ህገ-ወጥ እርድ በማከናወን ስጋ ለማከፋፈል የሞከረን ግለሰብ በቁጥጥር በማዎል 16 የቁም እንስሳና 15 ሺህ ብር መቀጣቱ ተገለፀ
ግንቦት 20/2017ዓ/ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 በመኖሪያ ግቢ ውስጥ ህገ-ወጥ እርድ በማከናወን ስጋ በማከፋፈል የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር በማዎል 16 የቁም እንስሳቶች በመውረስ 15 ሺህ ብር መቀጣቱ ገለፀ።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 9 ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሂርጴ ጅፋራ ከዚህ በፊት በወረዳው ለግለሰብና ለተቋም ሰፊ ግንዛቤ መፈጠሩ በመግለጽ በዛሬው ዕለት ከጧቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ከህብረተሰቡ በተገኘው ጥቆማ መሰረት በተደረገ ክትትል በህብረተሰባችን ጤና ለማስጠበቅና የአካባቢ ውበት ለማስጠበቅ ሲባል በደንቡ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዎል።
በቦታው የተገኘው የታረዱ ከ20 በላይ የፍየልና የበግ ስጋ ለቄራዎች ድርጅት እንዲወገድ ማስረከባቸው የገለጹ ሲሆን መረጃው ለሰጡ የህብረለሰብ ክፍሎችና ኦፕሬሽኑ ለሰሩ ኦፊሰሮች ምስጋና አቅርበዋል።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ የመንግስትና የህዝብ ገቢ በማሳጣት በህብረተሰቡ የጤና ችግርና የአካባቢ የውበት የሚያበላሽ መሆኑ በመረዳት ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 በመጠቆምና ሀላፊነቱ እንዲወጣ መልዕክቱን አስተላልፏል ፡፡
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ግንቦት 20/2017ዓ/ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 በመኖሪያ ግቢ ውስጥ ህገ-ወጥ እርድ በማከናወን ስጋ በማከፋፈል የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር በማዎል 16 የቁም እንስሳቶች በመውረስ 15 ሺህ ብር መቀጣቱ ገለፀ።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 9 ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሂርጴ ጅፋራ ከዚህ በፊት በወረዳው ለግለሰብና ለተቋም ሰፊ ግንዛቤ መፈጠሩ በመግለጽ በዛሬው ዕለት ከጧቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ከህብረተሰቡ በተገኘው ጥቆማ መሰረት በተደረገ ክትትል በህብረተሰባችን ጤና ለማስጠበቅና የአካባቢ ውበት ለማስጠበቅ ሲባል በደንቡ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዎል።
በቦታው የተገኘው የታረዱ ከ20 በላይ የፍየልና የበግ ስጋ ለቄራዎች ድርጅት እንዲወገድ ማስረከባቸው የገለጹ ሲሆን መረጃው ለሰጡ የህብረለሰብ ክፍሎችና ኦፕሬሽኑ ለሰሩ ኦፊሰሮች ምስጋና አቅርበዋል።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ የመንግስትና የህዝብ ገቢ በማሳጣት በህብረተሰቡ የጤና ችግርና የአካባቢ የውበት የሚያበላሽ መሆኑ በመረዳት ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 በመጠቆምና ሀላፊነቱ እንዲወጣ መልዕክቱን አስተላልፏል ፡፡
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍3🖕1
የስነ-ምግባር ችግሮችና ብልሹ አሰራርን መከላከልና መፀየፍ እንደሚገባ ተገለፀ
20 - 09 - 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት የባለስልጣኑ እና የክ/ከተማ አመራሮች በተገኙበት ከ119 ወረዳዎች ሽፍት አስተባባሪዎች ጋር ግምገማዊ የስልጠና መድረክ ተካሄደ ።
በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ራሱን በቴክኖሎጂ በማዘመን፣ የገጽታ ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር ፣ ብልሹ አሰራርን በመታገል ፣ የኦፊሰሩን ሙያዊ አቅም በማጠናከርና አዲስ የፖራ ሚሊተሪ ኃይል መልምሎ በማሰልጠን ከተማችን ከደንብ ጥሰት የጸዳች ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በማከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል ።
አክለውም ብልሹ አሰራር ሌብነት እንደ ሀገር ፣ ከተማ እና ለተቋማችን ገጽታ ግንባታ ላይ የሚያመጣውን ተጽዕኖ በመገንዘብ ሁሉም አካል ሊከላከለውና ሊጸየፈው እንደሚገባ ገልጸዋል ።
የስነ-ምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል ለሽፍት አስተባባሪዎች የተዘጋጀው የስልጣንና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
ሽፍት አስተባባሪዎች ያለውን የስራ ጥንካሬ በማስቀጠል እና አንዳንድ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ክፍተቶችን በማስተካከልና በማሻሻል በቀጣይ ስልጠናውን ጨርሰው ወደ ስራ የሚቀላቀለውን የፖራ ሚሊተሪ ኃይል ለመቀበልና ከብልሹ አስራር የጸዳ ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን ዝግጁ መሆን እንደሚገባ ተገልጿል ።
