ባለስልጣኑ ልምዱን እና ተሞክሮውን ለመንገዶች ባለስልጣን ልዑካን ቡድን አባላት አጋራ
18/9/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ለመጡ የልዑካን ቡድን አባላት ሙስናና በለሹ አሰራሮችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አኳያ በተቋም አደረጃጀት፣ በመመሪያ ዝግጅት ፤በሰው ሃይል አደረጃጀት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር በተመለከተ ያለውን ልምድና ተሞክሮ አጋርቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ በልምድ ማጋራቱ ወቅት የተቋሙ አደረጃጀት እና ተቋሙ በማጠናከር የተቋሙና የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ሂደት በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልፀዋል።
በልምድ ልውውጡ ባለስልጣኑ እንደየስራ ክፍላቸው ብልሹ አሰራር ከመከላከልና ከመቆጣጠር ረገድ የተተገበሩ ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ገለጸፃ አድርገዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ከተቋሙ ልምድ በመውሰድ እና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ለልዑካን ቡድኑ አባላት አስረድተዋል፡፡
የመንገዶች ባለስልጣን የልዑካን ቡድን አባላት ተቋሙ የተደራጀበት እና ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመነጋገር እየሰራ ያለው ውጤታማ ስራዎች አድንቀው የወሰዱት ተሞክሮ እና ልምዱን በተቋማቸው ተግባራዊ በማድረግ እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ዘገባው :-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
18/9/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ለመጡ የልዑካን ቡድን አባላት ሙስናና በለሹ አሰራሮችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አኳያ በተቋም አደረጃጀት፣ በመመሪያ ዝግጅት ፤በሰው ሃይል አደረጃጀት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር በተመለከተ ያለውን ልምድና ተሞክሮ አጋርቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ በልምድ ማጋራቱ ወቅት የተቋሙ አደረጃጀት እና ተቋሙ በማጠናከር የተቋሙና የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ሂደት በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልፀዋል።
በልምድ ልውውጡ ባለስልጣኑ እንደየስራ ክፍላቸው ብልሹ አሰራር ከመከላከልና ከመቆጣጠር ረገድ የተተገበሩ ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ገለጸፃ አድርገዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ከተቋሙ ልምድ በመውሰድ እና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ለልዑካን ቡድኑ አባላት አስረድተዋል፡፡
የመንገዶች ባለስልጣን የልዑካን ቡድን አባላት ተቋሙ የተደራጀበት እና ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመነጋገር እየሰራ ያለው ውጤታማ ስራዎች አድንቀው የወሰዱት ተሞክሮ እና ልምዱን በተቋማቸው ተግባራዊ በማድረግ እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ።
ዘገባው :-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
በኮሪደር ልማት ደህንነት ጥበቃ የታየውን መልካም ስራ በወንዝ ዳርቻ ብክለትና መከላከል ላይ ማስቀጠል እንደሚገባው ተገለፀ።
ግንቦት 19/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለተለያዩ የሀይማኖት አባቶች ፣አባገዳዎች ፣ ሀዳ ስንቄዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ፣ አርቲስቶች ፣ የብሎክ አደረጃጀት ሀላፊዎች እና ለየተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በወንዝና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
መድረኩ በሀይማኖት አባቶና በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት የተጀመረ።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ከተማ አስተዳደሩ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ልማት ከብክለት በመከላከል የኢኮኖሚ ምንጭ እንዲሆኑና በጤና ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ለማስቆም ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ጠቅሰዋል።
በመድረኩ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ከ70 በላይ ወንዞች ሲኖሩ ከመርዛማ ኬሚካል፣ ከመፀዳጃ ቤት ፍሳሾች እና ከበካይ ቆሻሻዎች መከላከል ደህንነታቸው ለማስጠበቅ ደንብ 180/2017 መውጣቱ አስታውቀዋል።
ስልጠናው በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጥ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደመረ በለጠ በሰነድ ቀረቧል።
በስልጠናው የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት፣ በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ፣ መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 የተደነገጉ አስተዳደራዊ እርምጃዎ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በስልጠናው ተሳታፊዎች ባለስልጣኑ በሚያከናውናቸው ተግባራት የከተማዋ የጀርባ ኦጥንት በመሆኑን በተለይ በወንዝና በወንዝ ዳርቻ ብክለት መከላከል ላይ ተቋሙን በማገዝ የድርሻቸው እደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
በእለቱ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየት እና ጥያቄዎች ሰፊ ውይይት በማድረግ ባለስልጣኑ የቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል እና በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በመድረኩ መሠጠቃለያ የወጣው ደንብ ተግባራዊነት የህብረተሰብ እገዛ አስፈላጊ በመሆኑ የዛሬ ስልጠና መድረክ ተሳታፊዎች ለአካባቢአቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ እንዲፈጥሩ መልእክት ተላልፏል።
