ከባለድርሻ ተቋመት ጋር የቅንጅት ተግባራት በማጠናከር ከተማችን ውብ፣ ጽዱና የደንብ መተላለፍ የቀነሰባት ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ
11/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎችን አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከልና የህግ ማስከበር ስራን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመናበብ በመስራት በከተማችን የደንብ መተላለፍ 83% እንዲቀንስ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል ።
አክለውም ደንብ ማስከበር በከተማዋ አስተዳደር የተሰጠዎን ተልዕኮ ለመወጣት የቅንጅት ስራዎች ከፍተኛ ሚና ያላቸው እንደመሆኑ በጋራ የመስራት ባህልን በማጠናከር ከተማችን ውብ ጽዱ የደንብ መተላለፍ የቀነሰባት ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል ።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥነትን በመከላከል፣ ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ ፣ የምሽት ንግድን በመደገፍ ፣ የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ብክለትን በመከላከል እንዲሁም የኮሪደር ልማቶች ደህንነት በመጠበቅ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ ውጤታማ ስራዎች መስራት መቻሉን በመድረኩ ተገልጸዋል ።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች በጥንካሬ እና በጉድለት በሰነድ ተለይተው በባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥና ድጋፍ ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ ተቋሙ ከ20 ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር በቅንጅት ለመስራት በሰነድ በተፈራረመው ልክ ወደ ስራ በመግባት በጋራ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
የመረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ነው፡፡
11/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎችን አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከልና የህግ ማስከበር ስራን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመናበብ በመስራት በከተማችን የደንብ መተላለፍ 83% እንዲቀንስ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል ።
አክለውም ደንብ ማስከበር በከተማዋ አስተዳደር የተሰጠዎን ተልዕኮ ለመወጣት የቅንጅት ስራዎች ከፍተኛ ሚና ያላቸው እንደመሆኑ በጋራ የመስራት ባህልን በማጠናከር ከተማችን ውብ ጽዱ የደንብ መተላለፍ የቀነሰባት ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል ።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥነትን በመከላከል፣ ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ ፣ የምሽት ንግድን በመደገፍ ፣ የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ብክለትን በመከላከል እንዲሁም የኮሪደር ልማቶች ደህንነት በመጠበቅ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ ውጤታማ ስራዎች መስራት መቻሉን በመድረኩ ተገልጸዋል ።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች በጥንካሬ እና በጉድለት በሰነድ ተለይተው በባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥና ድጋፍ ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ ተቋሙ ከ20 ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር በቅንጅት ለመስራት በሰነድ በተፈራረመው ልክ ወደ ስራ በመግባት በጋራ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
የመረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ነው፡፡
👍2