ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አከናወነ።
10 -06 -2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት አካሄደ፡፡
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ 38 የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ከአመራሩ ጀምሮ እስከ ኦፊሰሩ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባሙ መወጣትና መፈጸም ችሏል ለዚህም ለሰራው መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን በማቅረብ መጪው ሳምንት ስራዎቻችን በአግባቡ የምንወጣበት የደስታ ሳምንት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ የራሳቸውን የህይወትና የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
ባለስልጣኑ ሁልጊዜ አዳዲስ ሀሳቦችን ፣ተግባራትን ለማወቅ በሞመከር ጥረት ውስጥ ማለፍ ዉጤታማና ስኬታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል ፡፡
በተጨማሪም በመድረኩ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት" (ICSMIS ) ሲስተሙን የመጠቀሚያ ስም እና ማለፊያ ቃል በማዘጋጀት የዓመት እረፍትና የስራ ልምድ በሲስተም የሚጠየቅ መንገድ መመቻቸቱን የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ገልጸዋል
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
10 -06 -2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት አካሄደ፡፡
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ 38 የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ከአመራሩ ጀምሮ እስከ ኦፊሰሩ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባሙ መወጣትና መፈጸም ችሏል ለዚህም ለሰራው መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን በማቅረብ መጪው ሳምንት ስራዎቻችን በአግባቡ የምንወጣበት የደስታ ሳምንት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ የራሳቸውን የህይወትና የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
ባለስልጣኑ ሁልጊዜ አዳዲስ ሀሳቦችን ፣ተግባራትን ለማወቅ በሞመከር ጥረት ውስጥ ማለፍ ዉጤታማና ስኬታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል ፡፡
በተጨማሪም በመድረኩ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት" (ICSMIS ) ሲስተሙን የመጠቀሚያ ስም እና ማለፊያ ቃል በማዘጋጀት የዓመት እረፍትና የስራ ልምድ በሲስተም የሚጠየቅ መንገድ መመቻቸቱን የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ገልጸዋል
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍12❤2👏2
የደንብ ማስከበር ተግባርን ወደ መሬት ለማዉረድ ኦፊሰሩን በስነ-ምግባር ማነጽ ይገባል ተባለ
11/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ህገወጥ ተግባር የመከላከል፣ የመቆጣጠር እና እርምጃ የመዉሰድ ተልዕኮውን ለመወጣት በስነ-ምግባር ኦፊሰርን ለማብቃት የሚያስችል ስልጠና በየካ ክፍለ ከተማ አዳራሽ አካሄደ።
በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማው ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ቡድን መሪ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
በእለቱ ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ብልሹ አሠራርን ከመልካም አስተዳደር አኳያ በማየት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለችግሩ መፍትሔ ማስቀመጥ የስልጠናው ዓላማ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በመሆኑም ባለስልጣኑ ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር እንዲያደርስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እየሠጠ እንደሚገኝና በቀጣይም ክፍተት የታየባቸውን ቦታዎች ላይ ትኩረት በማድረግ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጽዋል።
በውይይቱም ላይ ከመዋቅር ጋር በተያያዘ ፣ የደመወዝ ልዩነት እና ሌሎች ጥቅማ ጥቅም በሚመለከት የተለያዪ ጥያቄዎች በውይይቱ ተነስቷል።
ኦፊሰሩ ከህዝቡ ወቶ ሠልጥኖ መልሶ ህብረተሰቡን የሚያገለግል እንደመሆኑ ሁልጊዜ እራሱን ከብልሹ አሠራር የጸዳ ህብረተሰቡን በታማኝነት የሚያገለግል ሊሆን ይገባል በሚል በውይይቱ ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቷል።
