በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የምሽት የንግድ ተቋማት ሰላማዊ ግብይት እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገለፀ
16- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማው ንግድ ቢሮ ጋር በመሆን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ስራዎች እንቅስቃሴ ምልከታ አካሂደዋል።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምሽት የንግድ እንቅስቃሴ ወቅት የደንብ ጥሰት እንዳይኖር የምሽት ምድብ በመመደብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የምሽት ስራው የሚያስተጓጉል የደንብ ጥሰትና የፀጥታ ችግር እንዳላጋጠመ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደተናገሩት ከተማችን አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረትና የበርካታ ሃገራት ኢምባሲዎች መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን ይህንን የሚመጥን የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ እንዲኖራት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ይህም በከተማዋን አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፍ ይበልጥ የሚያነቃቃ ነው ብለዋል።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው የፀጥታ ችግር እንዳይኖር ህብረተሰቡን በባለቤትነት በማሳትፍ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው የምሽት ግብይት ለንግዱ ማህበረሰብ እና በትራንስፖርት ለተሰማሩት ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በተጨማሪ ማህበራዊ መስተጋብር ከማሳደግ አንፃር ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።
በተለያዩ ጊዜያት በሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አቶ አድማሱ ገልፀው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎችም ያለምንም ስጋት እንዲገበያዩ ጠይቀዋል።
16- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማው ንግድ ቢሮ ጋር በመሆን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ስራዎች እንቅስቃሴ ምልከታ አካሂደዋል።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምሽት የንግድ እንቅስቃሴ ወቅት የደንብ ጥሰት እንዳይኖር የምሽት ምድብ በመመደብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የምሽት ስራው የሚያስተጓጉል የደንብ ጥሰትና የፀጥታ ችግር እንዳላጋጠመ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደተናገሩት ከተማችን አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረትና የበርካታ ሃገራት ኢምባሲዎች መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን ይህንን የሚመጥን የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ እንዲኖራት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ይህም በከተማዋን አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፍ ይበልጥ የሚያነቃቃ ነው ብለዋል።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው የፀጥታ ችግር እንዳይኖር ህብረተሰቡን በባለቤትነት በማሳትፍ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው የምሽት ግብይት ለንግዱ ማህበረሰብ እና በትራንስፖርት ለተሰማሩት ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በተጨማሪ ማህበራዊ መስተጋብር ከማሳደግ አንፃር ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።
በተለያዩ ጊዜያት በሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አቶ አድማሱ ገልፀው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎችም ያለምንም ስጋት እንዲገበያዩ ጠይቀዋል።
👍5❤1
ባለስልጣኑ የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን የበከለ ግለሰብ 3 መቶ ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
ሐምሌ 17/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ልዩ ቦታው ጎርጎርዮስ አካባቢ የሚገኘው ክላሲክ ኮንሰልቲንግ እንጂነርስ ኃላፊነቱ የተረጋገጠ የግል ማህበር የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን በመበከል ደንብ በመተላለፉ መቀጣቱ ተገለፀ።
ተቋሙ ከዚህ በፊት እንዲያስተካክል ግንዛቤ ቢሰጠውም ምንም አይነት የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ በደንብ ቁጥር 180 /2017 መሰረት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር መቀጣቱን የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ እስጢፋኖስ ገልፀዋል።
ባለስልጣን መረጃ በመስጠት ብክለት መከላከል እንዲቻል የጠቆሙትን የህብረተሰብ ክፍሎችን እያመሰገነ በቀጣይ ህብረተሰቡና ተቋማት ከዚህ ዓይነት ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል::
