች እንዳይራቡ የአካባቢ ንፅህናን በመጠበቅ በበሽታዎቹ የመያዝ ዕድልን ይቀንሳሉ።
4. የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማስተዋወቅ - ንፁህ የሆነ ከተማ ደኅንነታቸው የተጠበቀ እና ማራኪ የሕዝብ ቦታዎችን በማቅረብ ይታወቃል።
ይህም ነዋሪዎች የእግር እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ እና የተለያዩ ከቤት ውጪ የሚደረጉ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲሳተፉ ያበረታታል።
በዚህም ከመጠን በላይ ውፍረትን፣ የስኳር በሽታን እና ሌሎች ከአኗኗር ዘይቤ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ሥር የሰደዱ ሕመሞችን ለመከላከል ይረዳል።
5. ለአዕምሮ ጤና - ንፁህ እና በጥሩ ሁኔታ የተያዘ የከተማ ገጽታ ከተሻሻለ የአዕምሮ ጤና ጋር ይያያዛል።
አረንጓዴ ቦታዎች፣ መናፈሻዎች እና ውበትን የሚያጎናጽፉ አካባቢዎች ጭንቀትን ይቀንሳሉ። ይህም ለአጠቃላይ ሥነ-ልቦናዊ ጤና ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል።
6. የምግብ ደኅንነት እንዲኖር ያደርጋል - ንፁህ ከተሞች ተገቢ የምግብ ማከማቻ፣ አያያዝ እና አወጋገድን ጨምሮ ለምግብ ደኅንነት ቅድሚያ ይሰጣሉ።
በዚህም በምግብ እና በውኃ መበከል የሚከሰቱ በሽዎችን ለመከላከል ያግዛል።
7. የማኅበረሰብ ትሥሥር ይፈጥራል - ንፁህ ከተማ በነዋሪዎች መካከል ጠንካራ የእርስ በእርስ ግንኙነት እና የኃላፊነት ስሜትን ያጎለብታሉ።
ጤናማ አካባቢን ለመፍጠር በሚደረጉ የጽዳት እንቅስቃሴዎች፣ ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ፕሮግራሞች እና በሌሎች ማኅበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ላይ ዜጎች የመሳተፍ ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ የማኅበረሰብ ተሳትፎ እና ትብብር እንዲጨምር ዕድል ይፈጥራል።
8. ድንገተኛ አደጋዎችን መቋቋም - ንፁህ ከተሞች እንደ ወረርሽኝ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ለመሰሉ የሕዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች እና ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ ናቸው።
በከተሞቹ በሚገባ የተያዙ መሠረተ ልማቶች፣ ቀልጣፋ የቆሻሻ አወጋገድ እና የተቀናጁ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሥርዓቶች በሕዝብ ጤና ላይ የሚያደርሱትን ተፅዕኖ ይቀንሳሉ።
ለከተሞች ንፅህና ቅድሚያ በመስጠት ጤናማ፣ ደስተኛ እና ጠንካራ ትውልድ መፍጠር ይቻላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም “ፅዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” በሚል መሪ ቃል የማኅበረሰቡ የፅዳት ባህል ክብርን የጠበቀ ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ይፋ አድርገዋል።
ለዚህ ተግባር የሚውል የ“ፅዱ ኢትዮጵያ” የዲጂታል ቴሌቶን ተጀምሯል።
ንፁህና ፅዱ ከተማን መፍጠር የማዘጋጃ ቤት አልያም የባለሥልጣናት ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎችን ንቁ ተሳትፎ እና የጋራ ጥረት የሚጠይቅ ጉዳይ ነው።
ኢትዮጵያዊያንም ለንቅናቄው በጎ ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ።
እስከአሁን በ#ፅዱኢትዮጵያ ቴሌቶኑ ያልተሳተፉ ዜጎችም በመጪዎቹ ቀናት እና ሳምንታትም እንዲቀላቀሉ ጥሪ መቅረቡ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።
ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የከተማ ንፅህና ከውበት ባለፈ በበርካታ መንገዶች ከህዝብ ጤና ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው።
