የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.09K subscribers
1.75K photos
4 videos
1 file
52 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ የቢሮ ሰራተኞች የደንብ ልብስን ይፋ አደረገ

የካቲት 13/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለቢሮ ሰራተኞች ያዘገጀውን የደንብ ልብስ ምርቃት ፕሮግራም በአድዋ ሙዚየም መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል ።

በፕሮግራሙ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ፣ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ፣የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና አውት ሶርሲንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን በቀለ ፣ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ኮ/ር አህመድ መሀመድ ፣የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎች ፣የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ የማዕከሉ ዳይሬክተሮችና ሰራተኞች ፣ኦፊሰሮች አንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አንደተናገሩት ቢሮው የተሰጠውን ተልዕኮ ከማከናወን ጎን ለጎን የሪፎርምና የለውጥ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱንና በዛሬው ዕለትም የዚሁ ሁለንተናዊ ሪፎርም አካል የሆነው ለቢሮ ሰራተኞች የተዘጋጀውንየ ደንብ ልብስ የማስተዋወቅ ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል ።

አክለውም የተቋም ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር የስራ ቦታን ለሰራተኛው እና ለተገልጋዮች ምቹና ማራኪ አድርጓል፤ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ስማርት ቢሮ ለመገንባት በሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና አውት ሶርሲንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን በቀለ ከተማችን አዲስ አበባ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሪፎርም ስራ በማስፋት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በማከናወን ከተማችን እንደ ስሞ አዲስና ውብ እንድትሆን 24/7 ጠንክሮ በመስረት የተለያዩ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውና በመመረቃቸው ከተማችንን ውብና ድንቅ ከተማ ማድረግ እንደተቻለው የአገልግሎት አሰጣጡንም በዚያ ደረጃ ማሻሻል እና አገልግሎትን በስታንዳርድ ልክ መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ተቋሙ የተሰጠዉን ተልዕኮ ለመወጣትና ለስራዎች መሳካት የአመራሩና የሰራተኛው ቅንጅትና ግንኙነት በቀጣይም አጠናክሮ በማስቀጠል የስራ አፈጻጸሙን ከዚህ የተሻለ በማድረግ ውጤታማነቱን ማረጋገጥ ይችላል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከየት ወዴት ? በሚል የተዘጋጀው ሰነድ እና የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የተቋማት፣ዳይሬክተሮች፣ቡድኖች ፈጻሚዎች ምዘና ሪፖርት በባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥ ድጋፍና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል ።

በሰነዱ ባለስልጣኑ ከተመሰረተበት ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ አስከ አሁን ድረስ ያለው ነባራዊ ሁኔታና ያከናወናቸው ተግባራት ፣መዋቅራዊ አደረጃጀቶቹ በዝርዝር ተገልጿል ።

በመድረኩ በባለስልጣኑ የተለዩ የትጉህ ሰራተኞች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ባለስልጣጣኑ "ሰው ተኮር ተግባሮቻችን ለአብሮነታችን" በሚል መሪ ቃል የአቅመ ደካማ እናት ቤት እድሳት አጠናቆ ለባለቤቱ የቁልፍ ርክክብ አደረገ

13/06/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ "ሰው ተኮር ተግባሮቻችን ለአብሮነታችን" በሚል መሪ ቃል በወረዳ 02 ለሚገኙ አቅመ ደካማ የመኖሪያ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ አስረከበ፡፡

በቤቱ ምርቃት መርሀ-ግብር ላይ የአዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለ ስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ፣የወረዳ ደንብ ማስከበር አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

በፕሮግራሙ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥ ተግባራትን ከመከላከል ጎን ለጎን ወደ ማህበረሰቡ በመውረድ ሰው ተኮር የበጎፍቃድ ስራዎችን በመስራት ለህብረተሰቡ ያለውን አለኝታነት በተግባር እያሳየ ይገኛል ይህ ሰው ተኮር በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በምርቃት ፕሮግራሙ የኮልፌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ በኑሮአቸው ዝቅተኛ ገቢ ላላቸውና ረዳት ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች በሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ በክ/ከተማው በቤት እድሳት፣ማእድ በማጋራትና በሌሎች የተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡

አክለውም የብልፅግና እሳቤ ከሆነው የሰው ተኮር ስራ አንዱ በዛሬው እለት በክፍለ ከተማው ያሉ ወረዳዎችን በማስተባበር የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክበዋል በቤት እድሳት ወቅት አስተዋጾ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የቤት እድሳት የተደረገላት የወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሙሪዳ አወል ከደንብ ማስከበር አመራርና አባላት ለተደረገላቸው ድጋፍ ከልብ አመስግነዋል፡፡

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍2
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 የግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራም አካሂዷል ።

15 /06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 የመጀመሪያ ስድሰት ወር የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ።

በመርሀ ግብሩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ፣ የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ፣ ሌሎች አመራሮችና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ተቋሙ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እየሠራና እንዲሁም ስራዎችን በቴክኖሎጂ በማዘመን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝና የኦፊሰሮችን ጥቅማ ጥቅም ለማስጠበቅ ሰፊ ስራ አየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።

በዋናነትም ማንኛውንም የተቋሙን ተልዕኮ ስንወጣ በፍጹም ስነ-ምግባርና ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ኃላፊነታችን በታማኝነት አንወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመድረኩ የተገኙት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ በክ/ከተማው ሚሰተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ እና የአደባባይ በአላትና የአፍርካ ህብረት ጉባኤ ሰላማዊ ሆኖ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ተቋም ከሌሎች አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራዎችን መሰራቱንና ክ/ከተማውም እውቅና መስጠቱን አሰታውቀዋል፡፡

የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ በግማሽ ዓመቱ በክ/ከተማው እንደ ጽ/ቤት የነበረውን እቅድ አፈጻጸም ሲገልጹ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰቶችን በመከላከልና በመቆጣጠር ደንብ ተላላፊ ከሆኑ አካላት ከቅጣት 7 ሚሊዮን ብር ለመንግስት ገቢ መደረጉን ገልፀዋል።

በመጨረሻም በ2017በጀት ዓመት በስድስት ወራት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች የእውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን
1ኛ ወረዳ 01
2ኛ ወረዳ 03
3ኛ ወረዳ 05 በመሆናቸው የዋንጫና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆነዋል።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