ባለስልጣኑ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 1,750,000(አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ) ብር መቅጣቱ አስታወቀ
10/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በዛሬው ዕለት በወንዞችና የወንዞች ዳርቻ በካይ ቆሻሻ የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 1,750,000(አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ) ብር መቅጣቱ አስታውቋል።
ቅጣቶቹ በቄርቆስ ክፍለ ከተማ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ወደ ወንዝ በካይ ፍሳሾችን በመልቀቁ በድምሩ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር፣ በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 400,000/አራት መቶ ሺህ/ ብርተቀጥተዋል።
በተጨማሪም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወንዝ በመበከል ፋፋ የምግብ ፋብሪካ 400,000/አራት መቶ ሺህ/ ብር በጉለሌና በየካ ክፍለ ከተማ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቅ 150,000(ሀምሳ ሺህ) ብር እና 200,000(ሁለት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ ህብረተሰቡና ተቋማት ከዚህ ዓይነት ድርጊት እንዲቆጠቡም እያሳሰበ የሚወስደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በተጨማሪም ህብረተሰቡ ለማንኛውም አይነት የደንብ መተላለፍ በነፃ ስልክ 9995 መረጃና ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
10/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በዛሬው ዕለት በወንዞችና የወንዞች ዳርቻ በካይ ቆሻሻ የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 1,750,000(አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ) ብር መቅጣቱ አስታውቋል።
ቅጣቶቹ በቄርቆስ ክፍለ ከተማ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ወደ ወንዝ በካይ ፍሳሾችን በመልቀቁ በድምሩ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር፣ በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 400,000/አራት መቶ ሺህ/ ብርተቀጥተዋል።
በተጨማሪም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወንዝ በመበከል ፋፋ የምግብ ፋብሪካ 400,000/አራት መቶ ሺህ/ ብር በጉለሌና በየካ ክፍለ ከተማ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቅ 150,000(ሀምሳ ሺህ) ብር እና 200,000(ሁለት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ ህብረተሰቡና ተቋማት ከዚህ ዓይነት ድርጊት እንዲቆጠቡም እያሳሰበ የሚወስደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በተጨማሪም ህብረተሰቡ ለማንኛውም አይነት የደንብ መተላለፍ በነፃ ስልክ 9995 መረጃና ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ
10/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ለአመራሮች፣ ለባለሙያዎችና ኦፊሰሮች የአጭር ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርስቲው አመራሮች ውይይት አካሄዱ ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አመራሩና ባለሙያው የአፈጻጸም አቅሙ ጠንካራ እንዲሆን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ እና መልካም አስተዳደርን በመረዳት የደንብ ማስከበር አገልግሎቶችን በሚገባ እንዲሰጡ ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና ግንዛቤን ለማሳደግ አስፈለጊ መሆኑን ገልጸዋል ።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስራቸዉን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል፡፡
አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለሰልጣኞች አመቺ ቦታ እንዲሁም ከተቋሙ ጋር ተዛማጅነት ያለው ስልጠና ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች እና ኦፊሰሮች ስልጠና የተዘጋጀ መነሻ ሀሳብ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና አቅም ግንባታ ማዕከል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ፍቃዱ ጌታቸው አቅርበው ሰፊ ውይይት ተደርጓል ።
በተቋሙ ተመድበው የሚሰሩ አመራሮች እና ኦፊሰሮች ወቅቱን መሰረት ያደረገ ስልጠና በመስጠት የእውቀት ፣ክህሎት ፣አመለካከት ፣ የስነምግባር እና የስራ አፈጻጸማቸውን የላቀ በማድረግ ስለተቋማቸውና ስለሚሰጡት አገልግሎት ሁኔታ ልዩ ባህሪ በቂ ግንዛቤ ይዘው የህዝብ አገልጋይነት ስሜትን ተላብሰው የተቋሙን አላማ ለማሳካት በቀጣይ የሚሰጠው ስልጠና ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው በመድረኩ ተገልጿል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
10/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ለአመራሮች፣ ለባለሙያዎችና ኦፊሰሮች የአጭር ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርስቲው አመራሮች ውይይት አካሄዱ ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አመራሩና ባለሙያው የአፈጻጸም አቅሙ ጠንካራ እንዲሆን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ እና መልካም አስተዳደርን በመረዳት የደንብ ማስከበር አገልግሎቶችን በሚገባ እንዲሰጡ ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና ግንዛቤን ለማሳደግ አስፈለጊ መሆኑን ገልጸዋል ።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስራቸዉን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል፡፡
አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለሰልጣኞች አመቺ ቦታ እንዲሁም ከተቋሙ ጋር ተዛማጅነት ያለው ስልጠና ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች እና ኦፊሰሮች ስልጠና የተዘጋጀ መነሻ ሀሳብ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና አቅም ግንባታ ማዕከል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ፍቃዱ ጌታቸው አቅርበው ሰፊ ውይይት ተደርጓል ።
በተቋሙ ተመድበው የሚሰሩ አመራሮች እና ኦፊሰሮች ወቅቱን መሰረት ያደረገ ስልጠና በመስጠት የእውቀት ፣ክህሎት ፣አመለካከት ፣ የስነምግባር እና የስራ አፈጻጸማቸውን የላቀ በማድረግ ስለተቋማቸውና ስለሚሰጡት አገልግሎት ሁኔታ ልዩ ባህሪ በቂ ግንዛቤ ይዘው የህዝብ አገልጋይነት ስሜትን ተላብሰው የተቋሙን አላማ ለማሳካት በቀጣይ የሚሰጠው ስልጠና ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው በመድረኩ ተገልጿል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
❤5
ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ውይይት እያካሄደ ይገኛል
11/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል፡፡
በዉይይቱም የባለሥልጣኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፤ የክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣የባለድርሻ አካላት ኃላፊዎችና የማዕከሉ ዳይሬክተሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የመረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ነው፡፡
11/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል፡፡
በዉይይቱም የባለሥልጣኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፤ የክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣የባለድርሻ አካላት ኃላፊዎችና የማዕከሉ ዳይሬክተሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የመረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ነው፡፡
👍2