ንፁህ እና ፅዱ ከተማ በሚተገብረው ከተማን ንፁህ በሚያደርጉ ተግባራት እና ፖሊሲዎች አካላዊ፣ አዕምሯዊ እና ማኅበራዊ ጤናን በማጠናከር ለነዋሪዎቹ ደኅንነት ቅድሚያ ይሰጣል።
ከመገለጫዎቹም መካከልም በቂ የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት እና አገልግሎቶችን ለሁሉም ነዋሪዎች ዝግጁ እና ተደራሽ ማድረግ እንዲሁም ንፁህ አየር፣ ውኃ እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን መገንባት ይገኝበታል።
ንፁህ እና ፅዱ ከተማ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ አካባቢያዊ እና ባህላዊ ሁኔታዎች የእርስ በርስ መስተጋብር ላይ በጎ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ይነገራል።
የንፁህ ከተማ እና አካባቢ የጤና ጥቅሞች፦
1. የአየር ብክለትን መቀነስ - ንፁህ ከተሞች ዝቅተኛ የአየር ብክለት ያላቸው ሲሆን ይህም በአየር ብክለት ሳብያ ሊከሰት የሚችልን የመተንፈሻ አካላት ሕመም፣ የልብ እና የደም ቧንቧ በሽታዎች እንዲሁም ያለጊዜ የመሞት ዕድል እንዲቀንስ ያስችላል።
2. የውኃ ወለድ በሽታዎችን መከላከል - በንፁህ ከተሞች የሚተገበሩ የቆሻሻ አወጋገድ እና የንፅህና አጠባበቅ አሠራሮች የውኃ ምንጮችን ከመበከል ይከላከላሉ። ይህም እንደ ኮሌራ፣ ታይፎይድ፣ ትኩሳት እና ተቅማጥ ያሉ የውኃ ወለድ በሽታዎችን ለመከላከል ያግዛል።
3. ወባን የመሰሉ ትንኝ ወለድ በሽታዎችን መቆጣጠር - ንፁህ ከተሞች እንደ ትንኝ እና ዝንብ በመሳሰሉ ነፍሳት አማካኝነት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመከላከል ጠንካራ ቁጥጥር ያደርጋሉ።
ንፁህ ከተሞች ነፍሳቱ በከተሞች እንዳይራቡ የአካባቢ ንፅህናን በመጠበቅ በበሽታዎቹ የመያዝ ዕድልን ይቀንሳሉ።
4. የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማስተዋወቅ - ንፁህ የሆነ ከተማ ደኅንነታቸው የተጠበቀ እና ማራኪ የሕዝብ ቦታዎችን በማቅረብ ይታወቃል።
ይህም ነዋሪዎች የእግር እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ እና የተለያዩ ከቤት ውጪ የሚደረጉ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲሳተፉ ያበረታታል።
በዚህም ከመጠን በላይ ውፍረትን፣ የስኳር በሽታን እና ሌሎች ከአኗኗር ዘይቤ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ሥር የሰደዱ ሕመሞችን ለመከላከል ይረዳል።
5. ለአዕምሮ ጤና - ንፁህ እና በጥሩ ሁኔታ የተያዘ የከተማ ገጽታ ከተሻሻለ የአዕምሮ ጤና ጋር ይያያዛል።
አረንጓዴ ቦታዎች፣ መናፈሻዎች እና ውበትን የሚያጎናጽፉ አካባቢዎች ጭንቀትን ይቀንሳሉ። ይህም ለአጠቃላይ ሥነ-ልቦናዊ ጤና ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል።
6. የምግብ ደኅንነት እንዲኖር ያደርጋል - ንፁህ ከተሞች ተገቢ የምግብ ማከማቻ፣ አያያዝ እና አወጋገድን ጨምሮ ለምግብ ደኅንነት ቅድሚያ ይሰጣሉ።
በዚህም በምግብ እና በውኃ መበከል የሚከሰቱ በሽዎችን ለመከላከል ያግዛል።
7. የማኅበረሰብ ትሥሥር ይፈጥራል - ንፁህ ከተማ በነዋሪዎች መካከል ጠንካራ የእርስ በእርስ ግንኙነት እና የኃላፊነት ስሜትን ያጎለብታሉ።
ጤናማ አካባቢን ለመፍጠር በሚደረጉ የጽዳት እንቅስቃሴዎች፣ ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ፕሮግራሞች እና በሌሎች ማኅበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ላይ ዜጎች የመሳተፍ ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ የማኅበረሰብ ተሳትፎ እና ትብብር እንዲጨምር ዕድል ይፈጥራል።
8. ድንገተኛ አደጋዎችን መቋቋም - ንፁህ ከተሞች እንደ ወረርሽኝ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ለመሰሉ የሕዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች እና ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ ናቸው።