በመጨረሻም የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አያልነህ ሙላቱ በማጠቃለያዉ ላይ ባስተላለፋት መልክት እንደ ከተማም ሆነ ክፍለ ከተማ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ስራዎች የተሳለጠ እንዲሆን የደንብ ማስከበር ኦፊሰሩ ከስልጠናዉ ያገኘውን እውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እራሱን በስነ-ምግባር እና መልካም አስተዳደር በማነጽ የአገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ተልዕኮውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።፥
11/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ህገወጥ ተግባር የመከላከል፣ የመቆጣጠር እና እርምጃ የመዉሰድ ተልዕኮውን ለመወጣት በስነ-ምግባር ኦፊሰርን ለማብቃት የሚያስችል ስልጠና በየካ ክፍለ ከተማ አዳራሽ አካሄደ።
በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማው ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ቡድን መሪ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
በእለቱ ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ብልሹ አሠራርን ከመልካም አስተዳደር አኳያ በማየት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለችግሩ መፍትሔ ማስቀመጥ የስልጠናው ዓላማ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በመሆኑም ባለስልጣኑ ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር እንዲያደርስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እየሠጠ እንደሚገኝና በቀጣይም ክፍተት የታየባቸውን ቦታዎች ላይ ትኩረት በማድረግ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጽዋል።
በውይይቱም ላይ ከመዋቅር ጋር በተያያዘ ፣ የደመወዝ ልዩነት እና ሌሎች ጥቅማ ጥቅም በሚመለከት የተለያዪ ጥያቄዎች በውይይቱ ተነስቷል።
ኦፊሰሩ ከህዝቡ ወቶ ሠልጥኖ መልሶ ህብረተሰቡን የሚያገለግል እንደመሆኑ ሁልጊዜ እራሱን ከብልሹ አሠራር የጸዳ ህብረተሰቡን በታማኝነት የሚያገለግል ሊሆን ይገባል በሚል በውይይቱ ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቷል።
በመጨረሻም የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አያልነህ ሙላቱ በማጠቃለያዉ ላይ ባስተላለፋት መልክት እንደ ከተማም ሆነ ክፍለ ከተማ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ስራዎች የተሳለጠ እንዲሆን የደንብ ማስከበር ኦፊሰሩ ከስልጠናዉ ያገኘውን እውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እራሱን በስነ-ምግባር እና መልካም አስተዳደር በማነጽ የአገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ተልዕኮውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።፥
👍3😁1
ባለስልጣኑ ከሰላምና ጸጥታ ጋር በመሆን ከበጎፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር የእግር ኳስ ውድድር አካሄደ
11/06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ከሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋራ በመሆን ከበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ሰረተኞች ጋር በተደረገው የእግር ኳስ ጨዋታ አምስት ለሶስት በሆነ ውጤት በማሸነፍ ተጠናቋል።
ውድድሩ ስፖርት ለሰላም በሚል መሪ-ቃል የተደረገ ሲሆን የደንብ ማስከበርና የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሰራተኞች ቡድን 5 ለ3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
ጨዋታው ባለስልጣኑ በቀጣይ ለሚያቋቁመው ተስፋ የሚጣልባቸው ተጫዋቾች የታየበት ሲሆን በፍጹም የስፖርታዊ ጨዋነት
ተጠናቋል።
11/06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ከሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋራ በመሆን ከበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ሰረተኞች ጋር በተደረገው የእግር ኳስ ጨዋታ አምስት ለሶስት በሆነ ውጤት በማሸነፍ ተጠናቋል።
ውድድሩ ስፖርት ለሰላም በሚል መሪ-ቃል የተደረገ ሲሆን የደንብ ማስከበርና የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሰራተኞች ቡድን 5 ለ3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
ጨዋታው ባለስልጣኑ በቀጣይ ለሚያቋቁመው ተስፋ የሚጣልባቸው ተጫዋቾች የታየበት ሲሆን በፍጹም የስፖርታዊ ጨዋነት
ተጠናቋል።
👏2
ባለስልጣኑ የስድስተኛ ዙር የኦፊሰር የምልመላ ሂደት በተመለከተ ውይይት አካሄደ
11-06 -2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስድስተኛ ዙር የኦፊሰር ምልመላ ሂደት እና የነባር ኦፊሰሮች ምደባ ዙሪያ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተካሄደ ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለተቋሙ ህገ-ወጥነትና ብልሹ አሰራርን የሚጸየፍ ፤የከተማውን ደህንነት የሚያስጠብቅና ለስራዎች መሳካት ዝግጁ የሆነ አባል ስለሚያስፈልገው የምልመላ መስፈርቱን መሠረት በማድረግ የሚያሞሉ ወጣቶችን ብቻ መመዝገብ እንዳለበት ገልጸዋል ።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በበኩላቸው እንደተናገሩት የሚመዘገቡት ምልምል ኦፊሰሮች የወጣውን የዕድሜ ፣ የትምህርት ማስረጃ ፣ የአቋም፣ የስነምግባርና የመሳሰሉት መስፈርቶችን የሚያሟሉትን ጥርት ባለ መልኩ ምልመላ ማካሄድ ይገባናል ሲሉ ገልጸዋል ።
በውይይቱ መድረኩ የስድስተኛ ዙር የኦፊሰር ምልመላ ምዝገባ ሂደት አሁናዊ ሪፖርት የተመረጡ ክፍለ ከተሞች አቅርበው
የሰልጣኞች ምልመላም የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸል በመሆኑ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ምዝገባው መጀመራቸውና መስፈርቱን የሚያሟሉ ሰልጣኞች በወረዳዎች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ የክ/ከተማ ኃላፊዎች ገልጸዋል ፡፡
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ስነ-ምግባር የተላበሰና የሰላም ሀይል ለከተማው ሆኖ የሚያገለግል የኦፊሰር ምልመላ ለማድረግ ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል ።
አክለውም ከአደረጃጀት አመራርና ከፖለቲካ አመራር ጋር የምልመላ ሁኔታውን የጋራ ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በመድረኩ የኦፊሰሩን ሁኔታ ያገናዘበ የስራ መደብ ሁኔታ በማዘጋጀት ጥናት ተጠናቆ ወደ ተግባር መገባቱ ገልጸው ምደባው በጥንቃቄና በመመሪያው መሠረት መከናወን እንዳለበት የባለስልጣኑ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ተናግረዋል ።
በመጨረሻም በውይይቱ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች በባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቶበታል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
11-06 -2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስድስተኛ ዙር የኦፊሰር ምልመላ ሂደት እና የነባር ኦፊሰሮች ምደባ ዙሪያ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተካሄደ ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለተቋሙ ህገ-ወጥነትና ብልሹ አሰራርን የሚጸየፍ ፤የከተማውን ደህንነት የሚያስጠብቅና ለስራዎች መሳካት ዝግጁ የሆነ አባል ስለሚያስፈልገው የምልመላ መስፈርቱን መሠረት በማድረግ የሚያሞሉ ወጣቶችን ብቻ መመዝገብ እንዳለበት ገልጸዋል ።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ በበኩላቸው እንደተናገሩት የሚመዘገቡት ምልምል ኦፊሰሮች የወጣውን የዕድሜ ፣ የትምህርት ማስረጃ ፣ የአቋም፣ የስነምግባርና የመሳሰሉት መስፈርቶችን የሚያሟሉትን ጥርት ባለ መልኩ ምልመላ ማካሄድ ይገባናል ሲሉ ገልጸዋል ።
በውይይቱ መድረኩ የስድስተኛ ዙር የኦፊሰር ምልመላ ምዝገባ ሂደት አሁናዊ ሪፖርት የተመረጡ ክፍለ ከተሞች አቅርበው
የሰልጣኞች ምልመላም የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸል በመሆኑ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ምዝገባው መጀመራቸውና መስፈርቱን የሚያሟሉ ሰልጣኞች በወረዳዎች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ የክ/ከተማ ኃላፊዎች ገልጸዋል ፡፡
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ስነ-ምግባር የተላበሰና የሰላም ሀይል ለከተማው ሆኖ የሚያገለግል የኦፊሰር ምልመላ ለማድረግ ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል ።
አክለውም ከአደረጃጀት አመራርና ከፖለቲካ አመራር ጋር የምልመላ ሁኔታውን የጋራ ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በመድረኩ የኦፊሰሩን ሁኔታ ያገናዘበ የስራ መደብ ሁኔታ በማዘጋጀት ጥናት ተጠናቆ ወደ ተግባር መገባቱ ገልጸው ምደባው በጥንቃቄና በመመሪያው መሠረት መከናወን እንዳለበት የባለስልጣኑ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ተናግረዋል ።
በመጨረሻም በውይይቱ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች በባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቶበታል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍2👏2