ፕሬስ ሪሊዝ
የወንዝ ዳርቻ ልማትን ከብክለት በሚከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ ሊሰጥ ነው።
19/06/2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል" በሚል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ነገ ሀሙስ በ20/06/2017 ዓ.ም ጉርድ ሾላ በሚገኘው አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ቢሮ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ግንዛቤ እንሚፈጠር የባለስልጣኑ ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ አስታወቁ።
በግንዛቤ ስልጠናው ላይ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቅድመ መከላከልና መስክ ክትትል፣ ቁጥጥር ኦፊሰሮች የባለስልጣኑ ባለሙያዎች፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ስልጠናው ተሳታፊዎች እንደሚሆኑ አቶ የምስራች ገልፀዋል።
በቀጣይም ለከተማው ህብረተሰብ፣ ለባለድርሻ አካላት፣ ለአደረጃጀቶችና በጎ ፈቃደኞች ስለ ደንቡ ግንዛቤዎች በስፋት እንደሚፈጠር ጠቁመዋል።
ጥቆማው ፦ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
የወንዝ ዳርቻ ልማትን ከብክለት በሚከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ ሊሰጥ ነው።
19/06/2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል" በሚል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ነገ ሀሙስ በ20/06/2017 ዓ.ም ጉርድ ሾላ በሚገኘው አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ቢሮ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ግንዛቤ እንሚፈጠር የባለስልጣኑ ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ አስታወቁ።
በግንዛቤ ስልጠናው ላይ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቅድመ መከላከልና መስክ ክትትል፣ ቁጥጥር ኦፊሰሮች የባለስልጣኑ ባለሙያዎች፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ስልጠናው ተሳታፊዎች እንደሚሆኑ አቶ የምስራች ገልፀዋል።
በቀጣይም ለከተማው ህብረተሰብ፣ ለባለድርሻ አካላት፣ ለአደረጃጀቶችና በጎ ፈቃደኞች ስለ ደንቡ ግንዛቤዎች በስፋት እንደሚፈጠር ጠቁመዋል።
ጥቆማው ፦ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍11
ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የካቲት 19/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በስነ-ምግባር፣ ፀረ-ሙስና እና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው በሙስና መከላከል ስነ- ምግባራዊ አመራር፣ በጥቅም ግጭት እና አስቸኳይ ሙስና መከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራር ዙሪያ ሲሆን በፀረ-ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የቀጣይ እቅዶችን ዙሪያ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ተቋሙ በሰጠው ስልጠናና ግንዛቤ መሠረት በቀጣይ የስነ-ምግባር ችግር በሚታይባቸው ሰራተኞች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በስልጠናው የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቶ እንደተናገሩት ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር ማድረስ እንዳለበት ገልጸዋል።
አክለውም ኦፊሰሩ ሙስናን በመከላከል በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው በመግለጽ ኦፊሰሩ በሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እውቀት በመጨመር ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።
በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ባለሙያ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
የካቲት 19/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በስነ-ምግባር፣ ፀረ-ሙስና እና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው በሙስና መከላከል ስነ- ምግባራዊ አመራር፣ በጥቅም ግጭት እና አስቸኳይ ሙስና መከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራር ዙሪያ ሲሆን በፀረ-ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የቀጣይ እቅዶችን ዙሪያ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ተቋሙ በሰጠው ስልጠናና ግንዛቤ መሠረት በቀጣይ የስነ-ምግባር ችግር በሚታይባቸው ሰራተኞች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በስልጠናው የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቶ እንደተናገሩት ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር ማድረስ እንዳለበት ገልጸዋል።
አክለውም ኦፊሰሩ ሙስናን በመከላከል በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው በመግለጽ ኦፊሰሩ በሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እውቀት በመጨመር ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።
በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ባለሙያ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
👍3
የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል በወጣዉ ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ ተፈጠረ።
20/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና ከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በመተባበር
