በባለፈው አንድ ወር በወንዞችና የወንዝ ዳርቻ ብክለት መከላከል ላይ የተሰሩ ስራዎች ተገመገሙ።
03/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በጋራ በመሆን በወንዝ እና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ከየካቲት 24 እስከ ሚያዝያ 02/2017 ዓ.ም ድረስ የተሰሩ ስራዎች የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት ሪፓርት ሪፓርቱ ቀርቦ ተገምግሟል።
በግምገማው ላይ ንግግር ያደረጉት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቅንጅት የመስራት ሂደቱ ያመጣው ውጤት መልካም መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም 2,858 የሚሆኑ የብክለት ድርጊቶች ከሚፅሙት ወንጀል መታቀብ በመቻላቸው ይበል የሚያሰኝ ከፍተኛ ለውጥ መሆኑን እና የሚለቀቁ ፍሳሾች የጉዳት መጠን በላቭራቶሪ በመመርመር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የተሰሩ ተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የግንዛቤ ቡድን መሪ አቶ አንበሳው ፈንታ ቀርቧል።
በሪፖርቱም በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ 2,354,443 የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ መፈጠረ መቻሉን፣2,858 ከሚፈፅሙት ወንጀል ማስተካከያ መደረጉ እና ህግን ተላልፈው በተገኙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 68,896,000 (ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ብር ) የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል።
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በአሰራር ላይ ያጋጠሙ አጠቃላይ ሂደቶች በክፍተት በታዩ እና በቀጣይም መስተካከል የሚገባቸው አሰራሮች ላይ ከቤቱ ሀሳቦች ተንሸራሸረዋል። በዚህም የተለያዩ አስተያየት እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ምክክር ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በበኩላቸው የስራ አፈፃፀሙ በጣም ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም ሊመጣ የቻለው በቅንጅት በመግባባት ስራዎች በመሰራታቸው በመሆኑ ከቀሩ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት ይበልጥ ለውጥ እንደሚያመጣ ጠቁመዋል።
የአዲስ አበባ ወንዞች ሲፀዱ እኔም ተሳታፊ ነበርኩ የሚል ታሪክ ነጋሪ ለመሆን ወንዞች በዋናነት የሚበክሉት በማን ነው የሚለውን በማየት በቁርጠኝነት ስራዎች በጋራ እንስራ ያሉት ደግሞ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ናቸው።
በመጨረሻም በተቋማቱ የበላይ አመራሮች የቀጣይ የአሰራር አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
03/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በጋራ በመሆን በወንዝ እና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ከየካቲት 24 እስከ ሚያዝያ 02/2017 ዓ.ም ድረስ የተሰሩ ስራዎች የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት ሪፓርት ሪፓርቱ ቀርቦ ተገምግሟል።
በግምገማው ላይ ንግግር ያደረጉት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቅንጅት የመስራት ሂደቱ ያመጣው ውጤት መልካም መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም 2,858 የሚሆኑ የብክለት ድርጊቶች ከሚፅሙት ወንጀል መታቀብ በመቻላቸው ይበል የሚያሰኝ ከፍተኛ ለውጥ መሆኑን እና የሚለቀቁ ፍሳሾች የጉዳት መጠን በላቭራቶሪ በመመርመር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ የተሰሩ ተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የግንዛቤ ቡድን መሪ አቶ አንበሳው ፈንታ ቀርቧል።
በሪፖርቱም በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ 2,354,443 የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ መፈጠረ መቻሉን፣2,858 ከሚፈፅሙት ወንጀል ማስተካከያ መደረጉ እና ህግን ተላልፈው በተገኙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 68,896,000 (ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ብር ) የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል።
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በአሰራር ላይ ያጋጠሙ አጠቃላይ ሂደቶች በክፍተት በታዩ እና በቀጣይም መስተካከል የሚገባቸው አሰራሮች ላይ ከቤቱ ሀሳቦች ተንሸራሸረዋል። በዚህም የተለያዩ አስተያየት እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ምክክር ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ በበኩላቸው የስራ አፈፃፀሙ በጣም ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም ሊመጣ የቻለው በቅንጅት በመግባባት ስራዎች በመሰራታቸው በመሆኑ ከቀሩ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት ይበልጥ ለውጥ እንደሚያመጣ ጠቁመዋል።
የአዲስ አበባ ወንዞች ሲፀዱ እኔም ተሳታፊ ነበርኩ የሚል ታሪክ ነጋሪ ለመሆን ወንዞች በዋናነት የሚበክሉት በማን ነው የሚለውን በማየት በቁርጠኝነት ስራዎች በጋራ እንስራ ያሉት ደግሞ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ናቸው።
በመጨረሻም በተቋማቱ የበላይ አመራሮች የቀጣይ የአሰራር አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአቅመ ደካማ ቤት በትንሣኤ ዋዜማ እርክብክብ ተካሄደ።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወረዳ 14 ቱሉ አጀርሳ አከባቢ ቤት ገንብቶ ለአርሶ አደር ወ/ሮ ቀጨኔ ሰንበቶ አስረከበ።