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 17/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ልዩ ቦታው ጎርጎርዮስ አካባቢ የሚገኘው ክላሲክ ኮንሰልቲንግ እንጂነርስ ኃላፊነቱ የተረጋገጠ የግል ማህበር የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን በመበከል ደንብ በመተላለፉ መቀጣቱ ተገለፀ።
ተቋሙ ከዚህ በፊት እንዲያስተካክል ግንዛቤ ቢሰጠውም ምንም አይነት የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ በደንብ ቁጥር 180 /2017 መሰረት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር መቀጣቱን የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ እስጢፋኖስ ገልፀዋል።
ባለስልጣን መረጃ በመስጠት ብክለት መከላከል እንዲቻል የጠቆሙትን የህብረተሰብ ክፍሎችን እያመሰገነ በቀጣይ ህብረተሰቡና ተቋማት ከዚህ ዓይነት ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል::
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍12
ወንዝና አካባቢ የበከሉ ሁለት ተቋማት 600,000 (ስድስት መቶ ሺህ) ብር ተቀጡ
ሐምሌ 17/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ልዩ ቦታው ይርጋሀይሌ አካባቢ የሚገኘው ስኬት ህንፃ ኃላፊነቱ የተረጋገጠ የግል ማህበር የዝናብ ውሀ ሽፋን በማድረግ የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን በመበከል ደንብ በመተላለፉ 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) መቀጣቱን ተገለፀ።
በተመሳሳይ በዛሬው እለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ኖህ ሪል ሰቴት ወደ ወንዝ ቆሻሻ በመጣሉ 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) ተቀጥቷል።
ተቋማቶቹ ከዚህ በፊት ግንዛቤ የተፈጠረላቸው መሆኑና ቅጣቱ በደንብ ቁጥር 180 /2017 መሰረት እያንዳንዳቸው 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) በድምሩ 600,000 (ስድስት መቶ ሺህ) ብር መቀጣታቸውን የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊዎች ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የክረምቱን የዝናብ ውሀ ሽፋን በማድረግ ቆሻሻ የሚለቁ ግለሰቦችና ተቋማት አካባቢውን ከመበከል በተጨማሪ የከተማው ማህበረሰብ የፍሳሽ ማስወገጃዎች በመድፈን ለጎርፍ አደጋ የሚያጋልጥ በመሆኑ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቧል።
ባለስልጣን መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸው የሚወጡ ነዋሪዎችን እያመሰገነ መላው የከተማው ነዋሪ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ 9995 ነፃ የስልክ መስመር እንዲጠቀሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 17/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ልዩ ቦታው ይርጋሀይሌ አካባቢ የሚገኘው ስኬት ህንፃ ኃላፊነቱ የተረጋገጠ የግል ማህበር የዝናብ ውሀ ሽፋን በማድረግ የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን በመበከል ደንብ በመተላለፉ 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) መቀጣቱን ተገለፀ።
በተመሳሳይ በዛሬው እለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ኖህ ሪል ሰቴት ወደ ወንዝ ቆሻሻ በመጣሉ 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) ተቀጥቷል።
ተቋማቶቹ ከዚህ በፊት ግንዛቤ የተፈጠረላቸው መሆኑና ቅጣቱ በደንብ ቁጥር 180 /2017 መሰረት እያንዳንዳቸው 300,000 (ሶትት መቶ ሺ ብር) በድምሩ 600,000 (ስድስት መቶ ሺህ) ብር መቀጣታቸውን የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊዎች ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የክረምቱን የዝናብ ውሀ ሽፋን በማድረግ ቆሻሻ የሚለቁ ግለሰቦችና ተቋማት አካባቢውን ከመበከል በተጨማሪ የከተማው ማህበረሰብ የፍሳሽ ማስወገጃዎች በመድፈን ለጎርፍ አደጋ የሚያጋልጥ በመሆኑ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቧል።
ባለስልጣን መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸው የሚወጡ ነዋሪዎችን እያመሰገነ መላው የከተማው ነዋሪ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ 9995 ነፃ የስልክ መስመር እንዲጠቀሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍7
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ
19/11/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ።
በፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ከማዕከል እስከ ወረዳ አመራሩና ኦፊሰሩ በመናበብ ቀን ከለሊት 7/24 በመስራቱ በአፈጻጸሙ በከተማ ደረጃ አንደኛ በመውጣት የዘመናዊ መኪና ተሸላሚ ሆነናል ሲሉ ገልጸዋል ።
ተቋማችን ለዚህ ስኬት ያበቃው የከተማችን ፈጣን እድገት ያማከለ እቅድ አቅዶ ከክ/ከተማና ወረዳዎች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ በማድረግ በየጊዜው መገመገም መቻሉ በተጨማሪም ህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው በማድረግ ደንብ ጥሰትን የሚጸየፍ ለኦፊሰሩም አጋዥ ሆኖ በጋራ በመስራቱ ነው ብለዋል።