በከተሞቹ በሚገባ የተያዙ መሠረተ ልማቶች፣ ቀልጣፋ የቆሻሻ አወጋገድ እና የተቀናጁ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሥርዓቶች በሕዝብ ጤና ላይ የሚያደርሱትን ተፅዕኖ ይቀንሳሉ።
ለከተሞች ንፅህና ቅድሚያ በመስጠት ጤናማ፣ ደስተኛ እና ጠንካራ ትውልድ መፍጠር ይቻላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም “ፅዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” በሚል መሪ ቃል የማኅበረሰቡ የፅዳት ባህል ክብርን የጠበቀ ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ይፋ አድርገዋል።
ለዚህ ተግባር የሚውል የ“ፅዱ ኢትዮጵያ” የዲጂታል ቴሌቶን ተጀምሯል።
ንፁህና ፅዱ ከተማን መፍጠር የማዘጋጃ ቤት አልያም የባለሥልጣናት ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎችን ንቁ ተሳትፎ እና የጋራ ጥረት የሚጠይቅ ጉዳይ ነው።
ኢትዮጵያዊያንም ለንቅናቄው በጎ ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ።
እስከአሁን በ#ፅዱኢትዮጵያ ቴሌቶኑ ያልተሳተፉ ዜጎችም በመጪዎቹ ቀናት እና ሳምንታትም እንዲቀላቀሉ ጥሪ መቅረቡ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።
👍2
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ የባለጉዳይ የቅሬታ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ አደረገ።
*አዳስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተቋሙ ላይ የሚፈጠሩ ቅሬታዎችን መቀበል የሚያስችል ባር ኮድ የያዘ ፎርም ይፋ አደረገ።
ተቋሙ የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማዘመንና ከመቼውም ጊዜ በላይ የህብረተሰብ አገልጋይነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን የቅሬታ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ በማድረጉ ማንኛውም ባለጉዳይ በተቋሙ ላይ ያለውን ቅሬታ በቀላሉ በማቅረብ ቅሬታው መፈታቱን መከታተል እንደሚች ያሳወቁት የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ናቸው።
አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ 9995 የተባለ ነፃ የስልክ መስመር እንዳለውና የተለያዩ ጥቆማዎችን እንደሚቀበልና ከህብረተሰቡ ጋር ተቀራርቦ እየሠራ እንደሚገኝ አስታውሰዋል።
*አዳስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተቋሙ ላይ የሚፈጠሩ ቅሬታዎችን መቀበል የሚያስችል ባር ኮድ የያዘ ፎርም ይፋ አደረገ።
ተቋሙ የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማዘመንና ከመቼውም ጊዜ በላይ የህብረተሰብ አገልጋይነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን የቅሬታ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ በማድረጉ ማንኛውም ባለጉዳይ በተቋሙ ላይ ያለውን ቅሬታ በቀላሉ በማቅረብ ቅሬታው መፈታቱን መከታተል እንደሚች ያሳወቁት የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ናቸው።
አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ 9995 የተባለ ነፃ የስልክ መስመር እንዳለውና የተለያዩ ጥቆማዎችን እንደሚቀበልና ከህብረተሰቡ ጋር ተቀራርቦ እየሠራ እንደሚገኝ አስታውሰዋል።
👍1
ባለስልጣኑ ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አስተዳደር የልዑካን ቡድን አባላት የስራ ተሞክሮውን አጋራ!