በክፍለ ከተማው ስር የሚገኙትን አስራ ሶስት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎችን በማስተባበር በ120 ቀናት ውስጥ የሰው ተኮር ስራውን ማከናወን ተችሏል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስከያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባለስልጣኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ተልዕኮውን ከመወጣት ባሻገር ባለፉት 9ኝ ወራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 14 ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉን አስታውሰው ፤በቀጣይም ሌሎች ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሮ ካባ መብራቱ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደንብ መተላለፍችን ከመከላከል ጎን ለጎን ሙሉ ሠራዊቱን በማስተባበር ይህን የመሰለ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለሚያደርገው አስተዋጽኦ በክፍለ ከተማው ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በመርኃ ግብሩ ተገኝተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ግንባር ቀደም ሆኖ የሚያበረክተው ሰው ተኮሮ ስራዎች የሚደነቁና በጎነትን የሚያፀኑ መሆናቸውን በአፅንኦት ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት የኦፊሰሩን ስነ-መሃንዲሶች እና የአስራ ሶስቱንም ወረዳ ኃላፊና ኦፊሰሮች አሻራ ጥረት ውጤት መሆኑን እና ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ለአርሶ አደር ቀጨኔ የአውደ ዓመት ማዕድ አጋርተዋል።
በተያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብሄረፅጌ አከባበ ከ500ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የ2 አቅመ ደካሞች ቤቶቾን ገንብቶ ማስረከብ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህ ሰውተኮር በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጽ/ቤት ኃላፊው መቶ አለቃ ቦጋለ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በግንባታ ሂደቱ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅ ተሰጥቷል።
ዘገባባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በወረዳ 14 ቱሉ አጀርሳ አከባቢ ቤት ገንብቶ ለአርሶ አደር ወ/ሮ ቀጨኔ ሰንበቶ አስረከበ።
በክፍለ ከተማው ስር የሚገኙትን አስራ ሶስት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ወረዳዎችን በማስተባበር በ120 ቀናት ውስጥ የሰው ተኮር ስራውን ማከናወን ተችሏል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስከያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባለስልጣኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ተልዕኮውን ከመወጣት ባሻገር ባለፉት 9ኝ ወራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 14 ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉን አስታውሰው ፤በቀጣይም ሌሎች ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወሮ ካባ መብራቱ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የደንብ መተላለፍችን ከመከላከል ጎን ለጎን ሙሉ ሠራዊቱን በማስተባበር ይህን የመሰለ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ለሚያደርገው አስተዋጽኦ በክፍለ ከተማው ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በመርኃ ግብሩ ተገኝተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማዎች ግንባር ቀደም ሆኖ የሚያበረክተው ሰው ተኮሮ ስራዎች የሚደነቁና በጎነትን የሚያፀኑ መሆናቸውን በአፅንኦት ገልፀዋል።
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት የኦፊሰሩን ስነ-መሃንዲሶች እና የአስራ ሶስቱንም ወረዳ ኃላፊና ኦፊሰሮች አሻራ ጥረት ውጤት መሆኑን እና ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ለአርሶ አደር ቀጨኔ የአውደ ዓመት ማዕድ አጋርተዋል።
በተያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብሄረፅጌ አከባበ ከ500ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የ2 አቅመ ደካሞች ቤቶቾን ገንብቶ ማስረከብ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህ ሰውተኮር በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጽ/ቤት ኃላፊው መቶ አለቃ ቦጋለ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በግንባታ ሂደቱ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅ ተሰጥቷል።
ዘገባባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ በመንገድ ሽንት በመሽናት ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ ግለሰቦች 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ሽንት በመሽናት አካባቢ በማቆሸሽ ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እየዳዳቸው 2000 ብር በድምሩ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልፃል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
07/08/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ሽንት በመሽናት አካባቢ በማቆሸሽ ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እየዳዳቸው 2000 ብር በድምሩ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልፃል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።