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጋላ ዓለሙ በክፍለ ከተማ የሚታዪ የደንብ ጥሰቶችን በመከላከል በመቆጣጠርና ለህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ በመፍጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰቶችን እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል ።
በመድረኩ የተገኙት የክ/ከተማው አፈ ጉባኤ አቶ ወጋየሁ ኃይሉ ደንብ ማስከበር የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ ከመወጣት ጎን ለጎን የተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ በመሳተፍ የአቅመ ደካማ ቤት በማደስ፣ ማዕድ በማጋራት አረንጓዴ አሻራ ላይ በመሳተፍ በአይን የሚታይ በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ በህብረተሰቡም ተቀባይነቱ እየሰፋ እየሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
አክለውም ተቋሙ በከተማ አስተዳደር በተደረገው ምዘና በአፈጻጸሙ አንደኛ መውጣቱ የጥንካሬው ውጤት መሆኑን ገልፀዋል ።
በመድረኩ የተገኙት የክ/ከተማው የብልጽግና ፖርቲ ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ ደንብ ማስከበር ህገወጥነትን የሚከላከል ሰላምና ጸጥታን የሚያስከብር በከተማዋ እድገት የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋፅኦ በመወጣት የተሰሩ ፕሮጀክቶችና ኮሪደር ልማቶችን ውብ ጽዱ ሆነው እንዲቆዩና ለተገልጋዮች ምቹ በማድረግ በርካታ ተግባር አከናውኗል ሲሉ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ለወረዳው አመራሮች ፣ ከ1 - 3 ለወጡ ኦፊሰሮች፣ ለባለድርሻ አካላት፣ ለጸጥታ አካላት እንዲሁም ከጽ/ቤቱ ጎን ለስራው መሳካት ድጋፍ ላደረጉ አካላት የምስጋናና የእውቅና ሽልማት ተሰጥቷል ።
በ2017 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ወረዳዎች የእውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን
1ኛ ወረዳ 13
2ኛ ወረዳ 05
3ኛ ወረዳ 10 እና 2 የዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸለሚ ሆነዋል።
እንዲሁም በህጉና መመሪያው መሠረት አድርጎ እርምጃ የወሰዱና ቅጣቱን ገቢ ማድረግ ወረዳ 13 እና 11 የሞተር ሳይክል ተሸላሚ ሆነዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
19/11/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ።
በፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ከማዕከል እስከ ወረዳ አመራሩና ኦፊሰሩ በመናበብ ቀን ከለሊት 7/24 በመስራቱ በአፈጻጸሙ በከተማ ደረጃ አንደኛ በመውጣት የዘመናዊ መኪና ተሸላሚ ሆነናል ሲሉ ገልጸዋል ።
ተቋማችን ለዚህ ስኬት ያበቃው የከተማችን ፈጣን እድገት ያማከለ እቅድ አቅዶ ከክ/ከተማና ወረዳዎች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ በማድረግ በየጊዜው መገመገም መቻሉ በተጨማሪም ህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው በማድረግ ደንብ ጥሰትን የሚጸየፍ ለኦፊሰሩም አጋዥ ሆኖ በጋራ በመስራቱ ነው ብለዋል።
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጋላ ዓለሙ በክፍለ ከተማ የሚታዪ የደንብ ጥሰቶችን በመከላከል በመቆጣጠርና ለህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ በመፍጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰቶችን እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል ።
በመድረኩ የተገኙት የክ/ከተማው አፈ ጉባኤ አቶ ወጋየሁ ኃይሉ ደንብ ማስከበር የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ ከመወጣት ጎን ለጎን የተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ በመሳተፍ የአቅመ ደካማ ቤት በማደስ፣ ማዕድ በማጋራት አረንጓዴ አሻራ ላይ በመሳተፍ በአይን የሚታይ በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ በህብረተሰቡም ተቀባይነቱ እየሰፋ እየሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
አክለውም ተቋሙ በከተማ አስተዳደር በተደረገው ምዘና በአፈጻጸሙ አንደኛ መውጣቱ የጥንካሬው ውጤት መሆኑን ገልፀዋል ።
በመድረኩ የተገኙት የክ/ከተማው የብልጽግና ፖርቲ ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ ደንብ ማስከበር ህገወጥነትን የሚከላከል ሰላምና ጸጥታን የሚያስከብር በከተማዋ እድገት የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋፅኦ በመወጣት የተሰሩ ፕሮጀክቶችና ኮሪደር ልማቶችን ውብ ጽዱ ሆነው እንዲቆዩና ለተገልጋዮች ምቹ በማድረግ በርካታ ተግባር አከናውኗል ሲሉ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ለወረዳው አመራሮች ፣ ከ1 - 3 ለወጡ ኦፊሰሮች፣ ለባለድርሻ አካላት፣ ለጸጥታ አካላት እንዲሁም ከጽ/ቤቱ ጎን ለስራው መሳካት ድጋፍ ላደረጉ አካላት የምስጋናና የእውቅና ሽልማት ተሰጥቷል ።
በ2017 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ወረዳዎች የእውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን
1ኛ ወረዳ 13
2ኛ ወረዳ 05
3ኛ ወረዳ 10 እና 2 የዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸለሚ ሆነዋል።
እንዲሁም በህጉና መመሪያው መሠረት አድርጎ እርምጃ የወሰዱና ቅጣቱን ገቢ ማድረግ ወረዳ 13 እና 11 የሞተር ሳይክል ተሸላሚ ሆነዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤8