የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ውይይት አደረገ
ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም እና የቀሪ ወራት ስራዎች በተመለከተ ከ11 ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስራ ሂደት አስተባባሪዎች እና ቡድን መሪዎች ጋር ውይይት አደረገ።
በውይይቱ የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና በሚያዚያ ወር ድጋፍና ክትትል የታዩ ስራዎች በድክመትና ጥንካሬ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ዳይሬክቶሪት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠርካለም ጌታሁን ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱ በአጠቃላይ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተደረጉ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችና ስልጠናዎች ለባለድርሻ አካለት ፣ ለሲቪክ ማህበራት ፣ለበጎ ፈቃደኞች፣ ለፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች፣ ለፖለቲካ አመራሮች እና ለሀይማኖት አባቶች በተለያዮ ርዕሰ ጉዳዮች የተሰጡ ስልጠናዎች ና የግንዛቤ ሰራዎችን በዝርዝር አቅርበዋል።
በተለይ በደንብ ቁጥር 150/2015 ዓ.ም ለማሰፈፀም ተሻሽሎ በወጣው ደንብ ቁጥር 167/2016 ዓ.ም እና በወንዞች ዳርቻ ልማት አስመልክቶ በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ መድረኮች በመፍጠር የግንዛቤ ስራው ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ እና ውጤቶች መገኘቱ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በመድረኩ በክፍለ ከተማ እና በወረዳ በተደረገ የክትትልና ድጋፍ ግብር መልስ ለማሳያነት የሚሆኑ የለሚ ኩራ ፣ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 የአዲስ ከተማ እና የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች በጥንካሬ እና በክፍተት የነበራቸው ግብረ መልስ በመድረኩ ለማቅረብ ተችሎል።
በመጨረሻም በውይይቱ በቀረበው ሪፖርት እና ግብረ መልስ ላይ ከተሳታፊዎች አስተያየት እና ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን ከመድረክ ምላሽ ተሰጥቶባቸው የቀጣይ ወራት የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም እና የቀሪ ወራት ስራዎች በተመለከተ ከ11 ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስራ ሂደት አስተባባሪዎች እና ቡድን መሪዎች ጋር ውይይት አደረገ።
በውይይቱ የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና በሚያዚያ ወር ድጋፍና ክትትል የታዩ ስራዎች በድክመትና ጥንካሬ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ዳይሬክቶሪት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠርካለም ጌታሁን ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱ በአጠቃላይ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተደረጉ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችና ስልጠናዎች ለባለድርሻ አካለት ፣ ለሲቪክ ማህበራት ፣ለበጎ ፈቃደኞች፣ ለፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች፣ ለፖለቲካ አመራሮች እና ለሀይማኖት አባቶች በተለያዮ ርዕሰ ጉዳዮች የተሰጡ ስልጠናዎች ና የግንዛቤ ሰራዎችን በዝርዝር አቅርበዋል።
በተለይ በደንብ ቁጥር 150/2015 ዓ.ም ለማሰፈፀም ተሻሽሎ በወጣው ደንብ ቁጥር 167/2016 ዓ.ም እና በወንዞች ዳርቻ ልማት አስመልክቶ በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ መድረኮች በመፍጠር የግንዛቤ ስራው ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ እና ውጤቶች መገኘቱ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በመድረኩ በክፍለ ከተማ እና በወረዳ በተደረገ የክትትልና ድጋፍ ግብር መልስ ለማሳያነት የሚሆኑ የለሚ ኩራ ፣ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 የአዲስ ከተማ እና የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች በጥንካሬ እና በክፍተት የነበራቸው ግብረ መልስ በመድረኩ ለማቅረብ ተችሎል።
በመጨረሻም በውይይቱ በቀረበው ሪፖርት እና ግብረ መልስ ላይ ከተሳታፊዎች አስተያየት እና ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን ከመድረክ ምላሽ ተሰጥቶባቸው የቀጣይ ወራት የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍1
የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ከ6ኛ ዙር ዕጩ ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ጋር በስልጠናው ዙሪያ ውይይት አደረጉ
30/08/2017 ዓ.ም
**ይርጋለም/አፖስቶ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ እየሰጠ በሚገኘው የ6ኛ ዙር ዕጩ ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ሂደት ላይ የባለስልጣኑ እና ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመረሮች በተገኙበት ከሰልጣኞች ጋር ውይይት ተካሄደ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ አዲስ ምልምል ሰልጣኙ ስልጠናውን አጠናቆ በቀጣይ ወደ ስራ ሲቀላቀል ለተቋሙ ግንባር ቀደም ሰራተኛ በመሆን ትልቁን አስተዋጾ ያበረክታል ለዚህም ሰልጣኙ በስልጠና ወቅት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ስልጠናውን በብቃት ሊያጠናቅቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስልጠና ወቅት እያለፍን ያለነው ውጣውረድ ለግል ህይወታችንም ሆነ በስራ ላይ ለሚጠብቀን መንገድ ጠቃሚ ሆኖ አግኝተነዋል ያሉት ሰልጣኝ ኦፊሰሮቹ ቀጣይ የምንወስዳቸው ስልጠናዎችም የበለጠ ብቁ ጠንካራ ሆነን እንድንወጣ ያደርገናል በማለት ሀሳብ ሰጥተዋል።
በተለይ ስልጠናውን እየሰጡ እና እያስተባበሩ ላሉት የባለስልጣኑ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና አስተባባሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በመጨረሻም ከሰልጣኙ ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች በባለስልጣኑ አመራሮች ማብራሪያ በመስጠት ሰልጣኙ ስልጠናውን በተነሳሽነትና በሞራል በመውሰድ የበቃ ኦፊሰር ሆኖ በመውጣት ለተቋሙ ትልቅ ግብአት መሆን እንደሚገባቸው በመግለጽ ውይይቱ ተጠናቋል።
በሳምራዊት ዘሪሁን
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ
30/08/2017 ዓ.ም
**ይርጋለም/አፖስቶ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ እየሰጠ በሚገኘው የ6ኛ ዙር ዕጩ ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ሂደት ላይ የባለስልጣኑ እና ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመረሮች በተገኙበት ከሰልጣኞች ጋር ውይይት ተካሄደ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ አዲስ ምልምል ሰልጣኙ ስልጠናውን አጠናቆ በቀጣይ ወደ ስራ ሲቀላቀል ለተቋሙ ግንባር ቀደም ሰራተኛ በመሆን ትልቁን አስተዋጾ ያበረክታል ለዚህም ሰልጣኙ በስልጠና ወቅት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ስልጠናውን በብቃት ሊያጠናቅቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስልጠና ወቅት እያለፍን ያለነው ውጣውረድ ለግል ህይወታችንም ሆነ በስራ ላይ ለሚጠብቀን መንገድ ጠቃሚ ሆኖ አግኝተነዋል ያሉት ሰልጣኝ ኦፊሰሮቹ ቀጣይ የምንወስዳቸው ስልጠናዎችም የበለጠ ብቁ ጠንካራ ሆነን እንድንወጣ ያደርገናል በማለት ሀሳብ ሰጥተዋል።
በተለይ ስልጠናውን እየሰጡ እና እያስተባበሩ ላሉት የባለስልጣኑ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና አስተባባሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በመጨረሻም ከሰልጣኙ ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች በባለስልጣኑ አመራሮች ማብራሪያ በመስጠት ሰልጣኙ ስልጠናውን በተነሳሽነትና በሞራል በመውሰድ የበቃ ኦፊሰር ሆኖ በመውጣት ለተቋሙ ትልቅ ግብአት መሆን እንደሚገባቸው በመግለጽ ውይይቱ ተጠናቋል።
በሳምራዊት ዘሪሁን
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ
👍14❤1
ባለስልጣኑ ኮሪደር ልማት በመኪና ጉዳት ያደረሰው ሻሞ የመኪና ኪራይ ድርጅት 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