ሚያዚያ 22/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች ባለስልጣኑ ያለውን ልምድና ተሞክሮውን በሰነድ የተደገፈ ማብራሪያ በመስጠት ልምዱን አጋርቷል፡፡
ሰነዱን ያቀረቡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ የተቋሙ የስራ ተሞክሮውን መረጃ ፣የተቋም አደረጃጀት፣አሰራር፣ የመመሪያ ዝግጅት ፤የሰው ሃይል አደረጃጀት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር አስረድተዋል።
የባለስልጣኑ የስልጠናና የቅድመ መከላከል ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በተሞክሮ ማጋራቱ ወቅት እንተገለጹት ተቋሙ የከተማዋን ገጽታ ለመቀየር የራሱን ድርሻ ለመወጣት በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸው በዚህም ውጤት መገኘቱን በመግለጽ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከዚህ ልምድ በመውሰድ እና ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ስራዎች መስራት እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡
የባለስልጣኑዋና ፅ/ቤት ሀላፊ በበኩላቸው ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጠንክሮ በመስራት በጊዜ ሂደት ለውጥ ማምጣቱን በመግለፅ በሚያደርገው ልማታዊ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የትዊተር/X/ ሚዲያ ገፃችን
https://x.com/Addis_Denb?t=u8wW3qnxWk48GYzJ4RD96Q&s=09
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
ሚያዚያ 22/2016 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች ባለስልጣኑ ያለውን ልምድና ተሞክሮውን በሰነድ የተደገፈ ማብራሪያ በመስጠት ልምዱን አጋርቷል፡፡
ሰነዱን ያቀረቡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ የተቋሙ የስራ ተሞክሮውን መረጃ ፣የተቋም አደረጃጀት፣አሰራር፣ የመመሪያ ዝግጅት ፤የሰው ሃይል አደረጃጀት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር አስረድተዋል።
የባለስልጣኑ የስልጠናና የቅድመ መከላከል ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በተሞክሮ ማጋራቱ ወቅት እንተገለጹት ተቋሙ የከተማዋን ገጽታ ለመቀየር የራሱን ድርሻ ለመወጣት በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸው በዚህም ውጤት መገኘቱን በመግለጽ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከዚህ ልምድ በመውሰድ እና ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ስራዎች መስራት እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡
የባለስልጣኑዋና ፅ/ቤት ሀላፊ በበኩላቸው ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጠንክሮ በመስራት በጊዜ ሂደት ለውጥ ማምጣቱን በመግለፅ በሚያደርገው ልማታዊ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ለልዑካን ቡድኑ ገልፀዋል፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የትዊተር/X/ ሚዲያ ገፃችን
https://x.com/Addis_Denb?t=u8wW3qnxWk48GYzJ4RD96Q&s=09
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
👍4
ፅዱ እና ውብ ኢትዮጵያ ለመፍጠር ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀላፊነት አለበት
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተጀመረውን የ"ፅዱ ጎዳና -ኑሮ በጤና" ንቅናቄ ጥሪ ተቀብለው የተቋማችን አመራሮች እና ሰራተኞች "ፅዱ ኢትዮጵያ" ለመፍጠር በተጀመረው ዲጂታል ቴሌቶን ላይ በንቁ ተሳትፎ ተቀላቅለዋል።
ጥሪውን ተቀብለው የ“ጽዱ ጎዳና-ኑሮ በጤና” ንቅናቄን ለተሳተፉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና በራሳቸው ስም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
ሌሎች ያልተሳተፋችሁ አመራሮች እና ሰራተኞች ይህንን የበጎ ተግባር አላማ መሳካትም ሁሉም ሰው ያገባኛል በሚል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው ሂሳብ ቁጥር 1000623230248 የ“ጽዱ ጎዳና-ኑሮ በጤና” ንቅናቄን እንዲቀላቀሉና በስራው የራሳችሁ አሻራ እንድታስቀምጡ እና ሌሎችም እንዲቀላቀሉ እንድታስተባብሩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና በራሳቸው ስም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል::
በመጨረሻም እንደ ተቋማችን የተሠበሠበው ብር መረጃው ተሰብስቦ ለተቋሙ ሪፖርት መደረግ እንዳለበት ገልፀዋል።
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተጀመረውን የ"ፅዱ ጎዳና -ኑሮ በጤና" ንቅናቄ ጥሪ ተቀብለው የተቋማችን አመራሮች እና ሰራተኞች "ፅዱ ኢትዮጵያ" ለመፍጠር በተጀመረው ዲጂታል ቴሌቶን ላይ በንቁ ተሳትፎ ተቀላቅለዋል።
