የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.1K subscribers
1.81K photos
4 videos
1 file
53 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣናኑ የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት አስጀመረ

4/11/2017 ዓ.ም
አ አ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን የቤት እድሳት በ ወረዳ 05 እና የኮልፌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት በወረዳ 06 እንዲሁም የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሂደዋል ።

የቤት እድሳት መርኃ ግብሩን የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የወረዳ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት አስጀምረዋል።

የቤት እድሳቱን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ም/ ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የደንብ ጥሰትን ከመላከል ጎን ለጎን የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን በሰው ተኮር ተግባር የአቅመ ደካማ የቤት እድሳት ስራው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል ፡፡

በተመሳሳይ የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን የችግኝ ተከላ መርሐግብር በወረዳ 10 አካሂዷል ።

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ደንብ ማስከበር ህገወጥነት መከላከል እና ከፀጥታው ጋር የተያያዘ ስራ የሚሰራ ቢሆንም ማህበራዊ ሀላፊነትን ለመወጣት የልማትና ሰው ተኮር ሰራዎች ላይ በመሳተፍ በዛሬው ዕለት የአረንጓዴ አሻራ በማሳረፍ እንዲሁም የቤት እድሳት በማስጀመር ሀላፊነታቸው እየተወጡ እንየደሚገኙ ገልፀዋል።

በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ የ11ዱም ወረዳዎች የደንብ ማስከበር ሀላፊዎችና ኦፊሰሮች እንዲሁም የክ/ከተማው የወረዳ 10 አመራሮች ተገኝተዋል።

መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
👍3