03/09/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካሳንቺስ አካባቢ ምሽት 2:ዐዐ ሰአት አካባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ በኮርደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረስ የደንብ መተላለፍ የፈፀመ ሻሞ የመኪና ኪራይ ድርጅት 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ።
የደንብ መተላለፉ አዲስ በተስራው በኮርደር ልማት የብስክሌት መንገድ በመኪነና በመሄድ በህዝብ ሀብት ላይ በተሰራው ልማት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ድርጊቱ ከቅጣቱ ባለፈ በህግ ተጠያቂነትንም ስለሚያስከትል አሽከርካሪው ለጊዜው ቢሰወርም በህግ ቁጥጥር ስር ይውል ዘንድ ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
በሰዓቱ የተመደቡ ሁለት ኦፊሰሮች በቀጠናው ስራ ላይ ቢኖሩም አፋጣኝ እርምጃ ባለመውሰዳቸው የአንድ ወር ደሞዝ እንዲቀጡ ተደርጓል።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
03/09/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካሳንቺስ አካባቢ ምሽት 2:ዐዐ ሰአት አካባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ በኮርደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረስ የደንብ መተላለፍ የፈፀመ ሻሞ የመኪና ኪራይ ድርጅት 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ።
የደንብ መተላለፉ አዲስ በተስራው በኮርደር ልማት የብስክሌት መንገድ በመኪነና በመሄድ በህዝብ ሀብት ላይ በተሰራው ልማት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ድርጊቱ ከቅጣቱ ባለፈ በህግ ተጠያቂነትንም ስለሚያስከትል አሽከርካሪው ለጊዜው ቢሰወርም በህግ ቁጥጥር ስር ይውል ዘንድ ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
በሰዓቱ የተመደቡ ሁለት ኦፊሰሮች በቀጠናው ስራ ላይ ቢኖሩም አፋጣኝ እርምጃ ባለመውሰዳቸው የአንድ ወር ደሞዝ እንዲቀጡ ተደርጓል።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍13❤2
''ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቋምና አፈፃጸሙ በማሳደግ ተዓምራዊ ለውጥ በማምጣት ላይ ይገኛል" የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ የሰላም፣ የፍትህና መልካም አስተዳደር የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ
ግንቦት 4/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም የፍትህ መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴዎች የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት 9 ወራት የተሰሩ ስራዎችን በተመለከተ የመስክ ምልከታ በማድረግ አፈፃፀሙ ገመገሙ፡፡
በግምገማው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሰላም ፍትህና መልካም አስተዳደር የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን በማሳደግ ተምራዊ ለውጥ በማምጣት የከተማ አስተዳደሩን ደንብ ጥሰቶች በመከላከል አዳስ የወጡ ደንቦችን የማስተግበር ትልቅ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ገልፀው ይህንንም ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ በሎም ማዕከል ላይ በተደረገ የመስክ ምልከታ እና ሱፐር ቭዥን መመልከታቸውን ተናግረዋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ3ሺህ በላይ ለሚሆኑ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የደመወዝ ልዮነትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች መስተካከል መቻሉ ፤ ከድግሪ በላይ የሆኑ 2000 ምልምል የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አያይዘውም ባለስልጣኑ ለሀገሪቱ ክልል ከተሞች ደንብ የማስከበር ተሞክሮ የመስጠት አስተዎፆ እያደረጉ መሆኑን እና በከተማ አሰተዳደሩ ከሚገኙ አብዛኛው ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ደንብን የማስከበር ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስገንዝበዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ተስፋሁን አሉላ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ በርካታ የተቋም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸው ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ሰራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን በሪፖርቱ ቀርቦል፡፡
