ከ1100 በላይ የሚሆኑ የባለስልጣኑ የአመራሮችና ሰራተኞች የደም ልገሳ አደረጉ
ሐምሌ 11- 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር በመተባበር "ደም መስጠት ህይወት መስጠት ነው " በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሐ ግብር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም አከናወነ።
የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በክረምት በጎ ፍቃድ ከዘጠና ቀናት እቅድ አንዱ የሆነውን የደም የመለገስ መርሃ-ግብር አመራሩና ኦፍሰሩ በጋራ በመሆን በራስ ተነሳሽነት ደም ለመስጠት መገኘቱ የህሊና እርካታ የሚሰጥና ደም በመስጠት ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወት ለመታደግ መሆኑ ተናግረዋል።
አክለውም ደም ልገሳ የሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ የሚጠይቅ ታላቅ ሰብዓዊ አገልግሎት ሱሆን በተለያየ ምክንያትና አደጋ በደም እጦት የሚሞቱ ወገኖቻችንን ደም በመስጠት ህይወት የማዳን ስራ ለመስራት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ይመር ከበደ ከስጦታዎች ሁሉ ዉዱ ስጦታ የሆነውን የሰውን ልጅ ህይወት የሚያድነውን ደም ለመለገስ ፍቃደኛ ሆነው የተገኙ ከ1100 በላይ የሚሆኑ የደንብ ማስከበር አመራሮችና ኦፊሰሮች ከፍተኛ ምስጋና ይገባቸዋል ሱሉ ተናግረዋል ።
በቀጣይም በቋሚነት አባል ሆነን በየሶስት ወሩ ደም በመለገስ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ይመር ከበደ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
በደም ልገሳ መርሐ ግብር የባለስልጣኑ የክፍለ ከተማና የወረዳ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የማዕከል ሰራተኞች፣ከ11 ክፍለ ከተማ እና ከ119 ወረዳዎች በጎ-ፈቃደኛ ደም ለጋሽ ኦፊሰሮች ተሳትፈዋል ።
በመርሀ ግብሩ ባለስልጣኑ በከተማዋ የደንብ መተላለፎች ከመከላከልና ከመቆጣጠር በተጨማሪ በርካታ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሳተፍ የሀገር አለኝታ መሆኑ ተገልጿል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 11- 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር በመተባበር "ደም መስጠት ህይወት መስጠት ነው " በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሐ ግብር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም አከናወነ።
የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በክረምት በጎ ፍቃድ ከዘጠና ቀናት እቅድ አንዱ የሆነውን የደም የመለገስ መርሃ-ግብር አመራሩና ኦፍሰሩ በጋራ በመሆን በራስ ተነሳሽነት ደም ለመስጠት መገኘቱ የህሊና እርካታ የሚሰጥና ደም በመስጠት ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወት ለመታደግ መሆኑ ተናግረዋል።
አክለውም ደም ልገሳ የሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ የሚጠይቅ ታላቅ ሰብዓዊ አገልግሎት ሱሆን በተለያየ ምክንያትና አደጋ በደም እጦት የሚሞቱ ወገኖቻችንን ደም በመስጠት ህይወት የማዳን ስራ ለመስራት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ይመር ከበደ ከስጦታዎች ሁሉ ዉዱ ስጦታ የሆነውን የሰውን ልጅ ህይወት የሚያድነውን ደም ለመለገስ ፍቃደኛ ሆነው የተገኙ ከ1100 በላይ የሚሆኑ የደንብ ማስከበር አመራሮችና ኦፊሰሮች ከፍተኛ ምስጋና ይገባቸዋል ሱሉ ተናግረዋል ።
በቀጣይም በቋሚነት አባል ሆነን በየሶስት ወሩ ደም በመለገስ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ይመር ከበደ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
በደም ልገሳ መርሐ ግብር የባለስልጣኑ የክፍለ ከተማና የወረዳ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የማዕከል ሰራተኞች፣ከ11 ክፍለ ከተማ እና ከ119 ወረዳዎች በጎ-ፈቃደኛ ደም ለጋሽ ኦፊሰሮች ተሳትፈዋል ።
በመርሀ ግብሩ ባለስልጣኑ በከተማዋ የደንብ መተላለፎች ከመከላከልና ከመቆጣጠር በተጨማሪ በርካታ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሳተፍ የሀገር አለኝታ መሆኑ ተገልጿል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍4
504 ዩኒት ደም 3ሰዓት ባልሞላ ጊዜ መለገሱን ተገለፀ
