ባለስልጣኑ ከሰላምና ፀጥታና ከንግድቢሮ አመራሮች ጋር በመሆን የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ የመስክ ምልከታ አደረገ
ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም
*የአዲስ አበባ ****
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሰላምና ፀጥታና ከንግድቢሮ አመራሮች ጋር በመሆን የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ የመስክ ምልከታ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ግብይት የወጣውን ደንብ ተግባራዊ መደረጉን የመስክ ምልከታ አካሄደ።
በጉብኝቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ በወ/ሮ ሊዲያ ግርማ፣በንግድ ቢሮ ሀላፊ በወ /ሮ ሀቢባ ሲራጅ እና የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እና ሌሎች የክፍለ ከተማውና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በምልከታውም የከተማውና የክፍለ ከተማው የህገወጥ ንግድ ቁጥጥር የገበያ ማረጋጋት ግብረ ኃይል አባላትም ተገኝተዋል፡፡
የጉብኝቱ ዓላማ የንግድ ተቋማት በተቀመጠላቸው የሥራ ሰዓት ገደብ ክፍት ሆነው በአገልግሎት ላይ መሆናቸውንናየወጣውን ደንብ ተግባራዊ መሆኑን ለማረጋገጥ እንደሆነ ተጠቅሷል።
በጉብኝቱም የተቋማት የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ተከትሎ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴን ይበልጥ እንደሚያሳድግ ተብራርቷል።
የምሽት ንግድ አገልግሎት መስፋፋት የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ በማነቃቃት የዜጎችን ገቢ ከፍ ከማድረግ ባለፈ ለተጨማሪ የሥራ ዕድሎች መፈጠርና የስራ ባህልን እንደሚያሳድግም ተመላክቷል።
በምልከታው የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኒእመተላህ ከበደ የተገኙ ሲሆን በክፍለ ከተማው የተቋማት የምሽት የስራ ሰዓት ገደብ አተገባበርን አስመልክቶ ለግብረ ሀይል አባላት ገለፃ አድርገዋል።
ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም
*የአዲስ አበባ ****
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሰላምና ፀጥታና ከንግድቢሮ አመራሮች ጋር በመሆን የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ የመስክ ምልከታ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ግብይት የወጣውን ደንብ ተግባራዊ መደረጉን የመስክ ምልከታ አካሄደ።
በጉብኝቱ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ በወ/ሮ ሊዲያ ግርማ፣በንግድ ቢሮ ሀላፊ በወ /ሮ ሀቢባ ሲራጅ እና የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እና ሌሎች የክፍለ ከተማውና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በምልከታውም የከተማውና የክፍለ ከተማው የህገወጥ ንግድ ቁጥጥር የገበያ ማረጋጋት ግብረ ኃይል አባላትም ተገኝተዋል፡፡
የጉብኝቱ ዓላማ የንግድ ተቋማት በተቀመጠላቸው የሥራ ሰዓት ገደብ ክፍት ሆነው በአገልግሎት ላይ መሆናቸውንናየወጣውን ደንብ ተግባራዊ መሆኑን ለማረጋገጥ እንደሆነ ተጠቅሷል።
በጉብኝቱም የተቋማት የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ተከትሎ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴን ይበልጥ እንደሚያሳድግ ተብራርቷል።
የምሽት ንግድ አገልግሎት መስፋፋት የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ በማነቃቃት የዜጎችን ገቢ ከፍ ከማድረግ ባለፈ ለተጨማሪ የሥራ ዕድሎች መፈጠርና የስራ ባህልን እንደሚያሳድግም ተመላክቷል።
በምልከታው የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኒእመተላህ ከበደ የተገኙ ሲሆን በክፍለ ከተማው የተቋማት የምሽት የስራ ሰዓት ገደብ አተገባበርን አስመልክቶ ለግብረ ሀይል አባላት ገለፃ አድርገዋል።
👍4❤1
ባለስልጣኑ እስከ ምሽቱ አራት ስዓት ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች በመቆጣጠር ሰላማዊ ግብይት እንዲኖር እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ እና ከንግድ ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ንግድ ስራዎችና ግብይት ላይ የወጣውን ደንብ ተግባራዊ መደረጉን የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የስራ ባህልን እንደ ሀገር ለማሳደግ የንግድ ሱቆች ስራዎች በምሽት እየሰሩ የሚገኙ ሲሆን አንዳንድ የደንብ ጥሰቶችና ህገወጥ እንቅስቃሴዎች ለመከላከል ደንብ ማስከበር ሽፍቱን አጥፎ እስከ ምሽቱ አራት ስዓት በመስራት የህገወጥ ንግድ ቁጥጥርና የገበያ ማረጋጋት ስራዎችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል ።
በከተማችን የሚገኙ የንግድ ሱቆች እስከ ምሽት 4:00 ሰዓት እየሰሩ እንደሚገኙ በተደረገው ምልከታ ሰላማዊ የሆነና ምንም አይነት የጸጥታ ችግር ሳይኖር የንግድ እንቅሰቃሴው በመልካም ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ በምልከታው ተረጋግጧል።
በምልከታው በአንዳንድ አካባቢዎችዎ ይታያሉ ተብለው ከነጋዴዎች የተሰጡ የትራንስፖርት ችግር አስተያየቶችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ እንዲሰጥና እንደሚስተካከል የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ተናግረዋል ።
አክለውም ምሽት ላይ የጸጥታ ችግር ይኖራል የሚል ስጋት እንዳይኖር በ7/24 የስራ ባህል የጸጥታ መዋቅሩ ከተማዋን እየጠበቀ የሚገኝ ሲሆን የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ተከትሎ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴን ይበልጥ አንደሚያሳድግ ገልጸዋል ።
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደተናገሩት ከተማችን ሶስተኛ የዲፕሎማሲ መቀመጫና ትልቅ ከተማ እንደመሆኗ የምሽት ንግድ መኖሩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው ላይ መነቃቃት የሚፈጥርና የስራ ባህልን የሚያሳድግ ነው።
በምልከታውም የባለስልጣኑ፣የሰላምና ጸጥታና የንግድ ቢሮ የከተማውና የክፍለ ከተማው አመራሮች ፣ የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ፣ኦፊሰሮችና የሰላም ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል ፡፡
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ እና ከንግድ ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ንግድ ስራዎችና ግብይት ላይ የወጣውን ደንብ ተግባራዊ መደረጉን የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የስራ ባህልን እንደ ሀገር ለማሳደግ የንግድ ሱቆች ስራዎች በምሽት እየሰሩ የሚገኙ ሲሆን አንዳንድ የደንብ ጥሰቶችና ህገወጥ እንቅስቃሴዎች ለመከላከል ደንብ ማስከበር ሽፍቱን አጥፎ እስከ ምሽቱ አራት ስዓት በመስራት የህገወጥ ንግድ ቁጥጥርና የገበያ ማረጋጋት ስራዎችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል ።
በከተማችን የሚገኙ የንግድ ሱቆች እስከ ምሽት 4:00 ሰዓት እየሰሩ እንደሚገኙ በተደረገው ምልከታ ሰላማዊ የሆነና ምንም አይነት የጸጥታ ችግር ሳይኖር የንግድ እንቅሰቃሴው በመልካም ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ በምልከታው ተረጋግጧል።
በምልከታው በአንዳንድ አካባቢዎችዎ ይታያሉ ተብለው ከነጋዴዎች የተሰጡ የትራንስፖርት ችግር አስተያየቶችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ እንዲሰጥና እንደሚስተካከል የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ተናግረዋል ።
አክለውም ምሽት ላይ የጸጥታ ችግር ይኖራል የሚል ስጋት እንዳይኖር በ7/24 የስራ ባህል የጸጥታ መዋቅሩ ከተማዋን እየጠበቀ የሚገኝ ሲሆን የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ተከትሎ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴን ይበልጥ አንደሚያሳድግ ገልጸዋል ።
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደተናገሩት ከተማችን ሶስተኛ የዲፕሎማሲ መቀመጫና ትልቅ ከተማ እንደመሆኗ የምሽት ንግድ መኖሩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው ላይ መነቃቃት የሚፈጥርና የስራ ባህልን የሚያሳድግ ነው።
በምልከታውም የባለስልጣኑ፣የሰላምና ጸጥታና የንግድ ቢሮ የከተማውና የክፍለ ከተማው አመራሮች ፣ የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ፣ኦፊሰሮችና የሰላም ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል ፡፡
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍7
የልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በወረዳ 05 የአቅመ ደካማ እናት የቤት እድሳት አስጀመረ
16/11/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራና ምክትል ስራ አስኪያጆች በተገኙበት በወረዳ 05 ነዋሪ የሆኑ አቅመ ደካማ ወ/ሮ አስታጥቃ ቢሻው ቤት በ90 ቀን እቅድ ውስጥ አድሶ ለማስረከብ አስጀምረዋል።
ተቋሙ በ90 ቀናት እቅድ ውስጥ የችግኝ ተከላ፣ የማዕድ ማጋራት፣ የደም ልገሳና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የማድረግ ስራዎችን አጠናክሮ እየሠራ እንደሚገኝ ሻለቃ ዘሪሁን አስታውሰው፤ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የአቅ ደካማ እናት ቤትን በአጭር ቀናት ውስጥ አድሶ ለማስረከብ ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ የ2017 በጀት ዓመትእቅድ አፈፃፀም በላቀ ውጤት በማጠናቀቅ ከከተማው አስተዳደር ሴክተር ተቋማት ጋር ተወዳድሮ 1ኛ በመውጣት የመኪና ሽልማት በማግኘቱ ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የህብረተሰብ ክፍሎችና አጠቃላይ የተቋሙ አመራሮች፣ ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችና ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
16/11/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራና ምክትል ስራ አስኪያጆች በተገኙበት በወረዳ 05 ነዋሪ የሆኑ አቅመ ደካማ ወ/ሮ አስታጥቃ ቢሻው ቤት በ90 ቀን እቅድ ውስጥ አድሶ ለማስረከብ አስጀምረዋል።
ተቋሙ በ90 ቀናት እቅድ ውስጥ የችግኝ ተከላ፣ የማዕድ ማጋራት፣ የደም ልገሳና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የማድረግ ስራዎችን አጠናክሮ እየሠራ እንደሚገኝ ሻለቃ ዘሪሁን አስታውሰው፤ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የአቅ ደካማ እናት ቤትን በአጭር ቀናት ውስጥ አድሶ ለማስረከብ ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ የ2017 በጀት ዓመትእቅድ አፈፃፀም በላቀ ውጤት በማጠናቀቅ ከከተማው አስተዳደር ሴክተር ተቋማት ጋር ተወዳድሮ 1ኛ በመውጣት የመኪና ሽልማት በማግኘቱ ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የህብረተሰብ ክፍሎችና አጠቃላይ የተቋሙ አመራሮች፣ ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችና ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍7❤4👎1👏1