የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ከ6ኛ ዙር ዕጩ ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ጋር በስልጠናው ዙሪያ ውይይት አደረጉ
30/08/2017 ዓ.ም
**ይርጋለም/አፖስቶ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ እየሰጠ በሚገኘው የ6ኛ ዙር ዕጩ ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ሂደት ላይ የባለስልጣኑ እና ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመረሮች በተገኙበት ከሰልጣኞች ጋር ውይይት ተካሄደ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ አዲስ ምልምል ሰልጣኙ ስልጠናውን አጠናቆ በቀጣይ ወደ ስራ ሲቀላቀል ለተቋሙ ግንባር ቀደም ሰራተኛ በመሆን ትልቁን አስተዋጾ ያበረክታል ለዚህም ሰልጣኙ በስልጠና ወቅት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ስልጠናውን በብቃት ሊያጠናቅቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስልጠና ወቅት እያለፍን ያለነው ውጣውረድ ለግል ህይወታችንም ሆነ በስራ ላይ ለሚጠብቀን መንገድ ጠቃሚ ሆኖ አግኝተነዋል ያሉት ሰልጣኝ ኦፊሰሮቹ ቀጣይ የምንወስዳቸው ስልጠናዎችም የበለጠ ብቁ ጠንካራ ሆነን እንድንወጣ ያደርገናል በማለት ሀሳብ ሰጥተዋል።
በተለይ ስልጠናውን እየሰጡ እና እያስተባበሩ ላሉት የባለስልጣኑ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና አስተባባሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በመጨረሻም ከሰልጣኙ ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች በባለስልጣኑ አመራሮች ማብራሪያ በመስጠት ሰልጣኙ ስልጠናውን በተነሳሽነትና በሞራል በመውሰድ የበቃ ኦፊሰር ሆኖ በመውጣት ለተቋሙ ትልቅ ግብአት መሆን እንደሚገባቸው በመግለጽ ውይይቱ ተጠናቋል።
በሳምራዊት ዘሪሁን
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ
30/08/2017 ዓ.ም
**ይርጋለም/አፖስቶ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ እየሰጠ በሚገኘው የ6ኛ ዙር ዕጩ ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ሂደት ላይ የባለስልጣኑ እና ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመረሮች በተገኙበት ከሰልጣኞች ጋር ውይይት ተካሄደ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ አዲስ ምልምል ሰልጣኙ ስልጠናውን አጠናቆ በቀጣይ ወደ ስራ ሲቀላቀል ለተቋሙ ግንባር ቀደም ሰራተኛ በመሆን ትልቁን አስተዋጾ ያበረክታል ለዚህም ሰልጣኙ በስልጠና ወቅት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ስልጠናውን በብቃት ሊያጠናቅቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስልጠና ወቅት እያለፍን ያለነው ውጣውረድ ለግል ህይወታችንም ሆነ በስራ ላይ ለሚጠብቀን መንገድ ጠቃሚ ሆኖ አግኝተነዋል ያሉት ሰልጣኝ ኦፊሰሮቹ ቀጣይ የምንወስዳቸው ስልጠናዎችም የበለጠ ብቁ ጠንካራ ሆነን እንድንወጣ ያደርገናል በማለት ሀሳብ ሰጥተዋል።
በተለይ ስልጠናውን እየሰጡ እና እያስተባበሩ ላሉት የባለስልጣኑ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና አስተባባሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በመጨረሻም ከሰልጣኙ ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች በባለስልጣኑ አመራሮች ማብራሪያ በመስጠት ሰልጣኙ ስልጠናውን በተነሳሽነትና በሞራል በመውሰድ የበቃ ኦፊሰር ሆኖ በመውጣት ለተቋሙ ትልቅ ግብአት መሆን እንደሚገባቸው በመግለጽ ውይይቱ ተጠናቋል።
በሳምራዊት ዘሪሁን
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ
👍14❤1
ባለስልጣኑ ኮሪደር ልማት በመኪና ጉዳት ያደረሰው ሻሞ የመኪና ኪራይ ድርጅት 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
03/09/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካሳንቺስ አካባቢ ምሽት 2:ዐዐ ሰአት አካባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ በኮርደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረስ የደንብ መተላለፍ የፈፀመ ሻሞ የመኪና ኪራይ ድርጅት 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ።
የደንብ መተላለፉ አዲስ በተስራው በኮርደር ልማት የብስክሌት መንገድ በመኪነና በመሄድ በህዝብ ሀብት ላይ በተሰራው ልማት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ድርጊቱ ከቅጣቱ ባለፈ በህግ ተጠያቂነትንም ስለሚያስከትል አሽከርካሪው ለጊዜው ቢሰወርም በህግ ቁጥጥር ስር ይውል ዘንድ ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
በሰዓቱ የተመደቡ ሁለት ኦፊሰሮች በቀጠናው ስራ ላይ ቢኖሩም አፋጣኝ እርምጃ ባለመውሰዳቸው የአንድ ወር ደሞዝ እንዲቀጡ ተደርጓል።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
03/09/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካሳንቺስ አካባቢ ምሽት 2:ዐዐ ሰአት አካባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ በኮርደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረስ የደንብ መተላለፍ የፈፀመ ሻሞ የመኪና ኪራይ ድርጅት 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ።
የደንብ መተላለፉ አዲስ በተስራው በኮርደር ልማት የብስክሌት መንገድ በመኪነና በመሄድ በህዝብ ሀብት ላይ በተሰራው ልማት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ድርጊቱ ከቅጣቱ ባለፈ በህግ ተጠያቂነትንም ስለሚያስከትል አሽከርካሪው ለጊዜው ቢሰወርም በህግ ቁጥጥር ስር ይውል ዘንድ ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
በሰዓቱ የተመደቡ ሁለት ኦፊሰሮች በቀጠናው ስራ ላይ ቢኖሩም አፋጣኝ እርምጃ ባለመውሰዳቸው የአንድ ወር ደሞዝ እንዲቀጡ ተደርጓል።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍13❤2
''ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቋምና አፈፃጸሙ በማሳደግ ተዓምራዊ ለውጥ በማምጣት ላይ ይገኛል" የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ የሰላም፣ የፍትህና መልካም አስተዳደር የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ
ግንቦት 4/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም የፍትህ መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴዎች የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት 9 ወራት የተሰሩ ስራዎችን በተመለከተ የመስክ ምልከታ በማድረግ አፈፃፀሙ ገመገሙ፡፡
በግምገማው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሰላም ፍትህና መልካም አስተዳደር የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን በማሳደግ ተምራዊ ለውጥ በማምጣት የከተማ አስተዳደሩን ደንብ ጥሰቶች በመከላከል አዳስ የወጡ ደንቦችን የማስተግበር ትልቅ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ገልፀው ይህንንም ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ በሎም ማዕከል ላይ በተደረገ የመስክ ምልከታ እና ሱፐር ቭዥን መመልከታቸውን ተናግረዋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ3ሺህ በላይ ለሚሆኑ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የደመወዝ ልዮነትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች መስተካከል መቻሉ ፤ ከድግሪ በላይ የሆኑ 2000 ምልምል የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አያይዘውም ባለስልጣኑ ለሀገሪቱ ክልል ከተሞች ደንብ የማስከበር ተሞክሮ የመስጠት አስተዎፆ እያደረጉ መሆኑን እና በከተማ አሰተዳደሩ ከሚገኙ አብዛኛው ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ደንብን የማስከበር ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስገንዝበዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ተስፋሁን አሉላ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ በርካታ የተቋም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸው ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ሰራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን በሪፖርቱ ቀርቦል፡፡
ከቋሚ ኮሚቴው አባላት ባለስልጣኑ ከዕለት ወደ እለት እራሱን በማሻሻል አዳዲስ ስራዎችን በቁርጠኝነት በመስራት የተለወጠ ደንብ ማሳየት መቻሉን ፣ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ ያለውን መሻሻል ይበል የሚሰኝ ተግባር መሆኑን በመግለፅ በተለይም መድረኮች ሲኖሩ ቋሚ ኮሚቴውን በመጋበዝ የሚነሱ ችግሮችን ቀጥታ ቋሚ ኮሚቴው ከሚመለከተው አካል እንዲወስድ የማድረግ ስራ መሰራቱን የቋሚ ኮሚቴው ተወካዮች ገልፀዋል።
በተጨማሪም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተናበው ሰራዎችን ከሰባዊነት ጋር በመስራቱ ለውጦች መመጣታቸውን ጠቁመው በምዘናው አብዛኛው በጥንካሬ አንደሚወሰድ ተገልጿል ።
በመጨረሻም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋም ግንባታ እና አዲስ የስገነባውን የቴሌቪዥን እና የሬዲዮ ስቱዲዮ በመጉብኝት ምዘናው ተጠናቋል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ግንቦት 4/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም የፍትህ መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴዎች የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት 9 ወራት የተሰሩ ስራዎችን በተመለከተ የመስክ ምልከታ በማድረግ አፈፃፀሙ ገመገሙ፡፡
በግምገማው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሰላም ፍትህና መልካም አስተዳደር የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን በማሳደግ ተምራዊ ለውጥ በማምጣት የከተማ አስተዳደሩን ደንብ ጥሰቶች በመከላከል አዳስ የወጡ ደንቦችን የማስተግበር ትልቅ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ገልፀው ይህንንም ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ በሎም ማዕከል ላይ በተደረገ የመስክ ምልከታ እና ሱፐር ቭዥን መመልከታቸውን ተናግረዋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ3ሺህ በላይ ለሚሆኑ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የደመወዝ ልዮነትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች መስተካከል መቻሉ ፤ ከድግሪ በላይ የሆኑ 2000 ምልምል የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አያይዘውም ባለስልጣኑ ለሀገሪቱ ክልል ከተሞች ደንብ የማስከበር ተሞክሮ የመስጠት አስተዎፆ እያደረጉ መሆኑን እና በከተማ አሰተዳደሩ ከሚገኙ አብዛኛው ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ደንብን የማስከበር ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስገንዝበዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ተስፋሁን አሉላ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ በርካታ የተቋም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸው ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ሰራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን በሪፖርቱ ቀርቦል፡፡
ከቋሚ ኮሚቴው አባላት ባለስልጣኑ ከዕለት ወደ እለት እራሱን በማሻሻል አዳዲስ ስራዎችን በቁርጠኝነት በመስራት የተለወጠ ደንብ ማሳየት መቻሉን ፣ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ ያለውን መሻሻል ይበል የሚሰኝ ተግባር መሆኑን በመግለፅ በተለይም መድረኮች ሲኖሩ ቋሚ ኮሚቴውን በመጋበዝ የሚነሱ ችግሮችን ቀጥታ ቋሚ ኮሚቴው ከሚመለከተው አካል እንዲወስድ የማድረግ ስራ መሰራቱን የቋሚ ኮሚቴው ተወካዮች ገልፀዋል።
በተጨማሪም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተናበው ሰራዎችን ከሰባዊነት ጋር በመስራቱ ለውጦች መመጣታቸውን ጠቁመው በምዘናው አብዛኛው በጥንካሬ አንደሚወሰድ ተገልጿል ።
በመጨረሻም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋም ግንባታ እና አዲስ የስገነባውን የቴሌቪዥን እና የሬዲዮ ስቱዲዮ በመጉብኝት ምዘናው ተጠናቋል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍2
በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ደንብ የተላለፉ ተቋማት 1.5 ሚሊየን ብር ተቀጡ
04/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በለሚኩራ ክፋለ ከተማ ወረዳ 03 ኖህ ሪል እስቴት ከተቋሙ ግቢ የመፀዳጃ ቤት ፍሳሽ ከወንዝ ጋር በቀጥታ በማገናኘታቸው በተደጋጋሚ በተፈጠረላቸው በግንዛቤ እና በተወሰደባቸው የገንዘብ መቀጮ ተምረው ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እና ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ባለመቻላቸው በዛሬው እለት ከአካባቢ ጥበቃ፣ ከሰላም ፀጥታ እና ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት በሪከርድ የጥፋቱ እጥፍ 800,000 ብር መቀጣቱ አስታወቀ።
በተመሳሳይ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ሁለት ተቋማት ደንብ ቁጥር 180/2017 ተላልፈው በመገኘታቸው 700,000 በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።
በአጠቃላይ በዛሬው እለት በክፍለ ከተማው ደንብ ቁጥር 180/2017 ተላልፈው በተገኙ ሶስት ተቋማት ላይ በተወሰደ እርምጃ 1,500,000 ብር መቀጣታቸው ገልጿል።
ባለስልጣኑ በከተማው ከአሁን በፊት ተቀጥተው ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ ተቋምና ግለሰቦችን በሪከርድ የቅጣቱ እጥፍ በመቅጣት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
ተቋሙ ለከተማው ነዋሪዎች ማንኛውም የደንብ መተላለፎች ሲያጋጥሙ ለደንብ ማስከበር ባለስልጣን በነጻ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲያደርስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሮክቶሬት ነው።
04/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በለሚኩራ ክፋለ ከተማ ወረዳ 03 ኖህ ሪል እስቴት ከተቋሙ ግቢ የመፀዳጃ ቤት ፍሳሽ ከወንዝ ጋር በቀጥታ በማገናኘታቸው በተደጋጋሚ በተፈጠረላቸው በግንዛቤ እና በተወሰደባቸው የገንዘብ መቀጮ ተምረው ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እና ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ባለመቻላቸው በዛሬው እለት ከአካባቢ ጥበቃ፣ ከሰላም ፀጥታ እና ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት በሪከርድ የጥፋቱ እጥፍ 800,000 ብር መቀጣቱ አስታወቀ።
በተመሳሳይ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ሁለት ተቋማት ደንብ ቁጥር 180/2017 ተላልፈው በመገኘታቸው 700,000 በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል።
በአጠቃላይ በዛሬው እለት በክፍለ ከተማው ደንብ ቁጥር 180/2017 ተላልፈው በተገኙ ሶስት ተቋማት ላይ በተወሰደ እርምጃ 1,500,000 ብር መቀጣታቸው ገልጿል።
ባለስልጣኑ በከተማው ከአሁን በፊት ተቀጥተው ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ ተቋምና ግለሰቦችን በሪከርድ የቅጣቱ እጥፍ በመቅጣት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
ተቋሙ ለከተማው ነዋሪዎች ማንኛውም የደንብ መተላለፎች ሲያጋጥሙ ለደንብ ማስከበር ባለስልጣን በነጻ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲያደርስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሮክቶሬት ነው።
👍4