የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.09K subscribers
1.74K photos
4 videos
1 file
52 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የባለስልጣኑ የ6ኛ ዙር ዕጩ ፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና በተመለከተ የሽኝት እና የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ

26/09/2017 ዓ.ም
ይርጋለም/አፖስቶ/

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ ለሁለት ወራት በወታደራዊ እና ንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎች ሲያሰለጥናቸው የቆየው እጩ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የመሸኛ ዝግጅት እና በስልጠናው አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና እና የእውቅና መርሀ-ግብር ተካሂድዋል።

በምስጋና ዝግጅቱ ላይ የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በየደረጃው በመገኘት በስልጠናው ሂደት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ሰርተፍኬት አበርክተዋል።

በዝግጅቱ ላይ የባለስልጣኑ ምክትል ስ/አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሀገሪቱ ህግና ደንብ እንዲከበር የበኩልን አስተዋጽኦ በመወጣት ላይ እንደሚገኝ እና ለዚህም ማሳያ በየዙሩ ሰልጣኞችን በብቃት እያሰለጠነ እንደሚገኝ በመግለጽ በ6ኛ ዙር የኦፊሰሮች ስልጠና ላይም ይኸው ተግባር መቀጠሉን በማንሳት ለሰልጣኝ ኦፊሰሮቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

በፕሮግራሙ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ሰልጣኝ ኦፊሰሮቹ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት በተግባር በማዋል በቀጣይ ብቁ እና ሀላፊነቱን የሚወጣ ኦፊሰር በመሆን ተቋሙ የሚጥልባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ መልእክት አስተላልፈዋል።

በእለቱም በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ጊቢ ውስጥ በ6ኛ ዙር ዕጩ ፖራ-ሚሊተሪ ሰልጣኝ ኦፊሰሮች የተገነባ መዝናኛ ቤት ተመርቆ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አስረክቧል።

በሳምራዊት ዘሪሁን
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ
👍5
የ6ተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ለምረቃ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ ገቡ።

27/09/ 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ6ተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በአዲስ አበባ ኮልፌ ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ሲደርሱ የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አቀባበል ተደረገላቸው።

የ6ተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርስቲ አፓስቶ ካምፓስ ሲሰጥ የቆየዉን የሁለት ወር የወታደራዊና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና አጠናቀው ለምርቃት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ በሰላም መድረሳቸውን የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።

አክለውም ስልጠናው ለሁለት ወራት የተሰጠ ሲሆን እጩ ኦፊሰሮችም ቀን ከሌሊት በመትጋት ለምርቃ ብቁ መሆናቸውን አሳውቀዋል።

በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩኒቨርስቲ/በአፖስቶ ካምፖስ/ ሲሰጥ የቆየው የ6ተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ ሰልጣኞችም በንድፈ-ኃሳብና በወታደራዊ ስልጠናዎች ምዘናዎችን በብቃት አጠናቀው ለተልዕኮ ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት ባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ እና ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ናቸው።

ከስልጠናው በኃላ ለስራው በቂ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የንድፈ ሀሳብና የወታደራዊ ፈተናዎችን ወስደው በብቃት በማጠናቀቅ

በትላንትናውም ዕለት የባለስልጣኑና የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩኒቨርስቲው መምህራኖች ፣ ወታደራዊ አሰልጣኞች እንዲሁም የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት የስልጠናው ማጠቃለያ ደማቅ የሽኝት ፕሮግራም መደረጉን አቶ ንጋቱ አሳውቀዋል።

ኦፊሰሩ ባገኘው እውቀትና በተሰጠው ስልጠና መሰረት በቀጣይ በከተማችን ላይ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰቶችን በመከላከል ከተማችን እንደ ስሟ አዲስ አበባ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን የስነ-ልቦና ዝግጅት አድርጎ እንዲሰማራ አቅጣጫ የሰጡት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ናቸው።

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍51
የህዝብና የመንግስት መሬት በመውረር ግንባታ የገነባ ባለሀብት በቁጥጥር ስር በማዋል በግንባታው እርምጃ ተወሰደ

ግንቦት 27/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማሰከበር ባለስልጣን ‎በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በወረዳ 06 በ125 ካሬ መሬት ወረራ ያከናወነን ግለሰብ በቁጥጥር ስር በማዋል በአዋጅ 721/2004 መሰረት ተጠያቂ በማድረግ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ መደረጉ ተገለፀ። የወረዳዉ ደንብ ጽህፈት ቤት ሀላፈ አስታዉቋል።

‎በግለሰቡ የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ከወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ፣ ከወረዳዉ መሬት አስተዳደር ጽህፈት ቤት እንዲሁም ከፖሊስ ጋር በመተባበር በተገነባው ግንባታ ላይ እርምጃ የተወሰደ መሆኑን የደንብ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ኢ/ር ደሳለኝ ሌንጮ ገልፀዋል።

ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ የመንግስትና የህዝብ መሬት በህገ-ወጥ መንገድ በመውረር በበሚገነባ ግንባታ የህዝብና የመንግስት ሀብት ከብክነት እንዲጠብቁ መልዕክቱን አስተላልፏል።
👍104👎2