ለኢትዮጵያ ብልፅግና የመንግስት ሰራተኛው ተሳትፎ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
28/9/2017
**የአዲ ስአበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "ብቃት ያለው ሲቪል ሰርቪስ ለኢትዮጵያ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ስልጠና ከማዕከል አመራርና ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረገ።
የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊና ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው መንግስት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማድረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ውይይቶቹ መንግስትና ህዝብን ለማቀራረብ አስፈላጊ በመሆናቸውና ከውይይት የሚጨመቁ ሀሳቦች ፓሊሲዎችን ስትራቴጂዎች ሊቀይሩ እንደሚችሉ ገልፀዋል።
የመወያያ ሰነዱ በይዘት ሀገራዊ ለውጥ ያስመዘገባቸው ውጤቶችና የሲቪል ሰርቫንቱ ሚና፣ የሲቪል ሰርቪስ አሁናዊ ሀኔታ፣ የአመራር ሁኔታ፣ የመንግስት ሰራተኛ ሁኔታ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሲቪል ሰርቫንት ሪፎርም እና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ የመሳሰሉትን ዋና ዋና ይዘቶች ለማየት ተችሏል።
በሰነዱ በአዲስ አበባ ውስጥ ከ70ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞች ሲኖሩ እነዚህ ሰራተኞች አሁን ላለው ለውጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን በተለይም በትምህርት ፣ በጤና ፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣ በኮሪደር ልማት በመሳሰሉት ከተማ አቀፍ ስራዎች ሚናቸው ጉልህ መሆኑ ተገልጿል።
በውይይቱ የኑሮ ውድነት ላይ ስርነቀል ስራ መሰራት እንደሚገባ ፣ገበያ ማረጋጋት ምርቶችን ቀጥታ ከገበሬው የሚያገኝበት መንገዶች ቢመቻች፣ የቤት አቅርቦት ለመንግስት ሰራተኛው ቢታሰብበት፣ የትምህርት እድሎች ሰፋ ባለ መልኩ ቢዘጋጅ እና የሰራተኞች የፐብሊክ ትራንስፖርት እጥረት የመሳሰሉት ጉዳዮች በውይይቱ ተነስተዋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ሰራተኛው ከብልሹ አሰራር ችግር በመውጣት ህብረተሰብን ወጥ በሆነ መንገድ ማገልገል እንደሚገባ አና ለመንግሥት ሰራተኛውም ምቹ ሁኔታዎች ሊፈጠረለት እንደሚገባ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ከተማዋን በማዘመን ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝና ከላይ የተነሱ ጥያቄዎችን በየደረጃው ለመፍታት ሰፊ እርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በማጠቃለያ ንግግራቸው ላይ አመላክተዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
28/9/2017
**የአዲ ስአበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "ብቃት ያለው ሲቪል ሰርቪስ ለኢትዮጵያ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ስልጠና ከማዕከል አመራርና ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረገ።
የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊና ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው መንግስት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማድረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ውይይቶቹ መንግስትና ህዝብን ለማቀራረብ አስፈላጊ በመሆናቸውና ከውይይት የሚጨመቁ ሀሳቦች ፓሊሲዎችን ስትራቴጂዎች ሊቀይሩ እንደሚችሉ ገልፀዋል።
የመወያያ ሰነዱ በይዘት ሀገራዊ ለውጥ ያስመዘገባቸው ውጤቶችና የሲቪል ሰርቫንቱ ሚና፣ የሲቪል ሰርቪስ አሁናዊ ሀኔታ፣ የአመራር ሁኔታ፣ የመንግስት ሰራተኛ ሁኔታ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሲቪል ሰርቫንት ሪፎርም እና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ የመሳሰሉትን ዋና ዋና ይዘቶች ለማየት ተችሏል።
