ባለስልጣኑ በ2017 በጀት አመት በቅንጅት ለሰሩ ተቋማት እውቅና ሰጠ
ሐምሌ 03/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት ከባለድርሻ አካላት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም በመገምገም እውቅና በመስጠት በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት ለሚሰሩ ስራዎች የስምምነት ፊርማ ፕሮግራም አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት እቅዶችን በማቀድ በከተማዋ ከሚገኙ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የስምምነት ፊርማ በመፈራረም በቅንጅት አብሮ በመሰራት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያቶች ሰራዎች በመገምገም የተሻለ ስራዎችን ማከናወን መቻሉ ገልፀዋል ።
ተቋሙ ባሳለፈው በጀት ዓመት የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት የተቋም ግንባታ ሰራውን ማጠናከር ፣ የተቋሙን ተግባራት ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ከተማችንን ውብና ጽዱ እንድትሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ከፍተኛ ሰራ መሰራቱ ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮና ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት በከተማችን የሚስተዋሉ ደንብ ጥሰቶች በ69.8% እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን ዋና ሰራ አስኪያጁ ገልፀዋል ።
የአዲስ አበባ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ በከተማችን እየታየ ያለው ፈጣን እድገት፣ የሚሰሩ ፕሮጀክቶችና የተሰሩ የኮሪደር ልማቶች የቅንጅት ስራዎችን በማጠናከር 7/24 በመስራት የተገኙ ውጤቶች መሆናቸው ተናግረዋል ።
አክለውም የደንብ ማስከበር በፊት የነበረው ገጽታ ለማስተካከልና በከተማችን የደንብ ጥሰት የቀነሰባት ለማድረጉ በየጊዜው የሚያከናውነው የቅንጅት ስራዎች ጉልህ ሚና እንዳለቸው በመግለፅ በቀጣይ ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
የደንብ ማስከበር በ2017 በጀት ዓመት ከባለድርሻ አካላት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎች የእቅድ ሰነድ በባለስልጣኑ የስታንዳርድዜሽንና አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል።
በሰነዱ በበጀት ዓመት ውስጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተፈፀሙ ዋና ዋና ተግባራትና የነበሩ ውስንነቶች እና የተወሰዱ መፍትሄዎችን በዝርዝር ቀርበዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ የተቋሙ ባለድርሻ አካላት የቅንጅት ስራዎችን በጋራ ማቀድ እና መገምገም ይበል የሚያሰኝና በቀጣይም ይህን የቅንጅት ተግባር በማጎልበትና በማጠናከር በበጀት ዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በጋራ በርብርብ እንደሚሰሩ አስተያየት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም በ2017 በጀት ዓመት በጋራ አብረው ለሰሩ ባለድርሻ አካላት በየደረጃቸው የእውቅና ሽልማት በማበርከትና በመድረኩ ከተገኙ የባለድርሻ አካላት ጋር በ2018 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የትስስር ሰነድ ተፈራርሟል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 03/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት ከባለድርሻ አካላት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም በመገምገም እውቅና በመስጠት በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት ለሚሰሩ ስራዎች የስምምነት ፊርማ ፕሮግራም አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት እቅዶችን በማቀድ በከተማዋ ከሚገኙ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የስምምነት ፊርማ በመፈራረም በቅንጅት አብሮ በመሰራት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያቶች ሰራዎች በመገምገም የተሻለ ስራዎችን ማከናወን መቻሉ ገልፀዋል ።
ተቋሙ ባሳለፈው በጀት ዓመት የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት የተቋም ግንባታ ሰራውን ማጠናከር ፣ የተቋሙን ተግባራት ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ከተማችንን ውብና ጽዱ እንድትሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ከፍተኛ ሰራ መሰራቱ ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮና ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት በከተማችን የሚስተዋሉ ደንብ ጥሰቶች በ69.8% እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን ዋና ሰራ አስኪያጁ ገልፀዋል ።
የአዲስ አበባ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ በከተማችን እየታየ ያለው ፈጣን እድገት፣ የሚሰሩ ፕሮጀክቶችና የተሰሩ የኮሪደር ልማቶች የቅንጅት ስራዎችን በማጠናከር 7/24 በመስራት የተገኙ ውጤቶች መሆናቸው ተናግረዋል ።