ባስልጣኑ ''ደም በመለገስ ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ ህይወት እንታደግ'' በሚል መሪ ቃል ባደረገው የደም ልገሳ መርሀ-ግብር ከ1100 በላይ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሽ አመራሮቹና ሰራተኞቹ በማሳተፍ ከ504 ዩኒት ደም መለገሱን ብሄራዊ ደም ባንክ ገለፀ።
የደም ልገሳው እጅግ ውጤታማና የተቀናጀ በመሆኑ ስራው መሳካቱ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች ላደረጉት መልካም ተግባር በብሄራዊ ደም ባንክ ተመስግነዋል።
"ደም መስጠት ህይወት መስጠት ነው"
መረጃው፡-የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
ባስልጣኑ ''ደም በመለገስ ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ ህይወት እንታደግ'' በሚል መሪ ቃል ባደረገው የደም ልገሳ መርሀ-ግብር ከ1100 በላይ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሽ አመራሮቹና ሰራተኞቹ በማሳተፍ ከ504 ዩኒት ደም መለገሱን ብሄራዊ ደም ባንክ ገለፀ።
የደም ልገሳው እጅግ ውጤታማና የተቀናጀ በመሆኑ ስራው መሳካቱ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች ላደረጉት መልካም ተግባር በብሄራዊ ደም ባንክ ተመስግነዋል።
"ደም መስጠት ህይወት መስጠት ነው"
መረጃው፡-የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
👍14❤8
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር መርሀ ግብ ተካሄደ።
14- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በእውቀት ሽግግሩ መርሀ ግብር እለቱን በስኬት በማለት ካለቸው ልምድና ተሞክሮ ሰነድ ያቀረቡት የባለስልጣኑ የክትትል ቁጥጥር እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ ባለሙያ አቶ በሀይሉ አበራ የፓራ ሚሊቴሪ ህይወት ላይ ያጠነጠነ ሰነድ ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።
ወታደር ማለት ከብሔር፣ ከሀይማኖት፣ ከዘር እና ከጎሰኝነት አስተሳብ የፀዳ ኢትዮጵያዊነትን ተላብሶ ለሀገር ሉአላዊነት ክብር መስዋእት መሆን ነው ያሉት አቅራቢው ክብር ሰው በመሆን ብቻ የሚሰጥ መሆኑን በወታደራዊ ማስልጠኛ ቆይታ አይቻለሁ።
ለኔ እዚህ ደራጃ ለመድረስ የቤተሰቦቼ ጥብቅ ክትትልና የሞራል ድጋፍ እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና በፓራ ሚሊተሪ የስራ ቆይታየ ከቅርብ ሀላፊዎቼ ብሎም የስራ ባልደረቦቼ ያገኘሁት ልምድና እውቀት ነው በማለት የእውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም በህይወቴ ትልቅ ችግርን በትንሽ ተስፋ ማለፍ እንደሚቻል አይቻለሁ ስለዚህ ችግሮችን ተቋቁሞ ተስፋን በመሰነቅ ነገን አሻግሮ ማየት ያስፈልጋል በማለት ገልፀዋል።
በመጨረሻም ከወታደራዊ ማሰልጠኛ ጀምሮ በስራ ቆይታቸው ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ በሰፊው በማቅረብ ዝግጅታቸውን ቋጭተዋል።
ዘጋባው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
14- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በእውቀት ሽግግሩ መርሀ ግብር እለቱን በስኬት በማለት ካለቸው ልምድና ተሞክሮ ሰነድ ያቀረቡት የባለስልጣኑ የክትትል ቁጥጥር እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ ባለሙያ አቶ በሀይሉ አበራ የፓራ ሚሊቴሪ ህይወት ላይ ያጠነጠነ ሰነድ ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።
ወታደር ማለት ከብሔር፣ ከሀይማኖት፣ ከዘር እና ከጎሰኝነት አስተሳብ የፀዳ ኢትዮጵያዊነትን ተላብሶ ለሀገር ሉአላዊነት ክብር መስዋእት መሆን ነው ያሉት አቅራቢው ክብር ሰው በመሆን ብቻ የሚሰጥ መሆኑን በወታደራዊ ማስልጠኛ ቆይታ አይቻለሁ።
ለኔ እዚህ ደራጃ ለመድረስ የቤተሰቦቼ ጥብቅ ክትትልና የሞራል ድጋፍ እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና በፓራ ሚሊተሪ የስራ ቆይታየ ከቅርብ ሀላፊዎቼ ብሎም የስራ ባልደረቦቼ ያገኘሁት ልምድና እውቀት ነው በማለት የእውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም በህይወቴ ትልቅ ችግርን በትንሽ ተስፋ ማለፍ እንደሚቻል አይቻለሁ ስለዚህ ችግሮችን ተቋቁሞ ተስፋን በመሰነቅ ነገን አሻግሮ ማየት ያስፈልጋል በማለት ገልፀዋል።
በመጨረሻም ከወታደራዊ ማሰልጠኛ ጀምሮ በስራ ቆይታቸው ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ በሰፊው በማቅረብ ዝግጅታቸውን ቋጭተዋል።
ዘጋባው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤6