የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
995 subscribers
1.5K photos
4 videos
1 file
51 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፅ/ቤት አመራሮችና ሰራተኞች በማስተባበር የዝቅተኛ ደምወዝ ተከፋይ ሰራተኛ ቤት ሙሉ እድሳት አደረገ

ሚያዝያ 09/2017 ዓ. ም
** በአዲስ አበባ**

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የለሚ ኩራ ክ/ከተማ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር እና የሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት በማስተባበር ለአንድ ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ሰራተኛና ሙሉ የቤት ዕድሳት በማድረግ ለፋሲካ በአል ቤቱን አስረክቧል።

በርክክቡ ስነስርዓት ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘርሁን ተፈራ ባስተላለፉት መልዕክት ሁሉም ሰው ከሚያሰራው ሰራተኛ ጀምሮ ያለበትን የኑሮ ደረጃ በማየትና በመለየት መተጋገዝ፣ አብሮ መቆምና መመረዳዳት እንዳለበት አንስተው ወጣት እሸቱ የነበረበት የኑሮ ሁኔታ ከባድ እንደነበር በማየት እንደዚህ አይነት እገዛ እንዲደረግለት የተባበሩ አካላትን አመስግነዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ በበኩላቸው የፓርቲያችን ብልጽግና ሀሳብ እና የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶክተር አብይ አህመድ መልካም ጅምር የሆነውን እንደዚህ አይነት ሰዉ ተኮር ተግባር በመስራት ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ላይ ለመሰማራት እድል በማግኘታቸው እንደተደሰቱ በማንሳት እንደዚህ አይነት ተግባር በሁሉም መለመድ እንዳለበት ተናግሯል።

በመጨረሻም ቤት የታደሰለት ወጣት እሸቱ መሐመድ የቤት እድሳቱን ላስተባበሩ ሁሉ እና ስጦታ ስለተበረከተላቸው ምስጋና አቅርቧል።
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ለ2017 ዓ.ም ለትንሳኤ በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!
*******

ለመላው ኢትዮጵያውያንና ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!

የትንሳኤ በዓል የሰላም ፣የጤና ፣ የደስታ ፣ የፍቅር እና የመረዳዳት በዓል እንደሆንልን እመኛለሁ።

የትንሳኤ በዓል እየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ለሰዉ ልጆች ሁሉ ምህረት ያስገኘበት ለሰው ልጆች መስዋትነት የተከፈለበት በዓል ነው።

በዓሉን ስናከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት፣ በመተዛዘን ካለን በማካፈል በዓሉን በአብሮነት ልናከብር ይገባል ።

ባለስልጣኑ በከተማዋ የሚስተዋለውን የደንብ መተላለፎችና ህገ-ወጥነትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚያደርገው ጥረት ህብረተሰቡ አጋዥ በመሆን የበኩሉን እንዲወጣ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

መልካም የትንሳኤ በዓል!!!

ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ
ባለስልጣኑ በተሰጠው ሀላፊነት መሠረት የከተማው ኮሪደር መሠረተ-ልማት ጥበቃው አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ

12/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ አበባ ከተማ በሚሠራው የልማት ኮሪደር መሰረተ ልማቶችና በመሰራት ላይ ያለው ሥራ የጥበቃ ሥራው አጠናክሮ እንደሚሠራ አስታወቀ ።

ባለስልጣኑ በዛሬው በትንሳኤ በዓል እለት ከ11ዱም ክ/ከተማ የተውጣጡ 2400 የደንብ ማስከበር አመራሮችና ኦፍሠሮች በማሳተፍ በቂርቆስ፣በየካና በአራዳ ክፍለ ከተሞች የጽዳት ዘመቻ አከናውኗል።

በጽዳት ዘመቻው በካሳንቺስ የልማት ኮሪደር ካሳንቺስ፣ ሴቶች አደባባይ ፣መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን፣ አዋሬ፣ ግቢ ገብርኤል አካባቢ ተካሂዷል።

ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 መሰረት በኮሪደር ልማት ጥበቃ ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ አስተማሪ እርምጃዎች መውሰዱን አስታውቋል።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በበዓል ቤተሰባቸውን ጥለው በተሰጣቸው ሀላፊነት መሠረት በጽዳት ዘመቻው የተሳተፉ አመራሮችና ኦፍሠሮች ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

አክለውም የከተማው የኮሪደር መሠረተ-ልማት ጥበቃው አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀሙ ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ

15/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም የባለስልጣኑ አመራሮችና የማዕከል ዳይሬክተሮች በተገኙበት ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ ።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በዘጠኝ ወራት በነበረን አፈፃፀም የታዩ ጥንካሬዎች በማስቀጠል ክፍተቶችን በመለየት በበጀት በቀሪ ቀጣይ ወራቶች የመፈጸምና የማስፈፀም አቅምን በማጎልበት ውጤታማ ተግባር ማከናወን ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።

በሪፖርቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የደመወዝ ልዮነትና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች መስተካከል መቻሉ፣በርካታ የተቋም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸው ፣ የባለስልጣኑ የራሱን ስቲዲዮ በመገንባት ለቀጣይ ስራዎች ዝድጁ ማድረግ መቻሉ ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዋል፡፡

ባለስልጣኑ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድና ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን መቻሉ ጠቅሰው በተለይ አስራ አራት የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ ማስረከቡ በሪፖርቱ ተገልጿል ።

በወንዝና በወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችና እና የተወሰዱ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ቀርባል።

የባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በመድረኩ ማጠቃለያ ባደረጉት ንግግር አፈፃፀሙ ከባለፈው አመት አንፃር በጣም የተሻለ በመሆኑ የተቋሞ ግንባታ ላይ የተሰሩ ሰራዎች ለአቻ ተቋማት ተሞክሮ እንደሆኑ ገልፀው ለቀጣይ ቀሪ ወራቶች የታቀዱት ተግባራት እንዲሳኩ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