ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአቅመ ደካማ ቤት በትንሣኤ ዋዜማ እርክብክብ ተካሄደ።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወረዳ 14 ቱሉ አጀርሳ አከባቢ ቤት ገንብቶ ለአርሶ አደር ወ/ሮ ቀጨኔ ሰንበቶ አስረከበ።
በክፍለ ከተማው ስር የሚገኙትን አስራ ሶስት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎችን በማስተባበር በ120 ቀናት ውስጥ የሰው ተኮር ስራውን ማከናወን ተችሏል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስከያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባለስልጣኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ተልዕኮውን ከመወጣት ባሻገር ባለፉት 9ኝ ወራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 14 ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉን አስታውሰው ፤በቀጣይም ሌሎች ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሮ ካባ መብራቱ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደንብ መተላለፍችን ከመከላከል ጎን ለጎን ሙሉ ሠራዊቱን በማስተባበር ይህን የመሰለ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለሚያደርገው አስተዋጽኦ በክፍለ ከተማው ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በመርኃ ግብሩ ተገኝተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ግንባር ቀደም ሆኖ የሚያበረክተው ሰው ተኮሮ ስራዎች የሚደነቁና በጎነትን የሚያፀኑ መሆናቸውን በአፅንኦት ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት የኦፊሰሩን ስነ-መሃንዲሶች እና የአስራ ሶስቱንም ወረዳ ኃላፊና ኦፊሰሮች አሻራ ጥረት ውጤት መሆኑን እና ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ለአርሶ አደር ቀጨኔ የአውደ ዓመት ማዕድ አጋርተዋል።
በተያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብሄረፅጌ አከባበ ከ500ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የ2 አቅመ ደካሞች ቤቶቾን ገንብቶ ማስረከብ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህ ሰውተኮር በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጽ/ቤት ኃላፊው መቶ አለቃ ቦጋለ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በግንባታ ሂደቱ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅ ተሰጥቷል።
ዘገባባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወረዳ 14 ቱሉ አጀርሳ አከባቢ ቤት ገንብቶ ለአርሶ አደር ወ/ሮ ቀጨኔ ሰንበቶ አስረከበ።
በክፍለ ከተማው ስር የሚገኙትን አስራ ሶስት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎችን በማስተባበር በ120 ቀናት ውስጥ የሰው ተኮር ስራውን ማከናወን ተችሏል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስከያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባለስልጣኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ተልዕኮውን ከመወጣት ባሻገር ባለፉት 9ኝ ወራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 14 ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉን አስታውሰው ፤በቀጣይም ሌሎች ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሮ ካባ መብራቱ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደንብ መተላለፍችን ከመከላከል ጎን ለጎን ሙሉ ሠራዊቱን በማስተባበር ይህን የመሰለ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለሚያደርገው አስተዋጽኦ በክፍለ ከተማው ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በመርኃ ግብሩ ተገኝተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ግንባር ቀደም ሆኖ የሚያበረክተው ሰው ተኮሮ ስራዎች የሚደነቁና በጎነትን የሚያፀኑ መሆናቸውን በአፅንኦት ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት የኦፊሰሩን ስነ-መሃንዲሶች እና የአስራ ሶስቱንም ወረዳ ኃላፊና ኦፊሰሮች አሻራ ጥረት ውጤት መሆኑን እና ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ለአርሶ አደር ቀጨኔ የአውደ ዓመት ማዕድ አጋርተዋል።
በተያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብሄረፅጌ አከባበ ከ500ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የ2 አቅመ ደካሞች ቤቶቾን ገንብቶ ማስረከብ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህ ሰውተኮር በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጽ/ቤት ኃላፊው መቶ አለቃ ቦጋለ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በግንባታ ሂደቱ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅ ተሰጥቷል።
ዘገባባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ በመንገድ ሽንት በመሽናት ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ ግለሰቦች 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ሽንት በመሽናት አካባቢ በማቆሸሽ ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እየዳዳቸው 2000 ብር በድምሩ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልፃል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ሽንት በመሽናት አካባቢ በማቆሸሽ ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እየዳዳቸው 2000 ብር በድምሩ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልፃል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
በከተማዋ በ64% የደንብ መተላለፎች እንዲቀንስ ማድረግ መቻሉ ተገለፀ
ሚያዚያ 08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማ እና ከወረዳ አመራሮች ጋር በሳሬም ሆቴል የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ ከተማችን እንደ ስሟ አዲስ ውብ ለነዋሪዎቿ ምቹ የቱሪስት መስህብ እንድትሆን እየሰራ መሆኑ ገልፀዋል።
አያይዘውም በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከል ደንብ በማስከበርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በከተማችን የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች በ64% እንዲቀንስ ማድረግ መቻሉንና በሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ ከ የ14 የአቅመ ደካማ ቤት እድሳትና ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ ማስረከቡን ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል።
በሪፖርቱ ታቅደው የተፈጸሙ ክንውኖች ፣ በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተወሰዱ መፍትሔዎች ተገልፃል።
በ9 ወሩ ከደንብ ተላላፊዎች ቅጣት እና ከተወረሱ ንብረቶች ጨረታ ሽያጭ ከ290 ሚሊዮን ብር በላይ ለከተማው ገቢ ማስገባት መቻሉን በሪፖርቱ ተገልጿል ።
በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጁ አቶ ንጋቱ ደኛቸው እና ም/ስራ አስኪያጁ ከፍያለው ታደሰ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የማጠቃለያ ንግግርና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በዋና ሰራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ሚያዚያ 08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማ እና ከወረዳ አመራሮች ጋር በሳሬም ሆቴል የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ ከተማችን እንደ ስሟ አዲስ ውብ ለነዋሪዎቿ ምቹ የቱሪስት መስህብ እንድትሆን እየሰራ መሆኑ ገልፀዋል።
አያይዘውም በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከል ደንብ በማስከበርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በከተማችን የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች በ64% እንዲቀንስ ማድረግ መቻሉንና በሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ ከ የ14 የአቅመ ደካማ ቤት እድሳትና ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ ማስረከቡን ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል።
በሪፖርቱ ታቅደው የተፈጸሙ ክንውኖች ፣ በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተወሰዱ መፍትሔዎች ተገልፃል።
በ9 ወሩ ከደንብ ተላላፊዎች ቅጣት እና ከተወረሱ ንብረቶች ጨረታ ሽያጭ ከ290 ሚሊዮን ብር በላይ ለከተማው ገቢ ማስገባት መቻሉን በሪፖርቱ ተገልጿል ።
በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጁ አቶ ንጋቱ ደኛቸው እና ም/ስራ አስኪያጁ ከፍያለው ታደሰ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የማጠቃለያ ንግግርና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በዋና ሰራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