ከቋሚ ኮሚቴው አባላት ባለስልጣኑ ከዕለት ወደ እለት እራሱን በማሻሻል አዳዲስ ስራዎችን በቁርጠኝነት በመስራት የተለወጠ ደንብ ማሳየት መቻሉን ፣ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ ያለውን መሻሻል ይበል የሚሰኝ ተግባር መሆኑን በመግለፅ በተለይም መድረኮች ሲኖሩ ቋሚ ኮሚቴውን በመጋበዝ የሚነሱ ችግሮችን ቀጥታ ቋሚ ኮሚቴው ከሚመለከተው አካል እንዲወስድ የማድረግ ስራ መሰራቱን የቋሚ ኮሚቴው ተወካዮች ገልፀዋል።
በተጨማሪም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተናበው ሰራዎችን ከሰባዊነት ጋር በመስራቱ ለውጦች መመጣታቸውን ጠቁመው በምዘናው አብዛኛው በጥንካሬ አንደሚወሰድ ተገልጿል ።
በመጨረሻም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋም ግንባታ እና አዲስ የስገነባውን የቴሌቪዥን እና የሬዲዮ ስቱዲዮ በመጉብኝት ምዘናው ተጠናቋል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ግንቦት 4/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም የፍትህ መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴዎች የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት 9 ወራት የተሰሩ ስራዎችን በተመለከተ የመስክ ምልከታ በማድረግ አፈፃፀሙ ገመገሙ፡፡
በግምገማው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሰላም ፍትህና መልካም አስተዳደር የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን በማሳደግ ተምራዊ ለውጥ በማምጣት የከተማ አስተዳደሩን ደንብ ጥሰቶች በመከላከል አዳስ የወጡ ደንቦችን የማስተግበር ትልቅ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ገልፀው ይህንንም ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ በሎም ማዕከል ላይ በተደረገ የመስክ ምልከታ እና ሱፐር ቭዥን መመልከታቸውን ተናግረዋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ3ሺህ በላይ ለሚሆኑ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የደመወዝ ልዮነትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች መስተካከል መቻሉ ፤ ከድግሪ በላይ የሆኑ 2000 ምልምል የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አያይዘውም ባለስልጣኑ ለሀገሪቱ ክልል ከተሞች ደንብ የማስከበር ተሞክሮ የመስጠት አስተዎፆ እያደረጉ መሆኑን እና በከተማ አሰተዳደሩ ከሚገኙ አብዛኛው ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ደንብን የማስከበር ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስገንዝበዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ተስፋሁን አሉላ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ በርካታ የተቋም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸው ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰራታቸውን ፣ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ሰራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን በሪፖርቱ ቀርቦል፡፡
ከቋሚ ኮሚቴው አባላት ባለስልጣኑ ከዕለት ወደ እለት እራሱን በማሻሻል አዳዲስ ስራዎችን በቁርጠኝነት በመስራት የተለወጠ ደንብ ማሳየት መቻሉን ፣ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ ያለውን መሻሻል ይበል የሚሰኝ ተግባር መሆኑን በመግለፅ በተለይም መድረኮች ሲኖሩ ቋሚ ኮሚቴውን በመጋበዝ የሚነሱ ችግሮችን ቀጥታ ቋሚ ኮሚቴው ከሚመለከተው አካል እንዲወስድ የማድረግ ስራ መሰራቱን የቋሚ ኮሚቴው ተወካዮች ገልፀዋል።
በተጨማሪም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተናበው ሰራዎችን ከሰባዊነት ጋር በመስራቱ ለውጦች መመጣታቸውን ጠቁመው በምዘናው አብዛኛው በጥንካሬ አንደሚወሰድ ተገልጿል ።
በመጨረሻም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋም ግንባታ እና አዲስ የስገነባውን የቴሌቪዥን እና የሬዲዮ ስቱዲዮ በመጉብኝት ምዘናው ተጠናቋል ።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍2