የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት 38ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለሰራተኞቹ የስራ ስምሪት መስጠቱ ገለፀ
5/06/2017
**አዲስ አበባ**
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት 38ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታና በሰላም እንዲጠናቀቅ ለክፍለ ከተማው ፓራሚሊተሪ ሰራተኞች የስራ ስምሪት (ኦረንቴሽን) ሰጥቷል ፡፡
በመድረኩ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂርጳሳ እንደገለፁት እንግዶች በምቹ ሁኔታ ጉባኤያቸውን አጠናቀው ወደ ሀገራቸው በሰላም እንዲመለሱ ሽፍት በማጠፍ አዳርን ጨምሮ የበኩሉን የፀጥታ ስራ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት 24 ሰዓት እንዲሰሩ ጥብቅ ስምሪት መሰጠቱና ክትትለሰ መጀመሩ ገልጿል ፡፡
በተያያዘ ዜና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በኮሊደር ልማት መንገድ አህዮች ሲያዘዋውር የተገኘው ግለሰብ ወድያው በቀጠና ኦፊሠሮች በቁጥጥር ሰር ውለው 5000/አምስት ሺህ/ ብር በመቅጣት ወደ ፋይናስ ገቢ ሆኗል።
5/06/2017
**አዲስ አበባ**
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት 38ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታና በሰላም እንዲጠናቀቅ ለክፍለ ከተማው ፓራሚሊተሪ ሰራተኞች የስራ ስምሪት (ኦረንቴሽን) ሰጥቷል ፡፡
በመድረኩ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂርጳሳ እንደገለፁት እንግዶች በምቹ ሁኔታ ጉባኤያቸውን አጠናቀው ወደ ሀገራቸው በሰላም እንዲመለሱ ሽፍት በማጠፍ አዳርን ጨምሮ የበኩሉን የፀጥታ ስራ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት 24 ሰዓት እንዲሰሩ ጥብቅ ስምሪት መሰጠቱና ክትትለሰ መጀመሩ ገልጿል ፡፡
በተያያዘ ዜና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በኮሊደር ልማት መንገድ አህዮች ሲያዘዋውር የተገኘው ግለሰብ ወድያው በቀጠና ኦፊሠሮች በቁጥጥር ሰር ውለው 5000/አምስት ሺህ/ ብር በመቅጣት ወደ ፋይናስ ገቢ ሆኗል።
👍5👏2
ባለስልጣኑ በሁለተኛው የብልጽግና መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ከሰራተኞቹ ጋር ውይይት አካሄደ
06/06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል በ2ኛ የብልፀግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ።
በውይይት መድረኩ የሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ዙሪያ የተዘጋጀው ሰነድ በባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
በመድረኩም የፓርቲው የጉባዔ ውሳኔዎችና የቀጣይ አቅጣጫዎች በዝርዝር ቀርበዉ ሰፊ ዉይይት ተደርጓል የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ላይ ቀጣይ ትኩተረት ሊሰጣቸው እንደሚገቡ አቅጣጫ በተቀመጠባቸው ነጥቦች በዝርዝር ቀርበዋል፡፡
በውይይቱ የባለስልጣኑ አመራር እና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን ጠንካራ ተቋም መገንባት፣ ብሄራዊ ገዥ ትርክትን ማጠናከር ፣ የኢኮኖሚ እና ልማትን ከማፋጠን፣ ማህበራዊ ብልጽግና ከማረጋገጥ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራዎችን መሠራቱ ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ፓርቲው በአጭር ጊዜ በኢኮኖሚ ፣ በማህበራዊ እና በዲፕሎማሲው ረገድ አመርቂ ለውጦች ማምጣት ተችሏል ቀጣይነት እንዲኖረው ሁሉም የመንግስት ሰራተኛ የሚጠበቅበትን ሃላፊነት መወጣት ይኖርበታል ብለዋል።
06/06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል በ2ኛ የብልፀግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ።
በውይይት መድረኩ የሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ዙሪያ የተዘጋጀው ሰነድ በባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
በመድረኩም የፓርቲው የጉባዔ ውሳኔዎችና የቀጣይ አቅጣጫዎች በዝርዝር ቀርበዉ ሰፊ ዉይይት ተደርጓል የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ላይ ቀጣይ ትኩተረት ሊሰጣቸው እንደሚገቡ አቅጣጫ በተቀመጠባቸው ነጥቦች በዝርዝር ቀርበዋል፡፡
