የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.09K subscribers
1.73K photos
4 videos
1 file
52 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ በቀጣይ ለሚሰጠው የ6ኛ ዙር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና በተመለከተ ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር የስልጠና እቅድ ውይይት አደረገ ::

6 - 06 2017
አዲስ አበባ

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቀጣይ ለሚሰጠው 6ተኛ ዙር ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ስርአተ ትምህርት እና አጠቃላይ የስልጠና ሂደቱን እቅድ ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አድርጓል::

ስልጠና በንድፈ ሀሳብ እና በአካል ብቃት የጎለበተ ህጉን ከቃል በበለጠ መሬት ላይ ማስከበር የሚችል ኦፊሰር ከማፍራት አንፃር ጉልህ ሚና አለው ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በስልጠናው ዘርፈ ብዙ ልምድ ካለው ተቋም ጋር መስራታችን በንድፈ ሀሳብ በአካል ብቃትም የጎለበተ የሰው ሀይል ለመገንባት ጉልህ ሚና አለው ብለዋል::

አጠቃላይ የስልጠና ሂደቱን በሚመለከት ስርአተ ትምህርቱን እና አጠቃላይ የበጀት እቅድ ሰነድ በስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በወ/ሮ ላቀች ሃይሌ የቀረበ ሲሆን በሰነዱም ስለ ስልጠናው አላማ፣ የጊዜ ሰሌዳ፣ የሰው ሀይል ትንተና፣ስለ ትምህርት እና ፈተና አሰጣጥና የምዘና ሂደት እንዲሁም የግብአት እና በጀት ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጓል::

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ም/ጀነራል መስፍን አበበ በመጡት አመራሮች በእውቀት እና በአካል የዳበረ የሰው ሀይልን ይዞ እንደተቋም ለመራመድ ታስቦ ይህ ስልጠና መዘጋጀቱ መልካም መሆኑ ገልጸው ይህ እቅድ እንዲሳካ ዩኒቨርሲቲው የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጸዋል ::

በመጨረሻም ከቤቱ የተነሱትን ሀሳብ እና አስተያየቶች የጋራ በማድረግ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ተገልጿል።
👍16👏4
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በየ15 ቀኑ የሚታተመው ትምህርታዊ አምድ
👍21🥰3👏1
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አከናወነ።

10 -06 -2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት አካሄደ፡፡

የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ 38 የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ከአመራሩ ጀምሮ እስከ ኦፊሰሩ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባሙ መወጣትና መፈጸም ችሏል ለዚህም ለሰራው መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን በማቅረብ መጪው ሳምንት ስራዎቻችን በአግባቡ የምንወጣበት የደስታ ሳምንት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ።

በዕለቱ የባለስልጣኑ የስታንዳርዳይዜሽን ዝግጅት፣ አገልግሎት አሰጣጥድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ የራሳቸውን የህይወትና የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።

ባለስልጣኑ ሁልጊዜ አዳዲስ ሀሳቦችን ፣ተግባራትን ለማወቅ በሞመከር ጥረት ውስጥ ማለፍ ዉጤታማና ስኬታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል ፡፡

በተጨማሪም በመድረኩ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት" (ICSMIS ) ሲስተሙን የመጠቀሚያ ስም እና ማለፊያ ቃል በማዘጋጀት የዓመት እረፍትና የስራ ልምድ በሲስተም የሚጠየቅ መንገድ መመቻቸቱን የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ገልጸዋል

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍122👏2
የደንብ ማስከበር ተግባርን ወደ መሬት ለማዉረድ ኦፊሰሩን በስነ-ምግባር ማነጽ ይገባል ተባለ

11/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ህገወጥ ተግባር የመከላከል፣ የመቆጣጠር እና እርምጃ የመዉሰድ ተልዕኮውን ለመወጣት በስነ-ምግባር ኦፊሰርን ለማብቃት የሚያስችል ስልጠና በየካ ክፍለ ከተማ አዳራሽ አካሄደ።

በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማው ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ቡድን መሪ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።

በእለቱ ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ብልሹ አሠራርን ከመልካም አስተዳደር አኳያ በማየት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለችግሩ መፍትሔ ማስቀመጥ የስልጠናው ዓላማ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በመሆኑም ባለስልጣኑ ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር እንዲያደርስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እየሠጠ እንደሚገኝና በቀጣይም ክፍተት የታየባቸውን ቦታዎች ላይ ትኩረት በማድረግ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጽዋል።

በውይይቱም ላይ ከመዋቅር ጋር በተያያዘ ፣ የደመወዝ ልዩነት እና ሌሎች ጥቅማ ጥቅም በሚመለከት የተለያዪ ጥያቄዎች በውይይቱ ተነስቷል።

ኦፊሰሩ ከህዝቡ ወቶ ሠልጥኖ መልሶ ህብረተሰቡን የሚያገለግል እንደመሆኑ ሁልጊዜ እራሱን ከብልሹ አሠራር የጸዳ ህብረተሰቡን በታማኝነት የሚያገለግል ሊሆን ይገባል በሚል በውይይቱ ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አያልነህ ሙላቱ በማጠቃለያዉ ላይ ባስተላለፋት መልክት እንደ ከተማም ሆነ ክፍለ ከተማ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ስራዎች የተሳለጠ እንዲሆን የደንብ ማስከበር ኦፊሰሩ ከስልጠናዉ ያገኘውን እውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እራሱን በስነ-ምግባር እና መልካም አስተዳደር በማነጽ የአገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ተልዕኮውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።፥
👍3😁1