ባለስልጣኑ የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ
08-07 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ባደረገው ጠንካራ ክትትል መሠረት የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ ።
በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መዝገቡ ዲማ እንደገለፁት በግለሰብ ግቢ ውስጥ መሸሸጊያ በማድረግ ተከማችተው የተቀመጡ በርካታ ህገወጥ የንግድ እቃዎችን በደንብ ማስከበር ፅ/ቤት በግብረሀይል በመውረስ በግምት ከ400,000/ አራት መቶ ሺህ/ ብር በላይ የሚገመቱ እቃዎቾ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል ።
ባለስልጣኑ ህገወጥነትን እደማይታገስና በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንደሚገባቸውና ወደ ህጋዊ መንገድ እንዲገቡ አሳስቧል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
08-07 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ባደረገው ጠንካራ ክትትል መሠረት የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ ።
በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መዝገቡ ዲማ እንደገለፁት በግለሰብ ግቢ ውስጥ መሸሸጊያ በማድረግ ተከማችተው የተቀመጡ በርካታ ህገወጥ የንግድ እቃዎችን በደንብ ማስከበር ፅ/ቤት በግብረሀይል በመውረስ በግምት ከ400,000/ አራት መቶ ሺህ/ ብር በላይ የሚገመቱ እቃዎቾ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል ።
ባለስልጣኑ ህገወጥነትን እደማይታገስና በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንደሚገባቸውና ወደ ህጋዊ መንገድ እንዲገቡ አሳስቧል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍5
የ6ተኛ ዙር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የንድፈ ሃሳብ ትምህርት የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ተጀመረ።
09/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቀጣይ ለሚሰጠው እጩ የ6ኛ ዙር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና የባለድርሻ አካላት ደንብ፣ መመሪያና አሠራርን የተመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የአሠልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ።
በስልጠናው መነሻ ላይ ተገኝተው የስልጠናውን ዓላማ እና ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ እንዲከታተሉ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የባለስልጣኑ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ እና የደንብ መተላለፍ፣ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ናቸው።
ከማዕከሉና ከአስራ አንዱም ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ ሰልጥኖ አሰልጣኞች ስልጠናውን የሚሰጡት ባድርሻ ተቋም ከሆኑት ከግንባታ ፍቃድ፣ መሬት አስተዳደር ፣ ከተማ ግብርና፣ ቄራዎች ድርጅት፣ አከባቢ ጥበቃ፣ ውኃና ፍሳሽ፣ ፅዳት አስተዳደር፣ ትራፊክ ማናጅመንት፣ ንግድ ቢሮ እና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን የመጡ አሰልጣኞች ሲሆኑ ስልጠናውም በማዕከሉ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት የግንባታ ፍቃድ፣ መሬት አስተዳደር፣ ቄራዎች ድርጅት እና ከተማ ግብርና ደንብ፣ መመሪያዎችና አሰራሮች በዝርዝር ቀርቧል።
ስልጠናው ለቀጣይ ሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞችም በዲስፕሊንና በመልካም ተሳትፎ እየተከታተሉ መሆኑን ተመልክተናል።
ዘገባው:- የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
09/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቀጣይ ለሚሰጠው እጩ የ6ኛ ዙር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና የባለድርሻ አካላት ደንብ፣ መመሪያና አሠራርን የተመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የአሠልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ።
በስልጠናው መነሻ ላይ ተገኝተው የስልጠናውን ዓላማ እና ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ እንዲከታተሉ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የባለስልጣኑ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ እና የደንብ መተላለፍ፣ መከላከልና ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታሁን ናቸው።
ከማዕከሉና ከአስራ አንዱም ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ ሰልጥኖ አሰልጣኞች ስልጠናውን የሚሰጡት ባድርሻ ተቋም ከሆኑት ከግንባታ ፍቃድ፣ መሬት አስተዳደር ፣ ከተማ ግብርና፣ ቄራዎች ድርጅት፣ አከባቢ ጥበቃ፣ ውኃና ፍሳሽ፣ ፅዳት አስተዳደር፣ ትራፊክ ማናጅመንት፣ ንግድ ቢሮ እና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን የመጡ አሰልጣኞች ሲሆኑ ስልጠናውም በማዕከሉ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት የግንባታ ፍቃድ፣ መሬት አስተዳደር፣ ቄራዎች ድርጅት እና ከተማ ግብርና ደንብ፣ መመሪያዎችና አሰራሮች በዝርዝር ቀርቧል።
ስልጠናው ለቀጣይ ሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞችም በዲስፕሊንና በመልካም ተሳትፎ እየተከታተሉ መሆኑን ተመልክተናል።
ዘገባው:- የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍5
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት ወንዝን የበከሉ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 8,815,000/ ስምንት ሚሊየን ስምንት መቶ አስራ አምስት ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
09/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 8,815,000/ ስምንት ሚሊየን ስምንት መቶ አስራ አምስት ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 2,250,000 ብር፤በየካ ክፍለ ከተማ 1,800,000 ብር ፤በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 1,415,000 ብር፤በለሚ ኩራ ክ/ከተማ 1,300,000 ብር ቅጣት ተቀጥተዋል።
በያያዘ ዜና በቦሌ ክፍለ ከተማ 1,150,000 ብር ፤በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 700,000 ብር እና በልደታ ክ/ከተማ 200,000 ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል።
በአጠቃላይ በዛሬው እለት 26 ድርጅት እና
5 ግለሰቦች በድምሩ 8,815,000/ ስምንት ሚሊየን ስምንት መቶ አስራ አምስት ሺህ/ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ በሚበክሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
09/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 8,815,000/ ስምንት ሚሊየን ስምንት መቶ አስራ አምስት ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 2,250,000 ብር፤በየካ ክፍለ ከተማ 1,800,000 ብር ፤በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 1,415,000 ብር፤በለሚ ኩራ ክ/ከተማ 1,300,000 ብር ቅጣት ተቀጥተዋል።
በያያዘ ዜና በቦሌ ክፍለ ከተማ 1,150,000 ብር ፤በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 700,000 ብር እና በልደታ ክ/ከተማ 200,000 ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል።
በአጠቃላይ በዛሬው እለት 26 ድርጅት እና
5 ግለሰቦች በድምሩ 8,815,000/ ስምንት ሚሊየን ስምንት መቶ አስራ አምስት ሺህ/ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ በሚበክሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👏15👍6❤1