በውይይቱ የባለስልጣኑ አመራር እና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን ጠንካራ ተቋም መገንባት፣ ብሄራዊ ገዥ ትርክትን ማጠናከር ፣ የኢኮኖሚ እና ልማትን ከማፋጠን፣ ማህበራዊ ብልጽግና ከማረጋገጥ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራዎችን መሠራቱ ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ፓርቲው በአጭር ጊዜ በኢኮኖሚ ፣ በማህበራዊ እና በዲፕሎማሲው ረገድ አመርቂ ለውጦች ማምጣት ተችሏል ቀጣይነት እንዲኖረው ሁሉም የመንግስት ሰራተኛ የሚጠበቅበትን ሃላፊነት መወጣት ይኖርበታል ብለዋል።
👍6👏2🥰1
ባለስልጣኑ በቀጣይ ለሚሰጠው የ6ኛ ዙር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና በተመለከተ ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር የስልጠና እቅድ ውይይት አደረገ ::
6 - 06 2017
አዲስ አበባ
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቀጣይ ለሚሰጠው 6ተኛ ዙር ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ስርአተ ትምህርት እና አጠቃላይ የስልጠና ሂደቱን እቅድ ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አድርጓል::
ስልጠና በንድፈ ሀሳብ እና በአካል ብቃት የጎለበተ ህጉን ከቃል በበለጠ መሬት ላይ ማስከበር የሚችል ኦፊሰር ከማፍራት አንፃር ጉልህ ሚና አለው ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በስልጠናው ዘርፈ ብዙ ልምድ ካለው ተቋም ጋር መስራታችን በንድፈ ሀሳብ በአካል ብቃትም የጎለበተ የሰው ሀይል ለመገንባት ጉልህ ሚና አለው ብለዋል::
አጠቃላይ የስልጠና ሂደቱን በሚመለከት ስርአተ ትምህርቱን እና አጠቃላይ የበጀት እቅድ ሰነድ በስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በወ/ሮ ላቀች ሃይሌ የቀረበ ሲሆን በሰነዱም ስለ ስልጠናው አላማ፣ የጊዜ ሰሌዳ፣ የሰው ሀይል ትንተና፣ስለ ትምህርት እና ፈተና አሰጣጥና የምዘና ሂደት እንዲሁም የግብአት እና በጀት ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጓል::
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ም/ጀነራል መስፍን አበበ በመጡት አመራሮች በእውቀት እና በአካል የዳበረ የሰው ሀይልን ይዞ እንደተቋም ለመራመድ ታስቦ ይህ ስልጠና መዘጋጀቱ መልካም መሆኑ ገልጸው ይህ እቅድ እንዲሳካ ዩኒቨርሲቲው የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጸዋል ::
በመጨረሻም ከቤቱ የተነሱትን ሀሳብ እና አስተያየቶች የጋራ በማድረግ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ተገልጿል።
6 - 06 2017
አዲስ አበባ
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቀጣይ ለሚሰጠው 6ተኛ ዙር ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ስርአተ ትምህርት እና አጠቃላይ የስልጠና ሂደቱን እቅድ ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አድርጓል::
ስልጠና በንድፈ ሀሳብ እና በአካል ብቃት የጎለበተ ህጉን ከቃል በበለጠ መሬት ላይ ማስከበር የሚችል ኦፊሰር ከማፍራት አንፃር ጉልህ ሚና አለው ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በስልጠናው ዘርፈ ብዙ ልምድ ካለው ተቋም ጋር መስራታችን በንድፈ ሀሳብ በአካል ብቃትም የጎለበተ የሰው ሀይል ለመገንባት ጉልህ ሚና አለው ብለዋል::
አጠቃላይ የስልጠና ሂደቱን በሚመለከት ስርአተ ትምህርቱን እና አጠቃላይ የበጀት እቅድ ሰነድ በስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በወ/ሮ ላቀች ሃይሌ የቀረበ ሲሆን በሰነዱም ስለ ስልጠናው አላማ፣ የጊዜ ሰሌዳ፣ የሰው ሀይል ትንተና፣ስለ ትምህርት እና ፈተና አሰጣጥና የምዘና ሂደት እንዲሁም የግብአት እና በጀት ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጓል::
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ም/ጀነራል መስፍን አበበ በመጡት አመራሮች በእውቀት እና በአካል የዳበረ የሰው ሀይልን ይዞ እንደተቋም ለመራመድ ታስቦ ይህ ስልጠና መዘጋጀቱ መልካም መሆኑ ገልጸው ይህ እቅድ እንዲሳካ ዩኒቨርሲቲው የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጸዋል ::
በመጨረሻም ከቤቱ የተነሱትን ሀሳብ እና አስተያየቶች የጋራ በማድረግ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ተገልጿል።
👍16👏4