በሰነዱ በአዲስ አበባ ውስጥ ከ70ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞች ሲኖሩ እነዚህ ሰራተኞች አሁን ላለው ለውጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን በተለይም በትምህርት ፣ በጤና ፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣ በኮሪደር ልማት በመሳሰሉት ከተማ አቀፍ ስራዎች ሚናቸው ጉልህ መሆኑ ተገልጿል።
በውይይቱ የኑሮ ውድነት ላይ ስርነቀል ስራ መሰራት እንደሚገባ ፣ገበያ ማረጋጋት ምርቶችን ቀጥታ ከገበሬው የሚያገኝበት መንገዶች ቢመቻች፣ የቤት አቅርቦት ለመንግስት ሰራተኛው ቢታሰብበት፣ የትምህርት እድሎች ሰፋ ባለ መልኩ ቢዘጋጅ እና የሰራተኞች የፐብሊክ ትራንስፖርት እጥረት የመሳሰሉት ጉዳዮች በውይይቱ ተነስተዋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ሰራተኛው ከብልሹ አሰራር ችግር በመውጣት ህብረተሰብን ወጥ በሆነ መንገድ ማገልገል እንደሚገባ አና ለመንግሥት ሰራተኛውም ምቹ ሁኔታዎች ሊፈጠረለት እንደሚገባ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ከተማዋን በማዘመን ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝና ከላይ የተነሱ ጥያቄዎችን በየደረጃው ለመፍታት ሰፊ እርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በማጠቃለያ ንግግራቸው ላይ አመላክተዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
❤5
እንኳን ለ1446ኛው አረፋ/ለዒድ አል-አድሐ/ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!!!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለዒድ አል-አድሐ/አረፋ/ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! እያለ ባለስልጣኑና በራሴ ስም መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።
የአረፉ /ኢድ አል-አድሐ/ በዓል የሰላም ፣የጤና ፣የፍቅር እና የመረዳዳት በዓል እንዲሆንልን እየተመኘሁ ህዝበ ሙስሊሙ በበዓሉ ወቅት በአብሮነትና በመተሳሰብ ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ በማጋራት ያለውን በማካፈል በአሉን በማክበር በተለመደው አብሮነት ስሜት እንዲያከብር አደራ እላለሁ ።
ባለስልጣኑ በአሉን አስመልክቶና ማንኛውም በከተማዋ የሚስተዋለውን የደንብ መተላለፍና ህገ-ወጥነትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚያደርገው ስራ ላይ ህዝበ ሙስሊሙ እንደተለመደው በንቃት እንዲሳተፍና በአክብሮት እጠይቃለሁ።
አዲስ አበባ ከተማችንን የደንብ መተላለፍ የማይስተዋልባት፤ ለነዋሪዎቿና እንግዶቿ ምቹ እንድትሆን ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ በመስጠት የበኩሎን እንዲወጡ በዚህ አጋጣሚ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።
በራሴ እና በባለስልጣን መስሪያ ቤት ስም መልካም በዓል እንዲሆንልን ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ።
ዒድ ሙባረክ!
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለዒድ አል-አድሐ/አረፋ/ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! እያለ ባለስልጣኑና በራሴ ስም መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።
የአረፉ /ኢድ አል-አድሐ/ በዓል የሰላም ፣የጤና ፣የፍቅር እና የመረዳዳት በዓል እንዲሆንልን እየተመኘሁ ህዝበ ሙስሊሙ በበዓሉ ወቅት በአብሮነትና በመተሳሰብ ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ በማጋራት ያለውን በማካፈል በአሉን በማክበር በተለመደው አብሮነት ስሜት እንዲያከብር አደራ እላለሁ ።
ባለስልጣኑ በአሉን አስመልክቶና ማንኛውም በከተማዋ የሚስተዋለውን የደንብ መተላለፍና ህገ-ወጥነትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚያደርገው ስራ ላይ ህዝበ ሙስሊሙ እንደተለመደው በንቃት እንዲሳተፍና በአክብሮት እጠይቃለሁ።
አዲስ አበባ ከተማችንን የደንብ መተላለፍ የማይስተዋልባት፤ ለነዋሪዎቿና እንግዶቿ ምቹ እንድትሆን ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ በመስጠት የበኩሎን እንዲወጡ በዚህ አጋጣሚ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።
በራሴ እና በባለስልጣን መስሪያ ቤት ስም መልካም በዓል እንዲሆንልን ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ።
ዒድ ሙባረክ!
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ!