ዘገባው፦ የባለስልጣኑ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ግንቦት 19/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለተለያዩ የሀይማኖት አባቶች ፣አባገዳዎች ፣ ሀዳ ስንቄዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ፣ አርቲስቶች ፣ የብሎክ አደረጃጀት ሀላፊዎች እና ለየተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በወንዝና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
መድረኩ በሀይማኖት አባቶና በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት የተጀመረ።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ከተማ አስተዳደሩ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ልማት ከብክለት በመከላከል የኢኮኖሚ ምንጭ እንዲሆኑና በጤና ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ለማስቆም ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ጠቅሰዋል።
በመድረኩ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ከ70 በላይ ወንዞች ሲኖሩ ከመርዛማ ኬሚካል፣ ከመፀዳጃ ቤት ፍሳሾች እና ከበካይ ቆሻሻዎች መከላከል ደህንነታቸው ለማስጠበቅ ደንብ 180/2017 መውጣቱ አስታውቀዋል።
ስልጠናው በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጥ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደመረ በለጠ በሰነድ ቀረቧል።
በስልጠናው የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት፣ በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ፣ መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 የተደነገጉ አስተዳደራዊ እርምጃዎ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በስልጠናው ተሳታፊዎች ባለስልጣኑ በሚያከናውናቸው ተግባራት የከተማዋ የጀርባ ኦጥንት በመሆኑን በተለይ በወንዝና በወንዝ ዳርቻ ብክለት መከላከል ላይ ተቋሙን በማገዝ የድርሻቸው እደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
በእለቱ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየት እና ጥያቄዎች ሰፊ ውይይት በማድረግ ባለስልጣኑ የቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል እና በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በመድረኩ መሠጠቃለያ የወጣው ደንብ ተግባራዊነት የህብረተሰብ እገዛ አስፈላጊ በመሆኑ የዛሬ ስልጠና መድረክ ተሳታፊዎች ለአካባቢአቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ እንዲፈጥሩ መልእክት ተላልፏል።
ዘገባው፦ የባለስልጣኑ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ብልሹ አሰራር ለመታገል የአመራሩ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።
19/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለማዕከል፣ ክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች ብልሹ አሠራርን ለመታገል የአመራሩ ሚና የላቀ መሆኑን የሚገልፅ የምክክር መድረክ ተካሄዷል።
ሳሬም ሆቴል አዳራሽ በተዘጋጀው ስልጠና ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት የስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራርን ለመታገል ሁሌም አመራሩ ግንባር ቀደም በመሆን ታግሎ የሚያታግል ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በባለስልጣኑ ስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ መነሻ የሆነ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ሰፊ ውይይትና ምክክር ተካሄዶበታል።
በስልጠናው ተሳታፊዎችም የተለያዩ ሃሳብና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን መሰል ስልጠናዎች ለስራ ቅልጥፍና እና ብልሹ አሰራሮችን ለማስወገድ ያለው ሚና የላቀ በመሆኑ መሠል ስልጠናዎች ተጠናክሮ መቀጠል እዳለበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በማጠቃለያው እንደተናገሩት ከላይ እስከ ታች ድረስ ያለው አመራር አስቀድሞ ተቋሙን መውደድና በእኔነት ስሜት ለፈፃሚው ስራን ማውረድና ግልፅና ተጠያቂነት ባለው መልኩ ተግባሩ መከናወኑን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተከናወኑ ተግባራትን በወቅቱ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ማድረግና ማንኛው ከተቋሙ አገልግሎት ፈልጎ የሚመጣን አካል በፍፁም ሰብአዊነት ማገልገል እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ መድረኩ ጠናቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
19/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለማዕከል፣ ክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች ብልሹ አሠራርን ለመታገል የአመራሩ ሚና የላቀ መሆኑን የሚገልፅ የምክክር መድረክ ተካሄዷል።
ሳሬም ሆቴል አዳራሽ በተዘጋጀው ስልጠና ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት የስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራርን ለመታገል ሁሌም አመራሩ ግንባር ቀደም በመሆን ታግሎ የሚያታግል ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በባለስልጣኑ ስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ መነሻ የሆነ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ሰፊ ውይይትና ምክክር ተካሄዶበታል።
በስልጠናው ተሳታፊዎችም የተለያዩ ሃሳብና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን መሰል ስልጠናዎች ለስራ ቅልጥፍና እና ብልሹ አሰራሮችን ለማስወገድ ያለው ሚና የላቀ በመሆኑ መሠል ስልጠናዎች ተጠናክሮ መቀጠል እዳለበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በማጠቃለያው እንደተናገሩት ከላይ እስከ ታች ድረስ ያለው አመራር አስቀድሞ ተቋሙን መውደድና በእኔነት ስሜት ለፈፃሚው ስራን ማውረድና ግልፅና ተጠያቂነት ባለው መልኩ ተግባሩ መከናወኑን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተከናወኑ ተግባራትን በወቅቱ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ማድረግና ማንኛው ከተቋሙ አገልግሎት ፈልጎ የሚመጣን አካል በፍፁም ሰብአዊነት ማገልገል እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ መድረኩ ጠናቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍2😁1