ባለስልጣኑ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት የተሰሩ ስራዎችን ገመገመ
16/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ቅንጅታዊ ስራዎችን ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ የባለስልጣኑ ኃላፊዎች በተገኙበት ከባለድርሻ አካላት አመራሮች ጋር በጋራ የግምገማ መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በዘጠኝ ወራት ከባለድርሻ አካላት ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት የሰራቸውን ስራዎች በወቅቱ በመገምገም ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀሪ ጊዜያት የአመቱን እቅድ ለማሳካት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ስራዎችን በጋራ መገምገም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የከተማችንና የአከባቢያችንን ውበት ማስጠበቅ ፣ የወንዝና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከላከል ፣ የከተማችን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ ፣ ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰትን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ተቀናጅቶ በመስራት ውጤታማ መሆን መቻሉን ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በዘጠኝ ወራት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች በጥንካሬ እና በጉድለት በሰነድ ተለይተው በባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል ።
የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በማጠናከር ወደ ቅጣት ከመገባቱ በፊት ለህብረተሰቡ ስለ ደንብ ማስከበር በቂ እውቀት በማስገንዘብ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ቅንጅት በማጠናከር ከተማችን እንደ ስሟ አዲስና ውብ ለነዋሪዎች ምቹ ለቱሪስት መስብ እንድትሆን በትጋት መስራት እንደሚገባ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ተናግረዋል ።
ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በርካታ ስኬታማ ተግባራትን በማከናወንና የገጽታ ግንባታ ስራን አጠናክሮ በመስራቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰቶች እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረክ መሪዎች ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
16/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ቅንጅታዊ ስራዎችን ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ የባለስልጣኑ ኃላፊዎች በተገኙበት ከባለድርሻ አካላት አመራሮች ጋር በጋራ የግምገማ መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በዘጠኝ ወራት ከባለድርሻ አካላት ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት የሰራቸውን ስራዎች በወቅቱ በመገምገም ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀሪ ጊዜያት የአመቱን እቅድ ለማሳካት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ስራዎችን በጋራ መገምገም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የከተማችንና የአከባቢያችንን ውበት ማስጠበቅ ፣ የወንዝና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከላከል ፣ የከተማችን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ ፣ ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰትን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ተቀናጅቶ በመስራት ውጤታማ መሆን መቻሉን ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በዘጠኝ ወራት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች በጥንካሬ እና በጉድለት በሰነድ ተለይተው በባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል ።
የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በማጠናከር ወደ ቅጣት ከመገባቱ በፊት ለህብረተሰቡ ስለ ደንብ ማስከበር በቂ እውቀት በማስገንዘብ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ቅንጅት በማጠናከር ከተማችን እንደ ስሟ አዲስና ውብ ለነዋሪዎች ምቹ ለቱሪስት መስብ እንድትሆን በትጋት መስራት እንደሚገባ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ተናግረዋል ።
ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በርካታ ስኬታማ ተግባራትን በማከናወንና የገጽታ ግንባታ ስራን አጠናክሮ በመስራቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰቶች እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረክ መሪዎች ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
April 24
April 24
የደንብ ማስከበር ሰራተኞች ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ተገለፀ
ሚያዚያ 17-2017ዓም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ለክፍለ ከተማው ሁሉም ወረዳዎች ለሚገኙ ከ650 በላይ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በስነምግባር እና ፀረ-ሙስና ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ቅርንጯፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በጥሩ ስነ-ምግባር ታንፀው የደንብ መተላለፎችን ለማስቀረት አያደረጉት ያለው ጥረት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ሰራተኞቹ የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ባለፈ በከተማዋ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ በበኩላቸው የዘርፉ ሰራተኞች ጥሩ ስነ-ምግባርን ተላብሰው ከፀረሙስና የፀዳ አገልግሎት በመስጠት ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ሰልጣኞች በበኩላቸው ከብልሹ አሰራር የፀዳና ደንብና መመሪያ መሰረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠናው ከፍተኛ አስተዎፅኦ እንዳለው ተናግረዋል::
ሚያዚያ 17-2017ዓም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ለክፍለ ከተማው ሁሉም ወረዳዎች ለሚገኙ ከ650 በላይ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በስነምግባር እና ፀረ-ሙስና ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ቅርንጯፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በጥሩ ስነ-ምግባር ታንፀው የደንብ መተላለፎችን ለማስቀረት አያደረጉት ያለው ጥረት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ሰራተኞቹ የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ባለፈ በከተማዋ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ በበኩላቸው የዘርፉ ሰራተኞች ጥሩ ስነ-ምግባርን ተላብሰው ከፀረሙስና የፀዳ አገልግሎት በመስጠት ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ሰልጣኞች በበኩላቸው ከብልሹ አሰራር የፀዳና ደንብና መመሪያ መሰረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠናው ከፍተኛ አስተዎፅኦ እንዳለው ተናግረዋል::
April 26
በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ለተቋሙ በጎ ፈቃደኞች ግንዛቤ ተፈጠረ
17/08/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ወንዝና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ከ11ዱም ክፍለ ከተማ ተወጣጡ በጎ ፈቃደኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በንግግራቸውም ባለስልጣኑ የከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን የመጠበቅ ፣ህጋዊ ንግድ የመፋጠር፣ ቆሻሻዎች በአግባቡ እንዲወገዱ የማድረግ ፣ የከተማን ፕላን የጠበቀ ግንባታ እንዲፈፀም የማድረግ ፣የመንግስትን መሬት የመጠበቅ እና ህጋዊ እርድ እንዲፈፀም የማድረግ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልፀው ደንቡን በሚተላለፉት ላይ አስተማሪ እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል።
አክለውም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ስራዎች ለመስራት ከበጎ ፈቃደኞች እገዛ አይነተኛውን ሚና እንደሚጫዎት እና በጎ ፈቃደኞች በደንቡ ላይ ግንዛቤ አግኝተው በሚኖሩበት አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ደንቡን እንዲያስገነዝቡ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጥ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደመረ በለጠ አማካኝነት በቀረበ ሰነድ የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት፣ በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ፣ መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 እና የቅጣት ሰንጠረዥ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል ደንቡን በተላለፉ ድርጅት እና ግለሰብ ለይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር እስከ ከፍተኛው አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚያስቀጣ ገልፀዋል።
የባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በደንቡ ዙሪያ በተለያዩ አግባቦች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ መሰጠቱን እና ግንዛቤ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
17/08/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ወንዝና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ከ11ዱም ክፍለ ከተማ ተወጣጡ በጎ ፈቃደኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በንግግራቸውም ባለስልጣኑ የከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን የመጠበቅ ፣ህጋዊ ንግድ የመፋጠር፣ ቆሻሻዎች በአግባቡ እንዲወገዱ የማድረግ ፣ የከተማን ፕላን የጠበቀ ግንባታ እንዲፈፀም የማድረግ ፣የመንግስትን መሬት የመጠበቅ እና ህጋዊ እርድ እንዲፈፀም የማድረግ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልፀው ደንቡን በሚተላለፉት ላይ አስተማሪ እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል።
አክለውም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ስራዎች ለመስራት ከበጎ ፈቃደኞች እገዛ አይነተኛውን ሚና እንደሚጫዎት እና በጎ ፈቃደኞች በደንቡ ላይ ግንዛቤ አግኝተው በሚኖሩበት አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ደንቡን እንዲያስገነዝቡ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጥ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደመረ በለጠ አማካኝነት በቀረበ ሰነድ የአዲስ አበባ ከተማ ወንዞች ብክለት፣ በአካባቢ እና በጤና ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ፣ መፍትሔዎች እንዲሁም የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 እና የቅጣት ሰንጠረዥ በዝርዝር ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል ደንቡን በተላለፉ ድርጅት እና ግለሰብ ለይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር እስከ ከፍተኛው አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚያስቀጣ ገልፀዋል።
የባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን በደንቡ ዙሪያ በተለያዩ አግባቦች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በተደጋጋሚ መሰጠቱን እና ግንዛቤ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋረ ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
April 26
April 26