👍4❤1
ፕረስ ሪልዝ
ባለስልጣኑ የስድስተኛ ዙር ፖራሚሊተሪ ሰልጣኝ ኦፊሰርሮች በነገዉ ዕለት በደማቅ ሁኔታ ሊያስመርቅ ነው
29 - 09 - 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለሁለት ወራት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በንድፈ ሀሳብና በወታደራዊ ስልጠና ሲያሰለጥናቸው የቆየዉን 2074(ሁለት ሺ ሰባ አራት) ምልምል የፖራ -ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በነገዉ እለት በደማቅ ሁኔታ ሊያስመርቅ ነው።
የምርቃት ፕሮግራሙ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ኮልፌ በሚገኘው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ የሚካሄድ ይሆናል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ባለስልጣኑ የስድስተኛ ዙር ፖራሚሊተሪ ሰልጣኝ ኦፊሰርሮች በነገዉ ዕለት በደማቅ ሁኔታ ሊያስመርቅ ነው
29 - 09 - 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለሁለት ወራት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በንድፈ ሀሳብና በወታደራዊ ስልጠና ሲያሰለጥናቸው የቆየዉን 2074(ሁለት ሺ ሰባ አራት) ምልምል የፖራ -ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በነገዉ እለት በደማቅ ሁኔታ ሊያስመርቅ ነው።
የምርቃት ፕሮግራሙ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ኮልፌ በሚገኘው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ የሚካሄድ ይሆናል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
❤14👍4
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለሁለት ወራት ያሰለጠናቸው ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን አሰመረቀ
30/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከ2ሺህ በላይ የ6ተኛ ዙር ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የካቤኔ አባላላታቸው በተገኙበት በድምቀት አስመረቀ።
ሰልጣኞቹ ላለፉት ሁለት ወራት በንድፈ-ሃሳብ እና በወታደራዊ ስልጠና በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ አፓስቶ ካምፓስ ሰልጥነው በብቃት ማጠናቀቃቸውን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የዛሬ ተመራቂዎች የትምህርት ደረጃቸው ዲግሪና ከዚያ በላይ የሆኑ 2074 ኦፊሰሮች መሆናቸውን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አሳውቀዋል።
ሰልጣኞቹ ለ192 ሰዓታት የንድፈ ሃሳብ ስልጠና እና ለ239 ሰዓታት የወታደራዊ ስልጠና በማካሄድ በድምሩ ለ431 ሰዓታት 2074 ተመራቂ ኦፊሰሮች ስልጠናው በሚፈለገው ዲስፕሊን መሠረት አሰልጥኖ ለምረቃ ብቁ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዘዳንት መስፍን አበበ አስታውቀዋል።
ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙን እያላቀ ከተማ አስተዳደሩ በሚፈልገው ልክ ተልዕኮውን እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብር ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ሲሆን ትልቅ መሰጠትና ብቃት ለሚጠይቀው የመስክ ስራ እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አሳስበዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከተማችን አዲስ አበባ እያስመዘገበች ባለችው ሁሉን አቀፍ ልማት ለነዋሪዎቿ ምቹ እየሆነች ነው።
ይህንንም ልማት በህግና ደንብ መመራት እንዲችል በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂና በሎጀስቲክ በመደገፍ ላይ እንገኛለን።
ከተማዋ በቀን ብቻ ሳይሆን በምሽትም ጭምር እንቅስቃሴዋ ያልተገደበ እንዲሆን ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሩን በሶስት ሺፍት በማሰማራት ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል።
በህዝብ ዘንድ ክብር የሚጎናፀፍ አገልግሎት ለመስጠት በዲሲፕሊን ታንፃችሁ ህዝባችሁን በማሳተፍና በማስተባበር ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አደራ እያልኩ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
30/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከ2ሺህ በላይ የ6ተኛ ዙር ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የካቤኔ አባላላታቸው በተገኙበት በድምቀት አስመረቀ።
ሰልጣኞቹ ላለፉት ሁለት ወራት በንድፈ-ሃሳብ እና በወታደራዊ ስልጠና በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ አፓስቶ ካምፓስ ሰልጥነው በብቃት ማጠናቀቃቸውን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የዛሬ ተመራቂዎች የትምህርት ደረጃቸው ዲግሪና ከዚያ በላይ የሆኑ 2074 ኦፊሰሮች መሆናቸውን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አሳውቀዋል።
ሰልጣኞቹ ለ192 ሰዓታት የንድፈ ሃሳብ ስልጠና እና ለ239 ሰዓታት የወታደራዊ ስልጠና በማካሄድ በድምሩ ለ431 ሰዓታት 2074 ተመራቂ ኦፊሰሮች ስልጠናው በሚፈለገው ዲስፕሊን መሠረት አሰልጥኖ ለምረቃ ብቁ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዘዳንት መስፍን አበበ አስታውቀዋል።
ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙን እያላቀ ከተማ አስተዳደሩ በሚፈልገው ልክ ተልዕኮውን እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብር ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ሲሆን ትልቅ መሰጠትና ብቃት ለሚጠይቀው የመስክ ስራ እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አሳስበዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከተማችን አዲስ አበባ እያስመዘገበች ባለችው ሁሉን አቀፍ ልማት ለነዋሪዎቿ ምቹ እየሆነች ነው።
ይህንንም ልማት በህግና ደንብ መመራት እንዲችል በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂና በሎጀስቲክ በመደገፍ ላይ እንገኛለን።
ከተማዋ በቀን ብቻ ሳይሆን በምሽትም ጭምር እንቅስቃሴዋ ያልተገደበ እንዲሆን ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሩን በሶስት ሺፍት በማሰማራት ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል።
በህዝብ ዘንድ ክብር የሚጎናፀፍ አገልግሎት ለመስጠት በዲሲፕሊን ታንፃችሁ ህዝባችሁን በማሳተፍና በማስተባበር ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አደራ እያልኩ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍10❤3