የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
996 subscribers
1.5K photos
4 videos
1 file
51 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀሙ ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ

15/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም የባለስልጣኑ አመራሮችና የማዕከል ዳይሬክተሮች በተገኙበት ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ ።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በዘጠኝ ወራት በነበረን አፈፃፀም የታዩ ጥንካሬዎች በማስቀጠል ክፍተቶችን በመለየት በበጀት በቀሪ ቀጣይ ወራቶች የመፈጸምና የማስፈፀም አቅምን በማጎልበት ውጤታማ ተግባር ማከናወን ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።

በሪፖርቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የደመወዝ ልዮነትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች መስተካከል መቻሉ፣በርካታ የተቋም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸው ፣ የባለስልጣኑ የራሱን ስቲዲዮ በመገንባት ለቀጣይ ስራዎች ዝድጁ ማድረግ መቻሉ ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዋል፡፡

ባለስልጣኑ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን መቻሉ ጠቅሰው በተለይ አስራ አራት የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ ማስረከቡ በሪፖርቱ ተገልጿል ።

በወንዝና በወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችና እና የተወሰዱ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ቀርባል።

የባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በመድረኩ ማጠቃለያ ባደረጉት ንግግር አፈፃፀሙ ከባለፈው አመት አንፃር በጣም የተሻለ በመሆኑ የተቋሞ ግንባታ ላይ የተሰሩ ሰራዎች ለአቻ ተቋማት ተሞክሮ እንደሆኑ ገልፀው ለቀጣይ ቀሪ ወራቶች የታቀዱት ተግባራት እንዲሳኩ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ባለስልጣኑ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት የተሰሩ ስራዎችን ገመገመ

16/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ቅንጅታዊ ስራዎችን ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ የባለስልጣኑ ኃላፊዎች በተገኙበት ከባለድርሻ አካላት አመራሮች ጋር በጋራ የግምገማ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በዘጠኝ ወራት ከባለድርሻ አካላት ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት የሰራቸውን ስራዎች በወቅቱ በመገምገም ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀሪ ጊዜያት የአመቱን እቅድ ለማሳካት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ስራዎችን በጋራ መገምገም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።

ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የከተማችንና የአከባቢያችንን ውበት ማስጠበቅ ፣ የወንዝና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከላከል ፣ የከተማችን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ ፣ ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰትን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ተቀናጅቶ በመስራት ውጤታማ መሆን መቻሉን ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።

የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በዘጠኝ ወራት በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች በጥንካሬ እና በጉድለት በሰነድ ተለይተው በባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል ።

የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በማጠናከር ወደ ቅጣት ከመገባቱ በፊት ለህብረተሰቡ ስለ ደንብ ማስከበር በቂ እውቀት በማስገንዘብ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ቅንጅት በማጠናከር ከተማችን እንደ ስሟ አዲስና ውብ ለነዋሪዎች ምቹ ለቱሪስት መስብ እንድትሆን በትጋት መስራት እንደሚገባ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ተናግረዋል ።

ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በርካታ ስኬታማ ተግባራትን በማከናወንና የገጽታ ግንባታ ስራን አጠናክሮ በመስራቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰቶች እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ገልጸዋል ።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረክ መሪዎች ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
የደንብ ማስከበር ሰራተኞች ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ተገለፀ

ሚያዚያ 17-2017ዓም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ለክፍለ ከተማው ሁሉም ወረዳዎች ለሚገኙ ከ650 በላይ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በስነምግባር እና ፀረ-ሙስና ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

በስልጠናው መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ቅርንጯፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በጥሩ ስነ-ምግባር ታንፀው የደንብ መተላለፎችን ለማስቀረት አያደረጉት ያለው ጥረት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ሰራተኞቹ የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ባለፈ በከተማዋ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ በበኩላቸው የዘርፉ ሰራተኞች ጥሩ ስነ-ምግባርን ተላብሰው ከፀረሙስና የፀዳ አገልግሎት በመስጠት ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡

ሰልጣኞች በበኩላቸው ከብልሹ አሰራር የፀዳና ደንብና መመሪያ መሰረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠናው ከፍተኛ አስተዎፅኦ እንዳለው ተናግረዋል::