የመድረኩ ተሳታፊዎች ከአመራሩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣትና ብልሹ አሰራርን ለመታገል በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አስቀምጠው መድረኩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
20 - 09 - 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት የባለስልጣኑ እና የክ/ከተማ አመራሮች በተገኙበት ከ119 ወረዳዎች ሽፍት አስተባባሪዎች ጋር ግምገማዊ የስልጠና መድረክ ተካሄደ ።
በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ራሱን በቴክኖሎጂ በማዘመን፣ የገጽታ ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር ፣ ብልሹ አሰራርን በመታገል ፣ የኦፊሰሩን ሙያዊ አቅም በማጠናከርና አዲስ የፖራ ሚሊተሪ ኃይል መልምሎ በማሰልጠን ከተማችን ከደንብ ጥሰት የጸዳች ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በማከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል ።
አክለውም ብልሹ አሰራር ሌብነት እንደ ሀገር ፣ ከተማ እና ለተቋማችን ገጽታ ግንባታ ላይ የሚያመጣውን ተጽዕኖ በመገንዘብ ሁሉም አካል ሊከላከለውና ሊጸየፈው እንደሚገባ ገልጸዋል ።
የስነ-ምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል ለሽፍት አስተባባሪዎች የተዘጋጀው የስልጣንና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
ሽፍት አስተባባሪዎች ያለውን የስራ ጥንካሬ በማስቀጠል እና አንዳንድ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ክፍተቶችን በማስተካከልና በማሻሻል በቀጣይ ስልጠናውን ጨርሰው ወደ ስራ የሚቀላቀለውን የፖራ ሚሊተሪ ኃይል ለመቀበልና ከብልሹ አስራር የጸዳ ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን ዝግጁ መሆን እንደሚገባ ተገልጿል ።
የመድረኩ ተሳታፊዎች ከአመራሩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣትና ብልሹ አሰራርን ለመታገል በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አስቀምጠው መድረኩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍2
የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ጀመረ ።
20 - 09 - 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ለማዕከል ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች ፣ ባለሙያዎች እና የክ/ከተማ አስተባባሪዎችና ሲቪል ሰራተኞች ሁለተኛ ዙር ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል ።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና በጊዜ አጠቃቀም ፣ውጤታማ የቡድን የትብብር ችሎታ እና የራስ ተነሳሺነት ወይም እራስን ማስተዳደር በሚሉ ርዕሶች ላይ የሚሰጥ ይሆናል ።
እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሰልጣኞቹ ላይ የአመለካከትና የዕውቀት ዕድገት እንደሚያመጣ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ገልጸዋል ።
ስልጠናው ለምንሰራው ስራ እና ለግል ህይወታችን ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ በንቃትና ትኩረት በመስጠት መከታተል እንደሚገባ አሳስበዋል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
20 - 09 - 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ለማዕከል ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች ፣ ባለሙያዎች እና የክ/ከተማ አስተባባሪዎችና ሲቪል ሰራተኞች ሁለተኛ ዙር ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል ።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና በጊዜ አጠቃቀም ፣ውጤታማ የቡድን የትብብር ችሎታ እና የራስ ተነሳሺነት ወይም እራስን ማስተዳደር በሚሉ ርዕሶች ላይ የሚሰጥ ይሆናል ።
እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሰልጣኞቹ ላይ የአመለካከትና የዕውቀት ዕድገት እንደሚያመጣ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ገልጸዋል ።
ስልጠናው ለምንሰራው ስራ እና ለግል ህይወታችን ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ በንቃትና ትኩረት በመስጠት መከታተል እንደሚገባ አሳስበዋል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