የወንዞች ዳርቻ ልማትን እና ብክለት ለመከላከል
በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ በየደረጃው ለሚገኙ የተቋማቱ አመራሮች፣ አስተባባሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት በባለስልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አካሄደ።
የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ አዲስ አበባ ከተማ የአፍሪካ ከተሞች መዲና እንደመሆንዋ ስሟን የሚመጥን ንጹህ ወንዝ ጤናማ ህይወት የተላበሰች ከተማ ለማድረግ ትልቅ ተልዕኮን አንግቦ በመስራት ላይ ይገኛል ያሉት ኃላፊዉ ልማት ከአካባቢ ጥበቃ ጋር ይዋሀድ ዘንድ የወንዞች ዳርቻ ልማትን እና ብክለት ለመከላከል ለመጠበቅ ደንቡ መውጣቱን ገልጸዋል።
የከተማዋን የወንዞች ዳርቻ ማልማት፣ መንከባከብ እና ከብክለት የጸዳ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መስራት ከሁሉም ባለድርሻ አካል የሚጠበቅ መሆኑን በማንሳት ለዚህም ይረዳ ዘንድ በቀጣይ ለከተማው ህብረተሰብ ፣ባለድርሻ አካላትና አደረጃጀቶች ስለ ደንቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች በስፋት እንደሚያዘጋጅ በመግለጽ መድረኩን በይፋ አስጀምረዋል።
በመድረኩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በወንዞች ዳርቻ ዙርያ ሰፊ ጥናቶችን በማጥናት ለማስተዳደር አመቺ እንዲሆን ደንቡን በማጸደቅ ተግባራዊነቱን ለማስጠበቅ በጋራ ለመስራት ሂደቱ መጀመሩን በማንሳት የከተማዋን የወንዝ ተፋሰስ ፅዱ፣ ውብ እና ምቹ ሆነው አገልግሎት ላይ እንዲውሉ በየደረጃው ላሉ አካላት ግንዛቤ መፍጠር ተቀዳሚ ተግባር እንደሚሆን ገልጸዋል።
በመቀጠልም የአዲስ አበባ ወንዞች ብክለት የሚገኙበትን ደረጃ እንዲሁም ደንቡ የወጣበት ምክንያት እና ደንብ ቁጥር 180/2017 ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
በመጨረሻም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ወንዞቻችን የብክለት ምክንያት ሳይሆኑ የኢኮኖሚያችን ምንጭ እንዲሆን ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በበቂ መንገድ በመፍጠር ለህጉ ተገዢ ባልሆኑ አካላት ላይ እርምጃዎችን በመውሰድ ደንብ የማስከበር ተልዕኮውን ተግባራዊ እንደሚደረግ አስገንዝበዋል።
የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉቀን ዮናስ እንዳሉት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የወንዝ ዳርቻዎችን በማልማት ከተማዋን አለም አቀፍ ደረጃዎች ያሟላች ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የግንዛቤ ስልጠናው በነገው እለትም ለፈፃሚ አካላቱ ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በቀጣይም እስከ ህብረተሰቡ ድረስ በየደረጃው እንደሚወርድ ተገልጿል።
ዘገባው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
20/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና ከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በመተባበር
የወንዞች ዳርቻ ልማትን እና ብክለት ለመከላከል
በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ በየደረጃው ለሚገኙ የተቋማቱ አመራሮች፣ አስተባባሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት በባለስልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አካሄደ።
የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ አዲስ አበባ ከተማ የአፍሪካ ከተሞች መዲና እንደመሆንዋ ስሟን የሚመጥን ንጹህ ወንዝ ጤናማ ህይወት የተላበሰች ከተማ ለማድረግ ትልቅ ተልዕኮን አንግቦ በመስራት ላይ ይገኛል ያሉት ኃላፊዉ ልማት ከአካባቢ ጥበቃ ጋር ይዋሀድ ዘንድ የወንዞች ዳርቻ ልማትን እና ብክለት ለመከላከል ለመጠበቅ ደንቡ መውጣቱን ገልጸዋል።
የከተማዋን የወንዞች ዳርቻ ማልማት፣ መንከባከብ እና ከብክለት የጸዳ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መስራት ከሁሉም ባለድርሻ አካል የሚጠበቅ መሆኑን በማንሳት ለዚህም ይረዳ ዘንድ በቀጣይ ለከተማው ህብረተሰብ ፣ባለድርሻ አካላትና አደረጃጀቶች ስለ ደንቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች በስፋት እንደሚያዘጋጅ በመግለጽ መድረኩን በይፋ አስጀምረዋል።
በመድረኩ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በወንዞች ዳርቻ ዙርያ ሰፊ ጥናቶችን በማጥናት ለማስተዳደር አመቺ እንዲሆን ደንቡን በማጸደቅ ተግባራዊነቱን ለማስጠበቅ በጋራ ለመስራት ሂደቱ መጀመሩን በማንሳት የከተማዋን የወንዝ ተፋሰስ ፅዱ፣ ውብ እና ምቹ ሆነው አገልግሎት ላይ እንዲውሉ በየደረጃው ላሉ አካላት ግንዛቤ መፍጠር ተቀዳሚ ተግባር እንደሚሆን ገልጸዋል።
በመቀጠልም የአዲስ አበባ ወንዞች ብክለት የሚገኙበትን ደረጃ እንዲሁም ደንቡ የወጣበት ምክንያት እና ደንብ ቁጥር 180/2017 ቀርቦ ግንዛቤ ተፈጥሮበታል።
በመጨረሻም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ወንዞቻችን የብክለት ምክንያት ሳይሆኑ የኢኮኖሚያችን ምንጭ እንዲሆን ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በበቂ መንገድ በመፍጠር ለህጉ ተገዢ ባልሆኑ አካላት ላይ እርምጃዎችን በመውሰድ ደንብ የማስከበር ተልዕኮውን ተግባራዊ እንደሚደረግ አስገንዝበዋል።
የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉቀን ዮናስ እንዳሉት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የወንዝ ዳርቻዎችን በማልማት ከተማዋን አለም አቀፍ ደረጃዎች ያሟላች ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የግንዛቤ ስልጠናው በነገው እለትም ለፈፃሚ አካላቱ ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በቀጣይም እስከ ህብረተሰቡ ድረስ በየደረጃው እንደሚወርድ ተገልጿል።