ጥሪውን ተቀብለው የ“ጽዱ ጎዳና-ኑሮ በጤና” ንቅናቄን ለተሳተፉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና በራሳቸው ስም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
ሌሎች ያልተሳተፋችሁ አመራሮች እና ሰራተኞች ይህንን የበጎ ተግባር አላማ መሳካትም ሁሉም ሰው ያገባኛል በሚል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው ሂሳብ ቁጥር 1000623230248 የ“ጽዱ ጎዳና-ኑሮ በጤና” ንቅናቄን እንዲቀላቀሉና በስራው የራሳችሁ አሻራ እንድታስቀምጡ እና ሌሎችም እንዲቀላቀሉ እንድታስተባብሩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና በራሳቸው ስም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል::
በመጨረሻም እንደ ተቋማችን የተሠበሠበው ብር መረጃው ተሰብስቦ ለተቋሙ ሪፖርት መደረግ እንዳለበት ገልፀዋል።
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ
👍7
"በጎነት ለራስ ነው ካለን ላይ አካፍለን እና ተካፍለን መብላት ኢትዮጵያዊ ባህላችን ነው" አቶ ዳኜ ሒርጳሣ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ
24/08/2016 ዓ.ም
*አዲስአበባ *
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ የፋሲካ በዓልን አስመልክቶ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከናወነ።
በመርሃ ግብሩ የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳኜ ሒርጳሣ እንደገለፁት በዛሬው ዕለት ለሚያሳድጋቸው 9 ህፃናት ከሰራተኛው ወርሀዊ መዋጮ የተሰበሰበው በገንዘብ ለእያንዳንዳቸው 1300 ብር እና በዓይነት በጎፈቃደኞችን በማስተባበር ዱቄት፤ መኮረኒ፤ሩዝ፣ሳሙናና ሶፍት በስጦታ ማበርከቱን ገልፀዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም "በጎነት ለራስ ነው ካለን ላይ አካፍለን እና ተካፍለን መብላት ኢትዮጵያዊ ባህላችን ነው" በማለት በአሉን በአብሮነት እና በጋራ ለማሳለፍ በማስብ ለፋሲካ በዓል መዋያ የሚሆን የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር ለ54 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ነዋሪዎች ፣9 የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የሚያሳድጋቸው ህፃናት እንዲሁም 14 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የፅ/ቤቱ ሰራተኞች ማዕድ ማጋራታቸውን ገልፀዋል፡፡
በዕለቱም በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙልጌታ ተስፋዬ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ህገወጥነት ከመከላከልና እርምጃ ከመውሰድ ባሻገር ለአቅመ ደካሞች ቤት መገንባትና ለወገኖቹ አጋዥ መሆኑ በመግለፅ ህብረተስቡ ይህንን በመረዳት ከደንብ ማስከበር ጋራ በመሆን ህገወጥነትን መከላከል እንዳለበት አሳስበዋል ፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ለመስጠት ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
24/08/2016 ዓ.ም
*አዲስአበባ *
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ የፋሲካ በዓልን አስመልክቶ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከናወነ።
በመርሃ ግብሩ የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳኜ ሒርጳሣ እንደገለፁት በዛሬው ዕለት ለሚያሳድጋቸው 9 ህፃናት ከሰራተኛው ወርሀዊ መዋጮ የተሰበሰበው በገንዘብ ለእያንዳንዳቸው 1300 ብር እና በዓይነት በጎፈቃደኞችን በማስተባበር ዱቄት፤ መኮረኒ፤ሩዝ፣ሳሙናና ሶፍት በስጦታ ማበርከቱን ገልፀዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም "በጎነት ለራስ ነው ካለን ላይ አካፍለን እና ተካፍለን መብላት ኢትዮጵያዊ ባህላችን ነው" በማለት በአሉን በአብሮነት እና በጋራ ለማሳለፍ በማስብ ለፋሲካ በዓል መዋያ የሚሆን የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር ለ54 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ነዋሪዎች ፣9 የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የሚያሳድጋቸው ህፃናት እንዲሁም 14 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የፅ/ቤቱ ሰራተኞች ማዕድ ማጋራታቸውን ገልፀዋል፡፡
በዕለቱም በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙልጌታ ተስፋዬ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ህገወጥነት ከመከላከልና እርምጃ ከመውሰድ ባሻገር ለአቅመ ደካሞች ቤት መገንባትና ለወገኖቹ አጋዥ መሆኑ በመግለፅ ህብረተስቡ ይህንን በመረዳት ከደንብ ማስከበር ጋራ በመሆን ህገወጥነትን መከላከል እንዳለበት አሳስበዋል ፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ለመስጠት ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
👍2