አክለውም የደንብ ማስከበር በፊት የነበረው ገጽታ ለማስተካከልና በከተማችን የደንብ ጥሰት የቀነሰባት ለማድረጉ በየጊዜው የሚያከናውነው የቅንጅት ስራዎች ጉልህ ሚና እንዳለቸው በመግለፅ በቀጣይ ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
የደንብ ማስከበር በ2017 በጀት ዓመት ከባለድርሻ አካላት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎች የእቅድ ሰነድ በባለስልጣኑ የስታንዳርድዜሽንና አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል።
በሰነዱ በበጀት ዓመት ውስጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተፈፀሙ ዋና ዋና ተግባራትና የነበሩ ውስንነቶች እና የተወሰዱ መፍትሄዎችን በዝርዝር ቀርበዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ የተቋሙ ባለድርሻ አካላት የቅንጅት ስራዎችን በጋራ ማቀድ እና መገምገም ይበል የሚያሰኝና በቀጣይም ይህን የቅንጅት ተግባር በማጎልበትና በማጠናከር በበጀት ዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በጋራ በርብርብ እንደሚሰሩ አስተያየት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም በ2017 በጀት ዓመት በጋራ አብረው ለሰሩ ባለድርሻ አካላት በየደረጃቸው የእውቅና ሽልማት በማበርከትና በመድረኩ ከተገኙ የባለድርሻ አካላት ጋር በ2018 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የትስስር ሰነድ ተፈራርሟል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍4❤1
ባለስልጣናኑ የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት አስጀመረ
4/11/2017 ዓ.ም
አ አ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን የቤት እድሳት በ ወረዳ 05 እና የኮልፌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት በወረዳ 06 እንዲሁም የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሂደዋል ።
የቤት እድሳት መርኃ ግብሩን የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የወረዳ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት አስጀምረዋል።
የቤት እድሳቱን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ም/ ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የደንብ ጥሰትን ከመላከል ጎን ለጎን የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን በሰው ተኮር ተግባር የአቅመ ደካማ የቤት እድሳት ስራው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል ፡፡
በተመሳሳይ የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን የችግኝ ተከላ መርሐግብር በወረዳ 10 አካሂዷል ።
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ደንብ ማስከበር ህገወጥነት መከላከል እና ከፀጥታው ጋር የተያያዘ ስራ የሚሰራ ቢሆንም ማህበራዊ ሀላፊነትን ለመወጣት የልማትና ሰው ተኮር ሰራዎች ላይ በመሳተፍ በዛሬው ዕለት የአረንጓዴ አሻራ በማሳረፍ እንዲሁም የቤት እድሳት በማስጀመር ሀላፊነታቸው እየተወጡ እንየደሚገኙ ገልፀዋል።
በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ የ11ዱም ወረዳዎች የደንብ ማስከበር ሀላፊዎችና ኦፊሰሮች እንዲሁም የክ/ከተማው የወረዳ 10 አመራሮች ተገኝተዋል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
4/11/2017 ዓ.ም
አ አ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን የቤት እድሳት በ ወረዳ 05 እና የኮልፌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት በወረዳ 06 እንዲሁም የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሂደዋል ።
የቤት እድሳት መርኃ ግብሩን የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የወረዳ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት አስጀምረዋል።
የቤት እድሳቱን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ም/ ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የደንብ ጥሰትን ከመላከል ጎን ለጎን የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን በሰው ተኮር ተግባር የአቅመ ደካማ የቤት እድሳት ስራው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል ፡፡
በተመሳሳይ የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት የ90 ቀን እቅድ አካል የሆነውን የችግኝ ተከላ መርሐግብር በወረዳ 10 አካሂዷል ።
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ደንብ ማስከበር ህገወጥነት መከላከል እና ከፀጥታው ጋር የተያያዘ ስራ የሚሰራ ቢሆንም ማህበራዊ ሀላፊነትን ለመወጣት የልማትና ሰው ተኮር ሰራዎች ላይ በመሳተፍ በዛሬው ዕለት የአረንጓዴ አሻራ በማሳረፍ እንዲሁም የቤት እድሳት በማስጀመር ሀላፊነታቸው እየተወጡ እንየደሚገኙ ገልፀዋል።
በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ የ11ዱም ወረዳዎች የደንብ ማስከበር ሀላፊዎችና ኦፊሰሮች እንዲሁም የክ/ከተማው የወረዳ 10 አመራሮች ተገኝተዋል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
👍3