ዘገባው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍1
የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
የካቲት 20/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባሉት ክፍት የስራ መደቦች ላይ ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በአካል በመምጣት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ ፒያሳ እሪ በከንቱ አካባቢ ከኤሊያና ሆቴስ ወደ አብርሆት ቤተ-መፅሐፍ በሚወስደው መንገድ /EMA/ ህንጻ 8ኛ ፎቅ የባለሥልጣኑ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 08/11 ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
በመሆኑም ዝርዝር መረጃውን የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም በወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ መመልከት ይችላሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
የካቲት 20/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባሉት ክፍት የስራ መደቦች ላይ ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በአካል በመምጣት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ ፒያሳ እሪ በከንቱ አካባቢ ከኤሊያና ሆቴስ ወደ አብርሆት ቤተ-መፅሐፍ በሚወስደው መንገድ /EMA/ ህንጻ 8ኛ ፎቅ የባለሥልጣኑ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 08/11 ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
በመሆኑም ዝርዝር መረጃውን የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም በወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ መመልከት ይችላሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
👍9
በወንዝና ወንዝ ዳርቻዎች ላይ የሚደርሱ ብክለቶችን ለመከላከል ይፋ በሆነው ደንብ ላይ ግንዛቤ ተፈጠረ።
21/6/2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፣ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ መንገዶች ባለስልጣን እና ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 አስመልክቶ ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቀቀ።
በልጠናው የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባለስጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን በማጎልበቱ የከተማ አስተዳሩን ልማቶች ለመጠበቅ ተልዕኮዎች እየተሰጡት መሆኑን ጠቅሰው፤ የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ዙሪያ በወጣው ደንብ ላይ የተሰጠንን የስራ ተልዕኮ ለመወጣት የግንዛቤ ፈጠራ አስፈላጊ በመሆኑ በየደረጃው ግንዛቤ ፈጠራው እንደሚቀጥል አፅኖት ሰጥተዋል።
በስልጠናው የወንዝና ወንዝ ዳርቻን ስለማልማትና ከብክለት ስለመከላከል፣ ስለ ተከለከሉ ተግባራት እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራር ስለቅጣት ዓይነቶች በሰፊው ገለፃ ተደርጓል።
ለማህበረሰቡ ከሚሰጠው ግንዛቤ በኃላ በቸልተኝነት ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ አካል ላይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር ሲሆን ከፍተኛው እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ የሚያስቀጣ እንደሆነ በደንቡ ተገልጿል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመስክ ክትትል ቁጥጥር ኦፊሰሮች ፣ የባለስልጣኑ ባለሙያዎች ፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
በመጨረሻም ከሰልጣኞች አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ሀላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
21/6/2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፣ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ መንገዶች ባለስልጣን እና ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 አስመልክቶ ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቀቀ።
በልጠናው የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባለስጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን በማጎልበቱ የከተማ አስተዳሩን ልማቶች ለመጠበቅ ተልዕኮዎች እየተሰጡት መሆኑን ጠቅሰው፤ የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ዙሪያ በወጣው ደንብ ላይ የተሰጠንን የስራ ተልዕኮ ለመወጣት የግንዛቤ ፈጠራ አስፈላጊ በመሆኑ በየደረጃው ግንዛቤ ፈጠራው እንደሚቀጥል አፅኖት ሰጥተዋል።
በስልጠናው የወንዝና ወንዝ ዳርቻን ስለማልማትና ከብክለት ስለመከላከል፣ ስለ ተከለከሉ ተግባራት እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራር ስለቅጣት ዓይነቶች በሰፊው ገለፃ ተደርጓል።
ለማህበረሰቡ ከሚሰጠው ግንዛቤ በኃላ በቸልተኝነት ደንቡን ተላልፎ በሚገኝ አካል ላይ ዝቅተኛው የገንዘብ ቅጣት ሁለት ሺህ ብር ሲሆን ከፍተኛው እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ድረስ የሚያስቀጣ እንደሆነ በደንቡ ተገልጿል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመስክ ክትትል ቁጥጥር ኦፊሰሮች ፣ የባለስልጣኑ ባለሙያዎች ፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
በመጨረሻም ከሰልጣኞች አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ሀላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍1