የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደም ልገሳ እና የፎቶ አውደ ርዕይ ፕሮግራም አካሄደ
04- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ለ3ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕሮገራም እና ዓመታዊ ስራዎች በከፊል የሚያሳይ የፎቶ አውደ ርዕይ ፕሮግራም አካሂደዋል ።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ፣ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፖርቲ ኃላፊ ሙሉጌታ ጉልማ ፣የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ፣ የክ/ከተማው የሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ያሲን መሐመድ ፣ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ ኦፊሰሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው የሚታዩ የደንብ ጥሰቶችንና ህገወጥ ተግባራት በመከላከል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸዉን ስራዎችንም ለህብረተሰቡ ለማሳየት የፎቶ አውደ ርዕይ አዘጋጅቶ ለተመልካች ክፍት ማድረጉ ሊበረታታ የሚገባ ተግባር መሆኑን የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፖርቲ ኃላፊ ሙሉጌታ ጉልማ ተናግረዋል ።
በፕሮግራሙ ንግግር ያደረጉት የኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ የፎቶ አውደ ርዕዩ በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ መደበኛ ስራዎችና ዋና ዋና ተግባራት ፣ የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ተግባራት፣ የቅንጅት ስራዎች እንዲሁም በርካታ ተግባራትን የተካተቱበት ሲሆን ማህበረሰቡ እየተመለከተ ሀሳብና አስተያየት እንዲሰጥበት ዝግጅት መደረጉ ገልጸዋል ።
በእለቱ "ደሜን ለወገኔ " በሚል መሪ ቃል በክ/ከተማው የሚገኙ ሰራተኞችን እና ኦፊሰሮችን በማስተባበር የደም ልገሳ ፕሮግራም በበጀት አመቱ ለ3ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑ ተገልጿል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
04- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ለ3ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕሮገራም እና ዓመታዊ ስራዎች በከፊል የሚያሳይ የፎቶ አውደ ርዕይ ፕሮግራም አካሂደዋል ።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ፣ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፖርቲ ኃላፊ ሙሉጌታ ጉልማ ፣የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ፣ የክ/ከተማው የሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ያሲን መሐመድ ፣ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ ኦፊሰሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው የሚታዩ የደንብ ጥሰቶችንና ህገወጥ ተግባራት በመከላከል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸዉን ስራዎችንም ለህብረተሰቡ ለማሳየት የፎቶ አውደ ርዕይ አዘጋጅቶ ለተመልካች ክፍት ማድረጉ ሊበረታታ የሚገባ ተግባር መሆኑን የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፖርቲ ኃላፊ ሙሉጌታ ጉልማ ተናግረዋል ።
በፕሮግራሙ ንግግር ያደረጉት የኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ የፎቶ አውደ ርዕዩ በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ መደበኛ ስራዎችና ዋና ዋና ተግባራት ፣ የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ተግባራት፣ የቅንጅት ስራዎች እንዲሁም በርካታ ተግባራትን የተካተቱበት ሲሆን ማህበረሰቡ እየተመለከተ ሀሳብና አስተያየት እንዲሰጥበት ዝግጅት መደረጉ ገልጸዋል ።
በእለቱ "ደሜን ለወገኔ " በሚል መሪ ቃል በክ/ከተማው የሚገኙ ሰራተኞችን እና ኦፊሰሮችን በማስተባበር የደም ልገሳ ፕሮግራም በበጀት አመቱ ለ3ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑ ተገልጿል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍2
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የከተማ አስተዳደሩ የ2018 በጀት ዓመት በጀት 350.13 ቢሊየን ብር ለምክር ቤት ቀርቦ ውይይት በማድረግ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል፡፡
ምክር ቤቱ በሁለተኛው ቀን ወሎ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ለ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር በእቅድ መያዙን አቅርበዋል::
ከተመደበው በጀት ውስጥ ለካፒታል በጀት 249.9 ቢሊዮን ብር እና ለመደበኛ ወጪ 100.1 ቢሊዮን ብር በአጠቃላይ 350.13 ቢሊየን ብር ሆኖ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡
ባቀረቡት የበጅት ድልድል የ2018 በጀቱ በዋናነት ለደህነት ቅነሳ፣ ለዘላቂ ልማት፣ የስራ እድል ፈጠራ ለትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ከከተማው ነዋሪ በተለያዩ መንገድ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለሚሰጡ አገልግሎቶች ፣ ለአቅርቦት ድጎማዎችን እንዲሁም ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁጠባን መሰረት ያደረገ ስራ ላይ የሚውል ነው ብለዋል፡፡
ምክር ቤቱ በሁለተኛው ቀን ወሎ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ለ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር በእቅድ መያዙን አቅርበዋል::
ከተመደበው በጀት ውስጥ ለካፒታል በጀት 249.9 ቢሊዮን ብር እና ለመደበኛ ወጪ 100.1 ቢሊዮን ብር በአጠቃላይ 350.13 ቢሊየን ብር ሆኖ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡
ባቀረቡት የበጅት ድልድል የ2018 በጀቱ በዋናነት ለደህነት ቅነሳ፣ ለዘላቂ ልማት፣ የስራ እድል ፈጠራ ለትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ከከተማው ነዋሪ በተለያዩ መንገድ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለሚሰጡ አገልግሎቶች ፣ ለአቅርቦት ድጎማዎችን እንዲሁም ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁጠባን መሰረት ያደረገ ስራ ላይ የሚውል ነው ብለዋል፡፡
❤2
ባለስልጣኑ "በመትከል ማንሰራራት! " በሚል መሪ ቃል በችግኝ ተከላ መረሃ-ግብር አስጀመረ
ሀምሌ 5/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባስልጣን ከፍተኛ አመራሮች፣የለሚ ኩራ ፣የጉለሌ እና የቦሌ ክፍለ ከተማና የየካ ክፍለ ከተማ አመራሮች እና ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በጋር በመሆን የ2017/18 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ‘’በመትከል ማንሰራራት’’ በሚል መሪ ቃል በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ፈረንሳይ ለጋሲዎን አካባቢ በተዘጋጀው ቦታ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰቶችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር ባሻገር የአቅመ ደካማ ቤት በማደስ ፣ ደጋፊ የሌላቸውን ህፃናት በመደገፍ ፣ ደም በመለገስ እና የችግኝ ተከላ በማካሄድ በበጎ ተግባራት በግንባር ቀደም መሳተፋቸው ገልጸዋል።
ሻለቃ ዘሪሁን አያይዘውም የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብሩ ለተከታታይ 3 ቀናት እንደሚቀጥል በመግለፅ በከተማው የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ለማጠናከር እና ከተማዋን ውብ፣ ፅዱ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በማካሄድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጉ ተናግረዋል፡፡
በየካ ክፍለ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ከበደ ባለስልጣኑ ሀገራዊ ተልዕኮን በመቀበል ዘንድሮ የሚተከለውን ችግኝ ለመትከል ወደ ክፍለ ከተማችን በማጣቱ በማመስገን በቀጣይ የፅድቀት መጠኑን እንክባካቤ እንደሚያደርግ ከፍተኛ እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን በአግባቡ እንክብካቤ በማድረግ ከዚህ በፊት ከነበረው በላቀ መንገድ እንዲፀድቅ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ የገለፁት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ናቸው ።
በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ ከ3000/ከሶስት ሺህ/በላይ ችግኞችን የተተከለ ሲሆን የጥላ፣ የውበት እና የፍራፍሬ ዛፎች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
የችግኝ ተካላ መርሃ ግብሩን ያከናወኑት አመራርና ሰራተኞች ችግኙን በመትከል እንደተሳተፉ ሁሉ በቀጣይም በመንከባከብ ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን በመፍጠር ለትውልድ ለማስረከብ አሻራችዎን እንደሚያቆዩ ተናግረዋል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሀምሌ 5/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባስልጣን ከፍተኛ አመራሮች፣የለሚ ኩራ ፣የጉለሌ እና የቦሌ ክፍለ ከተማና የየካ ክፍለ ከተማ አመራሮች እና ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በጋር በመሆን የ2017/18 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ‘’በመትከል ማንሰራራት’’ በሚል መሪ ቃል በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ፈረንሳይ ለጋሲዎን አካባቢ በተዘጋጀው ቦታ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰቶችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር ባሻገር የአቅመ ደካማ ቤት በማደስ ፣ ደጋፊ የሌላቸውን ህፃናት በመደገፍ ፣ ደም በመለገስ እና የችግኝ ተከላ በማካሄድ በበጎ ተግባራት በግንባር ቀደም መሳተፋቸው ገልጸዋል።
ሻለቃ ዘሪሁን አያይዘውም የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብሩ ለተከታታይ 3 ቀናት እንደሚቀጥል በመግለፅ በከተማው የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ለማጠናከር እና ከተማዋን ውብ፣ ፅዱ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በማካሄድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጉ ተናግረዋል፡፡
በየካ ክፍለ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ከበደ ባለስልጣኑ ሀገራዊ ተልዕኮን በመቀበል ዘንድሮ የሚተከለውን ችግኝ ለመትከል ወደ ክፍለ ከተማችን በማጣቱ በማመስገን በቀጣይ የፅድቀት መጠኑን እንክባካቤ እንደሚያደርግ ከፍተኛ እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን በአግባቡ እንክብካቤ በማድረግ ከዚህ በፊት ከነበረው በላቀ መንገድ እንዲፀድቅ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ የገለፁት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ናቸው ።
በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ ከ3000/ከሶስት ሺህ/በላይ ችግኞችን የተተከለ ሲሆን የጥላ፣ የውበት እና የፍራፍሬ ዛፎች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
የችግኝ ተካላ መርሃ ግብሩን ያከናወኑት አመራርና ሰራተኞች ችግኙን በመትከል እንደተሳተፉ ሁሉ በቀጣይም በመንከባከብ ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን በመፍጠር ለትውልድ ለማስረከብ አሻራችዎን እንደሚያቆዩ ተናግረዋል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤5