የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.09K subscribers
1.73K photos
4 videos
1 file
52 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ሕብረተሰቡን በታማኝነት ማገልገል እንደሚገባ ተገለፀ።

22/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአቃቂ ቃሊቲ፣ ኮልፌ ቀራኒዮና ንፋስ ስልክ ላፍቶና አራዳ ክፍለ ከተማ አመራርና ኦፊሰሮች ጋር በስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የተመለከተ ግምገማዊ ስልጠና መድረክ አካሄደ።

በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራና ዘርፍ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

"የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የኦፊሰሩ ሚና" በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።

ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት በሁሉም ረገድ እየዘመነች ያለች ከተማን ደንብ መተላለፍ በአግባቡ ለመከላከል እና ህብረተሰቡን በታማኝነት ለማገልገል ከፍተኛ ቁርጠኝነት የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሌም በስነ-ልቦና ዝግጁ በመሆን ተልዕኳችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

በቅርቡ አስመርቀን ወደ ስራ የምናሰማራቸውን የ6ተኛ ዙር ኦፊሰሮቻችንን ጨምረን የሰው ኃይል አቅማችንን የበለጠ በማጠናከር ሕገ-ወጥነትንና የደንብ መተላለፍን በአስተማማኝ መልኩ የምንከላከል ይሆናል ብለዋል።

ሁሉም ኦፊሰር በተመደበበት ቀጠና ላይ በሰዓቱ በመገኝት ከስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራር በፀዳ መልኩ ተልእኮውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

በትላንትናው ዕለት ከተቀሩት ክፍለ ከተማ ኦፊሰሮችና አመራሮች ጋር ውጤታማ ውይይት መካሄዱ ይታወሳል።

መረጃው ፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
2👍1
ባለስልጣኑ ለ3 ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ

22/09 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ለማዕከል እና ለክፍለ ከተማ ሲቪለሸ ሠራተኞች በአንደኛና በሁለተኛ ዙር በአጠቃላይ ለ3 ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የአቅም ግንባታ ስልጠና አጠናቀቀ።

ስልጠናው በአሰልጣኝ ቢንያም አብረኃ በጊዜ አጠቃቀም፣ ውጤታማ የቡድን ትብብር ችሎታ እና የራስ ተነሳሺነት፣ እራስን ማስተዳደር እና ሌሎች ርዕሶች ላይ በምዘና የታጀበ ውጤታማ ስልጠና ተሰጥቷል።

በስልጠናውም ላይ ተሳታፊዎቹ የሰጡት አስተያየት በእውቀት፣ በአመለካከትና በክህሎታችን ላይ ስር ነቀል የሆነ ለውጥ የሚያመጣ እና ያገኘነው ስልጠናም በፈተና ጭምር የተረጋገጠ በመሆኑ ውጤታማ ነበር ሲሉ ተደምጠዋል።

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ኃላፊና ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ተገኝተዋል።

አቶ ንጋቱ እንዳሉት ተቋሙ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የአቅም ግንባታ ስራ ላይ እየሠራ እንደሚገኝና በእውቀት በአስተሳሰብና ክህሎት የበቃ ባለሙያ ለተቋም ለውጥ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ በቀጣይም መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

ሰልጣኞችም ተቋሙ ከፍተኛ ትኩረት በማድረግ ያቀረበውን ስልጠና ወደ ተግባር በመለወጥ በአፈፃፀማችን ላይ የሚታይ ተጨባጭ ለውጥ በማስመዝገብ ለህብረተሰባችን የተሻለ አገልግሎት ልንሰጥ ይገባል ብለዋል።

በዚህ ቴክኖሎጂ በዘመነበት ክፍለ ዘመን ላይ እንደመገኘታች መጠን በተለያዩ የኦን ላይን ኮሮሶች ጭምር እራሳችንን በማብቃት በሁሉም ዘርፍ ተወዳዳሪና ብቁ ባለሙያ ልንሆን ይገባል፤ በማለት መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍3
የከተማዋ ነዋሪዎች ከደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራትና ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ

ግንቦት 23/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 ዓ.ም የ10 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙ ከከተማው ነዋሪዎች ጋር የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ጽ/ቤት ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ውይይት አካሄደ።

የመድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት በባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የከተማችን ሰላምና ልማት ወዳድ ህዝብረተሰብ በማሳተፍ ከተማችን የደንብ መተላለፎች የቀነሰባትና ለነዋሪዎቿና ለእንግዶቿ ምቹ እንድትሆን በርካታ ውጤታማ ስራዎች ማከናወናቸው ተናግረዋል።

ዋና ስራ አስኪያጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች በመጠበቅ እንዲሁም በከተማወ የአደባባይ በዓላት በሰላም እንዲከበሩ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ገልፀዋል።

በመድረኩ የባለስልጣን የ2017 ዓ.ም የ10 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የባለስልጣኑ የዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በኮሎኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል።

በእለቱ የወንዞች ዳርቻ ልማት ለመጠበቅ የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 በተመለከተ ዓላማዎቹ፣ የወጡ ዝርዝር ቅጣቶችና መደረግ ያለበት የመፍትሄ አቅጣጫዎች በግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ በወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በሰነድ በማቅረብ ግንዛቤ ተፈጥሯል።

የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በመድረኩ የደንብ ባለስልጣን ቀድሞ ከነበረበት አሠራሩና አደረጃጀቱ በማሻሻል አሁን ላይ እየሰራቸው ያሉትን ውጤታማ ስራዎች የልማቱ ባለቤት የሆነው ህብረተሰብ ምስክርነት የተመሠከረበት መድረክ መሆኑን ገልፀዎል።

አክለውም ህብረተሰቡ አሁነሰ ላይ ያለውን እገዛ በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክት አስተላልፈዋል።

የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በበኩላቸው ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት በመስራታችን ለውጦች መጥተዋል፤ ይህንንም በትልልቅ መድርክ ላይ ከነዋሪው ህብረተሰብ በሚሰጡ አስተያየት ማረጋገጡ አመላክተዋል።

ምክትል ስራ አስኪያጁ ወደፊትም ከናንተ ጋር ስራዎችን አጠናክረው በመቀጠል ባለስልጣኑን ከፍ ወዳለ ደረጃ በማድረስ ከተማችን ከህገወጥ እናፀዳለን ብለዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከጊዜ ወደጊዜ እራሱን እያጠናከረና አሰራሩን እያሻሻለ በመምጣቱ የከተማ አስተዳደሩና የማህበረሰቡ አለኝታ መሆኑ መቻሉ ገልፀዋል።

ተሳታፊዋቹ ለኦፊሰሮች ቀንና ሌሊት በሁሉም የልማት፣የፀጥታና በጎ-ተግባራት ላይ እየተሳተፉ በመሆኑ ልዩ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ገልፀዋል።

የከተማው ነዋሪዎች አዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሚያከናውናቸው ማንኛውም ተግባራት በሚያስፈልገው ሁሉ አብሮ ለመስራትና ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን መድረኩን ሲመሩት በነበሩት ከፍተኛ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሮክቶሬት ነው።
👍31😢1