❤2
ኦፊሰሩ ከብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ የደንብ ጥሰትን መከላከል እንደሚገባ ተገለፀ ።
21/ 09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለአዲስ ከተማ ፣ ቂርቆስ እና ልደታ ክ/ከተማ ከሚገኙ ኦፊሰሮች ጋር ግምገማዊ የስልጠና መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በ7/24 ቀን ከሌሊት አመራሩና ኦፊሰሩ ተቀናጅቶ በመሰራት በከተማችን ፈጣን እድገት ላይ ተቋማችን የበኩሉን ሚና በብቃት በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የዛሬው ስልጠና ለቀጣይ ስራዎችን አጠናክሮ ለመስራት የሚያግዝ በመሆኑ በአግባቡ እንዲከታተሉ አሳስበዋል ።
በከተማችን ውስጥ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰቶችን አስቀድመን መከላከል እንዲሁም ሁሉም አካል ራሱን ከብልሹ አሰራር መቆጠብ እንደሚገባ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።
የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የኦፊሰሩ ሚና በሚል የተዘጋጀው የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
በአንዳንድ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ላይ የሚታዩ የስነምግባርና ብልሹ አሰራር ችግሮችን በመቅረፍ በአዲስ መንፈስና በመልካም የስራ ተነሳሽነት በቅርቡ ተመርቀው ወደ ሰራ ከሚገቡት ከ6ኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ጋር በመቀናጀት በመንግስትና በህዝብ የተጣለባችሁን ኃላፊነት በብቃት የሚወጣ ሃይል ልትሆኑ ይገባል ሲሉ አቶ እዮብ ተናግረዋል።
የመድረኩ ተሳታፊ ኦፊሰሮች እንደተናገሩት የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ በቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ነው።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አስቀምጠው መድረኩ ተጠናቋል።
በተያያዘ ዜና በቦሌ ክላስተር የካ፣ ቦሌ ፣ ለሚ ኩራ እና ጉለሌ ክ/ከተማ የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የኦፊሰሩ ሚና በሚል መሪ ቃል የስልጠና መድረክ አካሂደዋል ስልጠናው በሶስተኛ ክላስተር ለተቀሩት ክ/ከተማዎች በነገው ዕለት የሚቀጥል ይሆናል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
21/ 09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለአዲስ ከተማ ፣ ቂርቆስ እና ልደታ ክ/ከተማ ከሚገኙ ኦፊሰሮች ጋር ግምገማዊ የስልጠና መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በ7/24 ቀን ከሌሊት አመራሩና ኦፊሰሩ ተቀናጅቶ በመሰራት በከተማችን ፈጣን እድገት ላይ ተቋማችን የበኩሉን ሚና በብቃት በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የዛሬው ስልጠና ለቀጣይ ስራዎችን አጠናክሮ ለመስራት የሚያግዝ በመሆኑ በአግባቡ እንዲከታተሉ አሳስበዋል ።
በከተማችን ውስጥ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰቶችን አስቀድመን መከላከል እንዲሁም ሁሉም አካል ራሱን ከብልሹ አሰራር መቆጠብ እንደሚገባ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።
የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የኦፊሰሩ ሚና በሚል የተዘጋጀው የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
በአንዳንድ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ላይ የሚታዩ የስነምግባርና ብልሹ አሰራር ችግሮችን በመቅረፍ በአዲስ መንፈስና በመልካም የስራ ተነሳሽነት በቅርቡ ተመርቀው ወደ ሰራ ከሚገቡት ከ6ኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ጋር በመቀናጀት በመንግስትና በህዝብ የተጣለባችሁን ኃላፊነት በብቃት የሚወጣ ሃይል ልትሆኑ ይገባል ሲሉ አቶ እዮብ ተናግረዋል።
የመድረኩ ተሳታፊ ኦፊሰሮች እንደተናገሩት የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ በቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ነው።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አስቀምጠው መድረኩ ተጠናቋል።
በተያያዘ ዜና በቦሌ ክላስተር የካ፣ ቦሌ ፣ ለሚ ኩራ እና ጉለሌ ክ/ከተማ የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የኦፊሰሩ ሚና በሚል መሪ ቃል የስልጠና መድረክ አካሂደዋል ስልጠናው በሶስተኛ ክላስተር ለተቀሩት ክ/ከተማዎች በነገው ዕለት የሚቀጥል ይሆናል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍2